📌ቬሮኒካ አዳነ በናይጄሪያ አሳዛኝ ነገር ገጠማት
"የሚያሳዝን ቀን ነበር በናይጄሪያ ያሳለፍኩት"
ኢትዮጵያዊቷ የሙዚቃ ኮከብ ቬሮኒካ አዳነ በመላው አፍሪካ ትልቅ ግምት የሚሰጠውን የ9ኛው የአፍሪካ ሙዚቃ ሽልማት (AFRIMA) በአሸናፊነት አጠናቃለች። ቬሮኒካ በናይጄሪያ ሌጎስ በተካሄደው በዚህ ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ፦"The Best Artist, Duo or Group in African Traditional Music" በሚለው ዘርፍ አህጉራዊ ተፎካካሪዎቿን በመብለጥ ድልን ተቀዳጅታለች።
ከሽልማቱ በስተጀርባ ያለው አሳዛኝ ክስተት ምንድን ነው?
ድምፃዊቷ በሽልማት ስነ-ስርዓቱ ላይ ለምን አልታየሽም ለሚሏት ደጋፊዎቿ በማህበራዊ ትስስር ገጿ በሰጠችው ምላሽ በናይጄሪያ የገጠማት ነገር አስከፊ እንደነበር እንዲህ ስትል ገልጻለች.. ተጨማሪውን ያንብቡ:- https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/23
"የሚያሳዝን ቀን ነበር በናይጄሪያ ያሳለፍኩት"
ኢትዮጵያዊቷ የሙዚቃ ኮከብ ቬሮኒካ አዳነ በመላው አፍሪካ ትልቅ ግምት የሚሰጠውን የ9ኛው የአፍሪካ ሙዚቃ ሽልማት (AFRIMA) በአሸናፊነት አጠናቃለች። ቬሮኒካ በናይጄሪያ ሌጎስ በተካሄደው በዚህ ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ፦"The Best Artist, Duo or Group in African Traditional Music" በሚለው ዘርፍ አህጉራዊ ተፎካካሪዎቿን በመብለጥ ድልን ተቀዳጅታለች።
ከሽልማቱ በስተጀርባ ያለው አሳዛኝ ክስተት ምንድን ነው?
ድምፃዊቷ በሽልማት ስነ-ስርዓቱ ላይ ለምን አልታየሽም ለሚሏት ደጋፊዎቿ በማህበራዊ ትስስር ገጿ በሰጠችው ምላሽ በናይጄሪያ የገጠማት ነገር አስከፊ እንደነበር እንዲህ ስትል ገልጻለች.. ተጨማሪውን ያንብቡ:- https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/23
🖕15❤6😁4🤔2💩2👎1👏1
📌 የገና ኢግዚቢሽን ውዝግብ አስነሳ
በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ለ2018 ዓ.ም የገና በዓል የተሰናዳው የንግድ ባዛር እና ኤግዚቢሽን መጠናቀቁን ተከትሎ በተፈጠረ የክፍያ ውዝግብ፣ አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች እና ታዋቂ ግለሰቦች ንብረታቸውን ማውጣት አለመቻላቸው ተሰማ።
የውዝግቡ መነሻ የ2018 ዓ.ም የገና እና የፋሲካ በዓልን በኤግዚቢሽን ማዕከል እንዲያሰናዳ ጨረታውን አሸንፎ ውል የወሰደው "ዳሰማ ትሬዲንግ" የተሰኘው ተቋም ነው። ይህ ተቋም ለዝግጅቱ ድምቀት እና አገልግሎት አሰጣጥ ከተለያዩ አካላት ጋር የኮንትራት ስምምነት ፈጽሞ ነበር።
ከእነዚህም መካከል "አብረሃም የድግስ ዕቃ አከራይ" በኤግዚቢሽን ማዕከሉ ውስጥ የተተከሉትን ድንኳኖች በማቅረብ፣ እንዲሁም አንጋፋው ድምጻዊ ዳዊት ጽጌ የመድረክ እና የሙዚቃ ሥራዎችን ሙሉ በሙሉ በኮንትራት ወስደው አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል።
ኤግዚቢሽኑ መጠናቀቁን ተከትሎ እነዚህ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ንብረታቸውን ከማዕከሉ ለማውጣት ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል። ለዚህም በምክንያትነት...
ዝርዝሩን ያንብቡ:https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/25
በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ለ2018 ዓ.ም የገና በዓል የተሰናዳው የንግድ ባዛር እና ኤግዚቢሽን መጠናቀቁን ተከትሎ በተፈጠረ የክፍያ ውዝግብ፣ አገልግሎት አቅራቢ ድርጅቶች እና ታዋቂ ግለሰቦች ንብረታቸውን ማውጣት አለመቻላቸው ተሰማ።
የውዝግቡ መነሻ የ2018 ዓ.ም የገና እና የፋሲካ በዓልን በኤግዚቢሽን ማዕከል እንዲያሰናዳ ጨረታውን አሸንፎ ውል የወሰደው "ዳሰማ ትሬዲንግ" የተሰኘው ተቋም ነው። ይህ ተቋም ለዝግጅቱ ድምቀት እና አገልግሎት አሰጣጥ ከተለያዩ አካላት ጋር የኮንትራት ስምምነት ፈጽሞ ነበር።
ከእነዚህም መካከል "አብረሃም የድግስ ዕቃ አከራይ" በኤግዚቢሽን ማዕከሉ ውስጥ የተተከሉትን ድንኳኖች በማቅረብ፣ እንዲሁም አንጋፋው ድምጻዊ ዳዊት ጽጌ የመድረክ እና የሙዚቃ ሥራዎችን ሙሉ በሙሉ በኮንትራት ወስደው አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል።
ኤግዚቢሽኑ መጠናቀቁን ተከትሎ እነዚህ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ንብረታቸውን ከማዕከሉ ለማውጣት ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል። ለዚህም በምክንያትነት...
ዝርዝሩን ያንብቡ:https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/25
❤7😢2🍌1
📌ልዑል ሲሳይ እና 10 ነፃ ትኬቶች
ከድምፃዊ ልዑል ሲሳይ ጋር ኑ ቡና ጠጡ ነፃ 10 ትኬቶች አዘጋጅተናል። ይህን ፖስት ለ10 ሰዎች ሼር ያደርጉ።
ከተወዳጁ ድምፃዊ ልዑል ሲሳይ ጋር ቡና እየጠጣችሁ መስራት የምትፈልጉዋቸውን ስራዎች ከእሱ ጋር የምታወሩበት እና የምትወያዩበት መድረክ የፊታችን ቅዳሜ እንደሚካሄድ ይታወቃል።
የራሳችሁን ሥራዎች እንዲሁም ያለውን ልምድ አንድ ለአንድ በሚፈጠረው መድረክ ላይ ስለሰራቸው ሙዚቃዎች እንዲሁም ቀጣይ ስለሚያስባቸው ስራዎቹ የሚያካፍልበት የሲንክ አፕ ቻት ፕሮግራም ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ላይ መሳተፍ ለምትፈልጉ ሙዚቃ ላይ ፍላጎት ያላችሁ እንዲሁም የድምፃዊው አድናቂ ለሆናችሁ አድናቂዎች 10 ነፃ ትኬቶችን አዘጋጅተናል።
ትኬቱን ለማግኘት ይህ ፖስት ለአስር ሰዎች ሼር ያድርጉ:
📅️️️️ ቀን ፡ ጥር 9
⏰️️️️️️️ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ
📍️️️️ቦታ ፡ ጋዬ ቡና ልደታ ባልቻ ሆስፒታል ፊት ለፊት ( ካፕስቶን ህንፃ )
🎟️️️️ ተጨማሪ ትኬቶችን ለመግዛት
- መደበኛ - 500 ብር ( ከ ነፃ ቡና ጋር )
- ቪአይፒ - 1000 ብር ( ከነፃ ቡና እና ምግብ ጋር )
ያለውን ቦታ ውስን ስለሆነች አሁኑኑ ትኬቱን ይቁረጡ
ትኬትዎን ለመቁረጥ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ👇️️️️️️
https://linktr.ee/SyncUp.chat
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ከድምፃዊ ልዑል ሲሳይ ጋር ኑ ቡና ጠጡ ነፃ 10 ትኬቶች አዘጋጅተናል። ይህን ፖስት ለ10 ሰዎች ሼር ያደርጉ።
ከተወዳጁ ድምፃዊ ልዑል ሲሳይ ጋር ቡና እየጠጣችሁ መስራት የምትፈልጉዋቸውን ስራዎች ከእሱ ጋር የምታወሩበት እና የምትወያዩበት መድረክ የፊታችን ቅዳሜ እንደሚካሄድ ይታወቃል።
የራሳችሁን ሥራዎች እንዲሁም ያለውን ልምድ አንድ ለአንድ በሚፈጠረው መድረክ ላይ ስለሰራቸው ሙዚቃዎች እንዲሁም ቀጣይ ስለሚያስባቸው ስራዎቹ የሚያካፍልበት የሲንክ አፕ ቻት ፕሮግራም ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ላይ መሳተፍ ለምትፈልጉ ሙዚቃ ላይ ፍላጎት ያላችሁ እንዲሁም የድምፃዊው አድናቂ ለሆናችሁ አድናቂዎች 10 ነፃ ትኬቶችን አዘጋጅተናል።
ትኬቱን ለማግኘት ይህ ፖስት ለአስር ሰዎች ሼር ያድርጉ:
📅️️️️ ቀን ፡ ጥር 9
⏰️️️️️️️ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ
📍️️️️ቦታ ፡ ጋዬ ቡና ልደታ ባልቻ ሆስፒታል ፊት ለፊት ( ካፕስቶን ህንፃ )
🎟️️️️ ተጨማሪ ትኬቶችን ለመግዛት
- መደበኛ - 500 ብር ( ከ ነፃ ቡና ጋር )
- ቪአይፒ - 1000 ብር ( ከነፃ ቡና እና ምግብ ጋር )
ያለውን ቦታ ውስን ስለሆነች አሁኑኑ ትኬቱን ይቁረጡ
ትኬትዎን ለመቁረጥ ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ👇️️️️️️
https://linktr.ee/SyncUp.chat
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤6👏2🥰1😁1👌1
📌የኢትዮጵያዊ ምግቦች ፌስቲቫል ተዘጋጅ
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ኢትዮጵያዊ ምግቦች የሚቀርቡበት ፌስቲቫል ሊያዘጋጅ መሆኑን አስታወቀ፡፡
"ጋስትሮኖሚ" የተሰኘው ፌስቲቫሉ የሚዘጋጀው የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ጎልደን ግሩፕ ሆስፒታሊቲ ከተሰኘ ድርጅት ጋር በመተባበር ነው፡፡
የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ክፍት በሚሆነው በዚህ ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያዊ ምግቦች፣ የምግብ ግብአት አቅራቢዎች በሆቴሎችና በዘርፉ የተሰማሩ ከ100 በላይ ድርጅቶች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽነር አቶ ሁንዴ ከበደ የጥምቀት ከተራ በአልን አስታኮ በተዘጋጀው በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የውጭ አገር ዜጎች የሚታደሙ ሲሆን ከ20 ሺህ በላይ ሰዎችም ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ መግለጻቸውን ኤ.ኤም.ኤን ዘግቧል፡፡
ፌስቲቫሉ በሚሊኒየም አዳራሽ ጥር 9 እና 10 ለሁለት ቀናት ለህዝብ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ በዘገባው ተመላክቷል፡፡
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ኢትዮጵያዊ ምግቦች የሚቀርቡበት ፌስቲቫል ሊያዘጋጅ መሆኑን አስታወቀ፡፡
"ጋስትሮኖሚ" የተሰኘው ፌስቲቫሉ የሚዘጋጀው የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ጎልደን ግሩፕ ሆስፒታሊቲ ከተሰኘ ድርጅት ጋር በመተባበር ነው፡፡
የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ክፍት በሚሆነው በዚህ ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያዊ ምግቦች፣ የምግብ ግብአት አቅራቢዎች በሆቴሎችና በዘርፉ የተሰማሩ ከ100 በላይ ድርጅቶች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽነር አቶ ሁንዴ ከበደ የጥምቀት ከተራ በአልን አስታኮ በተዘጋጀው በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የውጭ አገር ዜጎች የሚታደሙ ሲሆን ከ20 ሺህ በላይ ሰዎችም ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ መግለጻቸውን ኤ.ኤም.ኤን ዘግቧል፡፡
ፌስቲቫሉ በሚሊኒየም አዳራሽ ጥር 9 እና 10 ለሁለት ቀናት ለህዝብ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ በዘገባው ተመላክቷል፡፡
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤4❤🔥1👎1
📌የኢትዮጵያ ፖስፖርት 90ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል
በ'Henley' የፓስፖርት መለኪያ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ከአለም 90ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በአለማችን ላይ የሚገኙ 199 ፓስፖርቶችን እና 227 የጉዞ መዳረሻዎችን መሰረት በማድረግ የፓስፖርቱ ባለቤቶች ያለ ቪዛ ምን ያህል ቦታዎች መሄድ እንደሚችሉ በማየት ደረጃ የሚሰጠው የ'Henley' የ2026 የፓስፖርት ደረጃ ይፋ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ፓስፖርት ኢራን፣ ሲንጋፖርና ታይላንድን ጨምሮ ወደ 43 መዳረሻዎች ያለ ቪዛ በመውሰድ..ተጨማሪውን ያንብቡ: https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/28
በ'Henley' የፓስፖርት መለኪያ የኢትዮጵያ ፓስፖርት ከአለም 90ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በአለማችን ላይ የሚገኙ 199 ፓስፖርቶችን እና 227 የጉዞ መዳረሻዎችን መሰረት በማድረግ የፓስፖርቱ ባለቤቶች ያለ ቪዛ ምን ያህል ቦታዎች መሄድ እንደሚችሉ በማየት ደረጃ የሚሰጠው የ'Henley' የ2026 የፓስፖርት ደረጃ ይፋ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ፓስፖርት ኢራን፣ ሲንጋፖርና ታይላንድን ጨምሮ ወደ 43 መዳረሻዎች ያለ ቪዛ በመውሰድ..ተጨማሪውን ያንብቡ: https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/28
❤3😁3
📌ታዋቂው ራፐር ኢትዮጵያን ማየት እፈልጋለሁ አለ
የአይሾው ስፒድ አስደናቂ የኢትዮጵያ ቆይታ ሌላኛውን ዝነኛ አሜሪካዊ ራፐር ዲዲጂን (DDG) ወደ ኢትዮጵያ እንዲሳብ አድርጎታል።
በኢትዮጵያ ባህልና እስክስታ ቀድሞውኑ የሚማረከው ዲዲጂ፣ አሁን ደግሞ በቀጥታ ስርጭት በተመለከተው እውነታ ረክቶ "ምድረ ቀደምቷን" ለመጎብኘት ያለውን ጽኑ ፍላጎት በይፋ አጋርቷል።
የአይሾው ስፒድን የቀጥታ ስርጭት ከተመለከተ በኋላ ከፍተኛ መነሳሳት ስለተፈጠረበት ዲዲጂ በኤክስ (X) ገጹ ወደ ኢትዮጵያ የመምጣት ፍላጎቱን አጋርቷል።
ልጥፉም ከ730 ሺህ በላይ ዕይታን አግኝቷል። በርካታ ተከታዮቹና ሌሎች ዓለምአቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪዎችም ጉዞውን እንደሚደግፉና ምድረ ቀደምት ወደ ሆነችው ኢትዮጵያ የሚያደርገው ጉዞ ስኬታማ እንዲሆንለት እያበረታቱት ይገኛሉ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የአይሾው ስፒድ አስደናቂ የኢትዮጵያ ቆይታ ሌላኛውን ዝነኛ አሜሪካዊ ራፐር ዲዲጂን (DDG) ወደ ኢትዮጵያ እንዲሳብ አድርጎታል።
በኢትዮጵያ ባህልና እስክስታ ቀድሞውኑ የሚማረከው ዲዲጂ፣ አሁን ደግሞ በቀጥታ ስርጭት በተመለከተው እውነታ ረክቶ "ምድረ ቀደምቷን" ለመጎብኘት ያለውን ጽኑ ፍላጎት በይፋ አጋርቷል።
የአይሾው ስፒድን የቀጥታ ስርጭት ከተመለከተ በኋላ ከፍተኛ መነሳሳት ስለተፈጠረበት ዲዲጂ በኤክስ (X) ገጹ ወደ ኢትዮጵያ የመምጣት ፍላጎቱን አጋርቷል።
ልጥፉም ከ730 ሺህ በላይ ዕይታን አግኝቷል። በርካታ ተከታዮቹና ሌሎች ዓለምአቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪዎችም ጉዞውን እንደሚደግፉና ምድረ ቀደምት ወደ ሆነችው ኢትዮጵያ የሚያደርገው ጉዞ ስኬታማ እንዲሆንለት እያበረታቱት ይገኛሉ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
😁7❤3🔥3👍2😱2
📌ለኢትዮጵያ ፍልስፍና አስፈላጊ መሆኑ ተገለፀ
ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ችግሮች ለመፍታት ውይይትና አመክንዮ ላይ የተመሰረተ ማህበረሰብ እንደሚያስፈልግ ተነግሯል።
ማህበረሰቡ ፍልስፍና ላይ ያለውን አረዳድና የዘርፉን ፋይዳ በሚመለከት የፍልስፍና መምህሩ ዶክተር ፋሲል መራዊ ከአራዳ ኤፍ.ኤም ጋር በነበራችው ቆይታ እንዳሉት ፥ ከዚህ ቀደም ፍልስፍና ከሃይማኖትና እሴት ጋር የሚቃረን አድርጎ የማሰብ የተሳሳተ አረዳድ መኖሩን ጠቅሰዋል።
ነገር ግን አሁን ላይ ፍልስፍናዊ ሃሳቦችን ማስተናገድ የሚችል ትውልድ እየተፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል።
ፍልስፍና ሚና ያለው መሆኑንና ወጣ ካሉ ሃሳቦች ባሻገር የነገ መንገዱን በራሱ ልክ መስፋት የሚችል ጠያቂ ትውልድ ለመፍጠር እንደሚያግዝም አስረድተዋል።
በተመሳሳይ ሌላኛው የፍልስፍና መምህር ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ይህንን ሃሳብ አጠናክረዋል።
በኢትዮጵያ ፍልስፍና እየዳበረ መምጣቱን የገለፁት ምሁራኑ፥ አንድ ሕዝብ መለወጥ እና መዘመን እንዲችል ሃሳብ መሰረታዊ መሆኑን ብሎም ሃሳብ በሂደት ሲያረጅ ደግሞ ፍልስፍናዊ ጥያቄዎችን ማንሳትና የክርክር ባህልን ማዳበር አስፈላጊ ስለመሆኑም ነው ያብራሩት።
©️ዘገባው የአራዳ ኤፍ አም ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ችግሮች ለመፍታት ውይይትና አመክንዮ ላይ የተመሰረተ ማህበረሰብ እንደሚያስፈልግ ተነግሯል።
ማህበረሰቡ ፍልስፍና ላይ ያለውን አረዳድና የዘርፉን ፋይዳ በሚመለከት የፍልስፍና መምህሩ ዶክተር ፋሲል መራዊ ከአራዳ ኤፍ.ኤም ጋር በነበራችው ቆይታ እንዳሉት ፥ ከዚህ ቀደም ፍልስፍና ከሃይማኖትና እሴት ጋር የሚቃረን አድርጎ የማሰብ የተሳሳተ አረዳድ መኖሩን ጠቅሰዋል።
ነገር ግን አሁን ላይ ፍልስፍናዊ ሃሳቦችን ማስተናገድ የሚችል ትውልድ እየተፈጠረ መሆኑን አስረድተዋል።
ፍልስፍና ሚና ያለው መሆኑንና ወጣ ካሉ ሃሳቦች ባሻገር የነገ መንገዱን በራሱ ልክ መስፋት የሚችል ጠያቂ ትውልድ ለመፍጠር እንደሚያግዝም አስረድተዋል።
በተመሳሳይ ሌላኛው የፍልስፍና መምህር ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ይህንን ሃሳብ አጠናክረዋል።
በኢትዮጵያ ፍልስፍና እየዳበረ መምጣቱን የገለፁት ምሁራኑ፥ አንድ ሕዝብ መለወጥ እና መዘመን እንዲችል ሃሳብ መሰረታዊ መሆኑን ብሎም ሃሳብ በሂደት ሲያረጅ ደግሞ ፍልስፍናዊ ጥያቄዎችን ማንሳትና የክርክር ባህልን ማዳበር አስፈላጊ ስለመሆኑም ነው ያብራሩት።
©️ዘገባው የአራዳ ኤፍ አም ነው።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤13👎2😁2
📌አዲስ ማለዳ ለጋዜጠኞች ማስታወቂያ አውጥቷል
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
1. የሥራ መደብ፡- ሪፖርተር
የትምህርት ደረጃ፡- በጋዜጠኝነትና ሥነ ተግባቦት እንዲሁም በተዛማጅ የትምህርት መስኮች የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ት
ልምድ፡- ቢያንስ ከአንድ ዓመት በላይ የሰራ/ች፣ በህትመትና ዲጂታል ሚዲያ ላይ የሰራ/ች ቢሆን ይመረጣል
ብዛት፡- 2
ደመወዝ፡- በድርጅቱ ስኬል መሠረት
2. የሥራ መደብ፡- አርታኢ
የትምህርት ደረጃ፡- በጋዜጠኝነትና ሥነ ተግባቦት እንዲሁም በተዛማጅ የማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ት፡፡ በሌላ ትምህርት መስክ የተማሩ ቢሆንም በሥራ ላይ የቆዩ ከሆነ መወዳደር ይችላሉ፡፡
ልምድ፡- አራት ዓመትና ከዚያ በላይ፣ በህትመትና በዲጂታል ሚዲያ ላይ የሰራ/ች
ብዛት፡- 1
ደመወዝ፡- በድርጅቱ ስኬል መሠረት
አድራሻ፡- አዲስ አበባ፣ ቦሌ ሆምስ (ከቦሌ ወደ ገርጂ በሚወስደው መንገድ ላይ ከአርጀንቲና ኤምባሲ ጀርባ)
ኢሜይል፡- addismaleda@gmail.com
ይህ ማስታወቂያ ከወጣ በኋላ ባሉት ተከታታይ አምስት የሥራ ቀናት የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃዎን ያስገቡ!
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
1. የሥራ መደብ፡- ሪፖርተር
የትምህርት ደረጃ፡- በጋዜጠኝነትና ሥነ ተግባቦት እንዲሁም በተዛማጅ የትምህርት መስኮች የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ት
ልምድ፡- ቢያንስ ከአንድ ዓመት በላይ የሰራ/ች፣ በህትመትና ዲጂታል ሚዲያ ላይ የሰራ/ች ቢሆን ይመረጣል
ብዛት፡- 2
ደመወዝ፡- በድርጅቱ ስኬል መሠረት
2. የሥራ መደብ፡- አርታኢ
የትምህርት ደረጃ፡- በጋዜጠኝነትና ሥነ ተግባቦት እንዲሁም በተዛማጅ የማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ት፡፡ በሌላ ትምህርት መስክ የተማሩ ቢሆንም በሥራ ላይ የቆዩ ከሆነ መወዳደር ይችላሉ፡፡
ልምድ፡- አራት ዓመትና ከዚያ በላይ፣ በህትመትና በዲጂታል ሚዲያ ላይ የሰራ/ች
ብዛት፡- 1
ደመወዝ፡- በድርጅቱ ስኬል መሠረት
አድራሻ፡- አዲስ አበባ፣ ቦሌ ሆምስ (ከቦሌ ወደ ገርጂ በሚወስደው መንገድ ላይ ከአርጀንቲና ኤምባሲ ጀርባ)
ኢሜይል፡- addismaleda@gmail.com
ይህ ማስታወቂያ ከወጣ በኋላ ባሉት ተከታታይ አምስት የሥራ ቀናት የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃዎን ያስገቡ!
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤5
📌ሴት የሬዲዮ ፕሮግራም አቅራቢ ማስታወቂያ
ዳጉ ኮምኒኬሽን ሴት የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ ይፈልጋል::
የትምህርት ዝግጅትና ልምድ ያላችሁ በቴሌግራም ሊንክ @Manaye7450 ላይ ሲቪ መላክ ትችላላችሁ ::
ሔሎኢትዮጵያ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ዳጉ ኮምኒኬሽን ሴት የሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ ይፈልጋል::
የትምህርት ዝግጅትና ልምድ ያላችሁ በቴሌግራም ሊንክ @Manaye7450 ላይ ሲቪ መላክ ትችላላችሁ ::
ሔሎኢትዮጵያ በኤፍ ኤም አዲስ 97.1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤6
📌አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት፣ በተዋናይነትና በሌሎች የጥበብ ስራዎች ውስጥ ስመጥር እና ተወዳጅ ከሆኑ የጥበብ ሰዎች አንዱ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ከዚህ ዓለም እንደተለየ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን አስታውቋል።
ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነበር።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት፣ በተዋናይነትና በሌሎች የጥበብ ስራዎች ውስጥ ስመጥር እና ተወዳጅ ከሆኑ የጥበብ ሰዎች አንዱ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ከዚህ ዓለም እንደተለየ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን አስታውቋል።
ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነበር።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
😭94😢17😱9❤2🤯2
የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ የህይወት ታሪክ
አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ በተለይም በኮሜዲ ትወና እና በቴሌቭዥን አቀራረብ ዘርፍ እጅግ ተወዳጅ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ ባለሙያዎች አንዱ ነበር። የእርሱ ድንገተኛ ህልፈት እጅግ ልብ ሰባሪ ዜና ነው።
የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ የህይወት ታሪክ
እዚህ አዲስ አበባ ፒያሳ አከባቢ በ1975 አመተ ምህርት ተወልዶ ያደገው ነጻነት ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለ የህይወት ጥሪውን ለይቶ በማወቅ ለሚወደው የትያትር እና ጥበብ ራሱን የሰጠ እና በዚህም ለከፍተኛ ደረጃ የደረሰ አርቲስት ነበር፡፡
ተዋናይ፣ ኮሜዲያን፣ የቴሌቭዥን ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በኢትዮጵያ የፊልም እና የቴሌቭዥን ታሪክ ውስጥ የራሱን ልዩ የሆነ የአቀራረብ ስልት እና የትወና ጥበብ በማሳየት የሚታወቅ ባለሙያ ነበር።
ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሆኖ.... ተጨማሪውን ያንብቡ https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/38
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ በተለይም በኮሜዲ ትወና እና በቴሌቭዥን አቀራረብ ዘርፍ እጅግ ተወዳጅ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ ባለሙያዎች አንዱ ነበር። የእርሱ ድንገተኛ ህልፈት እጅግ ልብ ሰባሪ ዜና ነው።
የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ የህይወት ታሪክ
እዚህ አዲስ አበባ ፒያሳ አከባቢ በ1975 አመተ ምህርት ተወልዶ ያደገው ነጻነት ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለ የህይወት ጥሪውን ለይቶ በማወቅ ለሚወደው የትያትር እና ጥበብ ራሱን የሰጠ እና በዚህም ለከፍተኛ ደረጃ የደረሰ አርቲስት ነበር፡፡
ተዋናይ፣ ኮሜዲያን፣ የቴሌቭዥን ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ በኢትዮጵያ የፊልም እና የቴሌቭዥን ታሪክ ውስጥ የራሱን ልዩ የሆነ የአቀራረብ ስልት እና የትወና ጥበብ በማሳየት የሚታወቅ ባለሙያ ነበር።
ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሆኖ.... ተጨማሪውን ያንብቡ https://news.1rj.ru/str/NorRadio1/38
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
😭7❤4
📌 ነጻነት ወርቅነህ ዛሬ ጠዋት
ነጻነት ዛሬ ጠዋት ወደ ስራ ሊሄድ እየለባበሰ ነበረ። ህመም ሲሰማው ጓደኛውን ጠርቶት ወደ ICMC ሆስፒታል ሄዱ። መንገድ ላይ እያለም ህመሙ እየባሰበት ነበረ። ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ምሳ ሰዓት ገደማ አረፈ። ፖሊሶች በሆስፒታሉ ተገኝተው ሙያዊ የምርመራ ስራቸውን አከናውነዋል።
አሌልቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅበሩኝ
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በሕይወት እያለ ሲሞት አሌልቱ ጊዮርጊስ ከአያቱ አጠገብ ቀብሩ እንዲፈጸም እንደሚፈልግ ለወዳጆቹ ደጋግሞ ይናገር የነበረ ሲሆን ያለፈው ሳምንትም አሌልቱ ጊዮርጊስ በመሄድ ቤተክርስቲያኒቱን የማሳደስ ስራ ስለማከናወን ከሚመለከታቸው የቤተክርስቲያኒቱ ኃላፊዎች ጋር ተነጋግሮ መመለሱ ተሰምቷል።
ኑሮዋን በአሜሪካ ያደረገችው ባለቤቱ እና የልጆቹ እናት እሁድ ጠዋት ከአሜሪካ አዲስ አበባ የምትገባ ሲሆን በዚያው ሰዓት ስርዓተ ቀብሩ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።
©️ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ነጻነት ዛሬ ጠዋት ወደ ስራ ሊሄድ እየለባበሰ ነበረ። ህመም ሲሰማው ጓደኛውን ጠርቶት ወደ ICMC ሆስፒታል ሄዱ። መንገድ ላይ እያለም ህመሙ እየባሰበት ነበረ። ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ምሳ ሰዓት ገደማ አረፈ። ፖሊሶች በሆስፒታሉ ተገኝተው ሙያዊ የምርመራ ስራቸውን አከናውነዋል።
አሌልቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅበሩኝ
አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ በሕይወት እያለ ሲሞት አሌልቱ ጊዮርጊስ ከአያቱ አጠገብ ቀብሩ እንዲፈጸም እንደሚፈልግ ለወዳጆቹ ደጋግሞ ይናገር የነበረ ሲሆን ያለፈው ሳምንትም አሌልቱ ጊዮርጊስ በመሄድ ቤተክርስቲያኒቱን የማሳደስ ስራ ስለማከናወን ከሚመለከታቸው የቤተክርስቲያኒቱ ኃላፊዎች ጋር ተነጋግሮ መመለሱ ተሰምቷል።
ኑሮዋን በአሜሪካ ያደረገችው ባለቤቱ እና የልጆቹ እናት እሁድ ጠዋት ከአሜሪካ አዲስ አበባ የምትገባ ሲሆን በዚያው ሰዓት ስርዓተ ቀብሩ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።
©️ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
😢31❤15💔2
በሀዘን ምክንያት አልበሙ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል
የልጅ ተመስገን መለሰ "ኢቲዲኤም ቢትስ" የሙዚቃ አልበም ዛሬ ጥር 8 ከምሽቱ 12:00 ላይ እንደሚለቀቅ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ሀዘን ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንደተራዘመ አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ አስታውቀዋል።
አዘጋጆቹ ተከታዩን መልዕክት አስተላልፏል"በአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት ምክንያት ጥልቅ ሀዘን ስለተሰማን ዛሬ ማታ ጥር 8 ሊለቀቅ የነበረው የETDM Beats የልጅ ተመስገን መለሰ አልበም ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን በትህትና እናሳውቃለን። ለቤተሰቡ እና ለመላው አድናቂዎቹ መፀናናትን እንመኛለን"።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የልጅ ተመስገን መለሰ "ኢቲዲኤም ቢትስ" የሙዚቃ አልበም ዛሬ ጥር 8 ከምሽቱ 12:00 ላይ እንደሚለቀቅ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ሀዘን ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንደተራዘመ አዘጋጆቹ ለኤቨንት አዲስ ሚዲያ አስታውቀዋል።
አዘጋጆቹ ተከታዩን መልዕክት አስተላልፏል"በአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት ምክንያት ጥልቅ ሀዘን ስለተሰማን ዛሬ ማታ ጥር 8 ሊለቀቅ የነበረው የETDM Beats የልጅ ተመስገን መለሰ አልበም ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን በትህትና እናሳውቃለን። ለቤተሰቡ እና ለመላው አድናቂዎቹ መፀናናትን እንመኛለን"።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤19👍2
📌አርቲስት ገነት ንጋቱ ከፍተኛ ትችት ቀረበባት
ታዋቂዋ አርቲስት ገነት ንጋቱ፣ የሞያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት ተከትሎ በዩቲዩብ ቻናሏ ባሰራጨችው ዘገባ ምክንያት ከህዝብ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞ እየደረሰባት ይገኛል።
አርቲስት ገነት ንጋቱ በዩቲዩብ ቻናሏ፣ የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት አስመልክቶ ቪዲዮ ለቃለች።
በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ መድረኮች ላይ የሚገኙ ተከታታዮች እና የዘርፉ ባለሙያዎች የሚከተሉትን ትችቶች ሰንዝረዋል፦
በቪዲዮው ላይ የምታሳየው እጅግ የበረታ ለቅሶና ድርጊት "ለካሜራ ተብሎ የተሰራ (Acting)" እንጂ እውነተኛ ሀዘን አይመስልም የሚሉ አስተያየቶች በስፋት ተሰንዝረዋል።
የሞያ ስነ-ምግባር ጉድለት: "በጓደኛ ሞት ትርፍ ለማግኘት መሞከር ነውረኝነት ነው" በሚል ብዙዎች ተቃውሟቸውን ገልጸዋል።
የዩቲዩብ ገቢ (Monetization): በሀዘን ሰዓት ማስታወቂያዎችን የያዙ ረጅም ቪዲዮዎችን መልቀቋ፣ ጉዳዩን ከሰው ልጅ ስሜት ይልቅ ወደ ንግድ የቀየረችው አስመስሎባታል።
የክብር መሸርሸር: አርቲስቷ ቀደም ሲል የነበራትን ክብርና ዝና በዚህ ድርጊቷ እየቀነሰችው እንደሆነ አስተያየት ሰጪዎች አስገንዝበዋል።
አርቲስት ገነት ንጋቱ ለቀረቡባት ትችቶች እስካሁን የሰጠችው ዝርዝር ምላሽ ባይኖርም፣ ይህ ክስተት በኢትዮጵያ የዩቲዩብ ይዘት ፈጣሪዎች መካከል "የእይታ ብዛት (Views) ወይስ የሞያ ስነ-ምግባር?" የሚለውን ክርክር ዳግም እንዲቀሰቀስ አድርጎታል።
©️Fast mereja
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ታዋቂዋ አርቲስት ገነት ንጋቱ፣ የሞያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት ተከትሎ በዩቲዩብ ቻናሏ ባሰራጨችው ዘገባ ምክንያት ከህዝብ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞ እየደረሰባት ይገኛል።
አርቲስት ገነት ንጋቱ በዩቲዩብ ቻናሏ፣ የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት አስመልክቶ ቪዲዮ ለቃለች።
በተለያዩ የሶሻል ሚዲያ መድረኮች ላይ የሚገኙ ተከታታዮች እና የዘርፉ ባለሙያዎች የሚከተሉትን ትችቶች ሰንዝረዋል፦
በቪዲዮው ላይ የምታሳየው እጅግ የበረታ ለቅሶና ድርጊት "ለካሜራ ተብሎ የተሰራ (Acting)" እንጂ እውነተኛ ሀዘን አይመስልም የሚሉ አስተያየቶች በስፋት ተሰንዝረዋል።
የሞያ ስነ-ምግባር ጉድለት: "በጓደኛ ሞት ትርፍ ለማግኘት መሞከር ነውረኝነት ነው" በሚል ብዙዎች ተቃውሟቸውን ገልጸዋል።
የዩቲዩብ ገቢ (Monetization): በሀዘን ሰዓት ማስታወቂያዎችን የያዙ ረጅም ቪዲዮዎችን መልቀቋ፣ ጉዳዩን ከሰው ልጅ ስሜት ይልቅ ወደ ንግድ የቀየረችው አስመስሎባታል።
የክብር መሸርሸር: አርቲስቷ ቀደም ሲል የነበራትን ክብርና ዝና በዚህ ድርጊቷ እየቀነሰችው እንደሆነ አስተያየት ሰጪዎች አስገንዝበዋል።
አርቲስት ገነት ንጋቱ ለቀረቡባት ትችቶች እስካሁን የሰጠችው ዝርዝር ምላሽ ባይኖርም፣ ይህ ክስተት በኢትዮጵያ የዩቲዩብ ይዘት ፈጣሪዎች መካከል "የእይታ ብዛት (Views) ወይስ የሞያ ስነ-ምግባር?" የሚለውን ክርክር ዳግም እንዲቀሰቀስ አድርጎታል።
©️Fast mereja
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤13👍3
📌ኮሜዲያን ደረጀ ኃይሌ ምላሽ ሰጠ
"እኔ መቀረፄን አላውቅም።ሲበዛ ሆዳምነት እና ከተማረ ሰው የማይጠበቅ ነው"
አርቲስት ገነት ንጋቱ፣ የሞያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት ተከትሎ በዩቲዩብ ቻናሏ ባሰራጨችው ዘገባ ምክንያት ከህዝብ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞ እየደረሰባት ይገኛል።
አርቲስት ገነት ንጋቱ በዩቲዩብ ቻናሏ፣ የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት አስመልክቶ ቪዲዮ ለቃለች።
እዚህ ቪዲዮ ላይ ኮሜዲያን ደረጀ ኃይሌን በስልክ ስታነጋገረው ታይታለች።
ኮሜዲያን ደረጀ ኃይሌ ስለ ተፈጠረው ነገር ተከታዩን ብሏል "እኔ መቀረፄን አላውቅም።እንደ ቀደመ ወዳጅነታችን ሀዘኗን ልትገልፅ መስሎኝ ሆስፒታል ሆኜ ነው በጥልቅ ሀዘን ውስጥ ሆኜ ያዋራሁዋት ሲበዛ ብልግናና ሆዳምነት ነው።ከተማረ የማይጠበቅ " ሲል ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"እኔ መቀረፄን አላውቅም።ሲበዛ ሆዳምነት እና ከተማረ ሰው የማይጠበቅ ነው"
አርቲስት ገነት ንጋቱ፣ የሞያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት ተከትሎ በዩቲዩብ ቻናሏ ባሰራጨችው ዘገባ ምክንያት ከህዝብ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞ እየደረሰባት ይገኛል።
አርቲስት ገነት ንጋቱ በዩቲዩብ ቻናሏ፣ የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህን ህልፈት አስመልክቶ ቪዲዮ ለቃለች።
እዚህ ቪዲዮ ላይ ኮሜዲያን ደረጀ ኃይሌን በስልክ ስታነጋገረው ታይታለች።
ኮሜዲያን ደረጀ ኃይሌ ስለ ተፈጠረው ነገር ተከታዩን ብሏል "እኔ መቀረፄን አላውቅም።እንደ ቀደመ ወዳጅነታችን ሀዘኗን ልትገልፅ መስሎኝ ሆስፒታል ሆኜ ነው በጥልቅ ሀዘን ውስጥ ሆኜ ያዋራሁዋት ሲበዛ ብልግናና ሆዳምነት ነው።ከተማረ የማይጠበቅ " ሲል ተናግሯል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤12🤔1
📌አርቲስት ገነት ንጋቱ በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ዙሪያ ያሰራጨችውን ቪዲዮ አነሳች፤ የ"Unsubscribe" ዘመቻም ገጥሟታል
አርቲስት ገነት ንጋቱ የሙያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህን ህልፈት ተከትሎ በዩቲዩብ ቻናሏ ላይ አሰራጭታው የነበረውን ቪዲዮ ከገጿ ላይ ማንሳቷ ታወቀ።
አርቲስቷ ቪዲዮውን ለማንሳት የተገደደችው፣ ቪዲዮው የሟቹን ክብር የማይመጥንና ቤተሰቦቹን የሚጎዳ ነው በሚል ከህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞ ከበረታባት በኋላ መሆኑ ተገልጿል። በተለይም በሀዘን ወቅት እንዲህ ያሉ መረጃዎችን ለዕይታ ማግኛ (Views) መጠቀም ተገቢ አይደለም በሚል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰፊ ቁጣ ተቀስቅሷል።
ከቪዲዮው መነሳት ባሻገር፣ ድርጊቱ ያስቆጣቸው በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በአርቲስት ገነት ንጋቱ የዩቲዩብ ቻናል ላይ "Unsubscribe" የማድረግ ዘመቻ መጀመራቸው ታይቷል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
አርቲስት ገነት ንጋቱ የሙያ ባልደረባዋ የሆነውን የአርቲስት ነፃነት ወርቅነህን ህልፈት ተከትሎ በዩቲዩብ ቻናሏ ላይ አሰራጭታው የነበረውን ቪዲዮ ከገጿ ላይ ማንሳቷ ታወቀ።
አርቲስቷ ቪዲዮውን ለማንሳት የተገደደችው፣ ቪዲዮው የሟቹን ክብር የማይመጥንና ቤተሰቦቹን የሚጎዳ ነው በሚል ከህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ትችት እና ተቃውሞ ከበረታባት በኋላ መሆኑ ተገልጿል። በተለይም በሀዘን ወቅት እንዲህ ያሉ መረጃዎችን ለዕይታ ማግኛ (Views) መጠቀም ተገቢ አይደለም በሚል በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰፊ ቁጣ ተቀስቅሷል።
ከቪዲዮው መነሳት ባሻገር፣ ድርጊቱ ያስቆጣቸው በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በአርቲስት ገነት ንጋቱ የዩቲዩብ ቻናል ላይ "Unsubscribe" የማድረግ ዘመቻ መጀመራቸው ታይቷል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
👍26❤2
📌አርቲስት ገነት ንጋቱ በይፋ ይቅርታ ጠየቀች
"በትላንትናው እለት በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ህልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን ገልጬ ዜና መሰራቴ ይታወቃል::በዚህ ቪዲዮ ላይ ከወዳጄና ጏደኛዬ ኮሜዲያን ደረጄ ሃይሌ ጋር ያደረጉትን የስልክ ልውውጥ አካትቼለሁ::የእሱን ሃሳብ ጨምሮ ማካተቴ መላው የኢትዮጵያ ህዝብን ቅር አሰኝቷል::
"ቅሬታውም ተገቢ ነው ብዬ ስላመንኩ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ና አድናቂዎቼን ይቅርታ ለመጠየቅ እወዳለሁ:: በድጋሚ እጅግ የምወደው ወንድሜ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ እልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን በመግለፅ ለቤተሰቦቹ ለወዳጆቹ ለመላው አድናቂዎቹ መፅናናትን እመኛለሁ::ነፍሱን በአፀደ ገነት ያኑሩልን "
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"በትላንትናው እለት በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ህልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን ገልጬ ዜና መሰራቴ ይታወቃል::በዚህ ቪዲዮ ላይ ከወዳጄና ጏደኛዬ ኮሜዲያን ደረጄ ሃይሌ ጋር ያደረጉትን የስልክ ልውውጥ አካትቼለሁ::የእሱን ሃሳብ ጨምሮ ማካተቴ መላው የኢትዮጵያ ህዝብን ቅር አሰኝቷል::
"ቅሬታውም ተገቢ ነው ብዬ ስላመንኩ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ና አድናቂዎቼን ይቅርታ ለመጠየቅ እወዳለሁ:: በድጋሚ እጅግ የምወደው ወንድሜ አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ እልፈት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን በመግለፅ ለቤተሰቦቹ ለወዳጆቹ ለመላው አድናቂዎቹ መፅናናትን እመኛለሁ::ነፍሱን በአፀደ ገነት ያኑሩልን "
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
👎28❤9👍9🖕2
ቺባን ፕሮፐርቲስ አልፋ ሬዚደንስ ባለ 5 ኮከብ ሆቴል
ቺባን ፕሮፐርቲስ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ደረጃ ያለው "አልፋ ሬዚደንስ" የተሰኘ ቅንጡ አፓርትመንት አስተዋወቀ
በሀገራችን የግንባታ ዘርፍ ለ17 ዓመታት ስኬታማ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየው ቺባን ፕሮፐርቲስ፣ "ቺባን አልፋ ሬዚደንስ" የተሰኘ የባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ደረጃና አገልግሎት የሚሰጥ ቅንጡ (Luxury) አፓርትመንት ለገበያ ማቅረቡን አስታወቀ።
ይህ አዲስ አፓርትመንት በሀገሪቱ የሪል ስቴት ልማት ዘርፍ አዲስ የአኗኗር ዘይቤን ለማስተዋወቅ ታቅዶ የተገነባ ነው።
ለስምንት ዓመታት ያህል የገበያ ጥናትና ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው ይህ ፕሮጀክት፣ አሁን ላይ የግንባታው ሂደት ለነዋሪዎች ምቹ ወደሆነ ደረጃ መድረሱ ተገልጿል።
"ቺባን አልፋ ሬዚደንስ" ነዋሪዎች የቅንጡ ሆቴል አገልግሎትን በቤታቸው እንዲያገኙ በሚያስችል መልኩ የተደራጀ ሲሆን፣ የሚከተሉትን አገልግሎቶች አካቷል፦
ዘመናዊ መገልገያዎች፦ ሰፊ የሆቴል ሎቢ፣ ሬስቶራንት፣ ካፌ፣ የጂም ማዕከል እና በሀገራችን የመጀመሪያው የሆነ ትልቅ "ኢንፊኒቲ ፑል" (Infinity Pool) በህንጻው አናት ላይ ተገንብቶለታል።
የቤት አማራጮች፦ ከስቱዲዮ እስከ ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ በህንጻው አናት ላይ ባለ ሁለት ወለል ግዙፍና ቅንጡ ፔንት ሀውሶችን (Pent-houses) ይዟል።
ጥራትና ደህንነት፦ የቤቶቹ የውስጥ ዲዛይን (Interior) በአውሮፓ ስታንዳርድ በተመረቱ ቁሳቁሶች የተሟላ ነው። በተለይም ከወለል እስከ ኮርኒስ የሚደርሱት መስኮቶች ድምጽና ሙቀት የማይሰርጉ በመሆናቸው ለነዋሪዎች ሰላማዊ ድባብ ይፈጥራሉ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ቺባን ፕሮፐርቲስ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ደረጃ ያለው "አልፋ ሬዚደንስ" የተሰኘ ቅንጡ አፓርትመንት አስተዋወቀ
በሀገራችን የግንባታ ዘርፍ ለ17 ዓመታት ስኬታማ ስራዎችን ሲያከናውን የቆየው ቺባን ፕሮፐርቲስ፣ "ቺባን አልፋ ሬዚደንስ" የተሰኘ የባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ደረጃና አገልግሎት የሚሰጥ ቅንጡ (Luxury) አፓርትመንት ለገበያ ማቅረቡን አስታወቀ።
ይህ አዲስ አፓርትመንት በሀገሪቱ የሪል ስቴት ልማት ዘርፍ አዲስ የአኗኗር ዘይቤን ለማስተዋወቅ ታቅዶ የተገነባ ነው።
ለስምንት ዓመታት ያህል የገበያ ጥናትና ዝግጅት ሲደረግበት የቆየው ይህ ፕሮጀክት፣ አሁን ላይ የግንባታው ሂደት ለነዋሪዎች ምቹ ወደሆነ ደረጃ መድረሱ ተገልጿል።
"ቺባን አልፋ ሬዚደንስ" ነዋሪዎች የቅንጡ ሆቴል አገልግሎትን በቤታቸው እንዲያገኙ በሚያስችል መልኩ የተደራጀ ሲሆን፣ የሚከተሉትን አገልግሎቶች አካቷል፦
ዘመናዊ መገልገያዎች፦ ሰፊ የሆቴል ሎቢ፣ ሬስቶራንት፣ ካፌ፣ የጂም ማዕከል እና በሀገራችን የመጀመሪያው የሆነ ትልቅ "ኢንፊኒቲ ፑል" (Infinity Pool) በህንጻው አናት ላይ ተገንብቶለታል።
የቤት አማራጮች፦ ከስቱዲዮ እስከ ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ በህንጻው አናት ላይ ባለ ሁለት ወለል ግዙፍና ቅንጡ ፔንት ሀውሶችን (Pent-houses) ይዟል።
ጥራትና ደህንነት፦ የቤቶቹ የውስጥ ዲዛይን (Interior) በአውሮፓ ስታንዳርድ በተመረቱ ቁሳቁሶች የተሟላ ነው። በተለይም ከወለል እስከ ኮርኒስ የሚደርሱት መስኮቶች ድምጽና ሙቀት የማይሰርጉ በመሆናቸው ለነዋሪዎች ሰላማዊ ድባብ ይፈጥራሉ።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤8🤣1
📌"ትስስር " የሥዕል አውደርዕይ ተከፈተ
ስድስት እውቅ ሠዓሊያን ሥራዎቻቸውን በአንድነት ያቀረቡበት "ትስስር" የተሰኘ የሥዕል አውደ-ርዕይ፤ ሐሙስ ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም. በይፋ ተመርቆ ተከፍቷል።
ይህ ለዐይን ማራኪ የሆኑ ሥራዎች የቀረቡበት አውደ-ርዕይ፤ በመካሄድ ላይ የሚገኘው በአዲስ አበባው እምብርት አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ውስጥ በሚገኘው አርት ጋለሪ ነው።
በዚህ "ትስስር" በተሰኘው አውርደርዕይ ውስጥ የተሳተፉ ባለሙያዎች የየራሳቸው የሆነ ለየት ያለ የአሳሳል ዘይቤ እና ፍልስፍና ያላቸው ሲሆኑ፣ እነርሱም፦አገኘሁ አዳነ፣ልዕልሰገድ ረታ፣ኡስማን ሀሰን፣ስዩም አያሌው፣ታምራት ሱልጣን እናያሬድ ኦለቪሊያ ናቸው።
አውደ-ርዕዩ እስከ የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ለተከታታይ አንድ ወር ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ስድስት እውቅ ሠዓሊያን ሥራዎቻቸውን በአንድነት ያቀረቡበት "ትስስር" የተሰኘ የሥዕል አውደ-ርዕይ፤ ሐሙስ ጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም. በይፋ ተመርቆ ተከፍቷል።
ይህ ለዐይን ማራኪ የሆኑ ሥራዎች የቀረቡበት አውደ-ርዕይ፤ በመካሄድ ላይ የሚገኘው በአዲስ አበባው እምብርት አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ ውስጥ በሚገኘው አርት ጋለሪ ነው።
በዚህ "ትስስር" በተሰኘው አውርደርዕይ ውስጥ የተሳተፉ ባለሙያዎች የየራሳቸው የሆነ ለየት ያለ የአሳሳል ዘይቤ እና ፍልስፍና ያላቸው ሲሆኑ፣ እነርሱም፦አገኘሁ አዳነ፣ልዕልሰገድ ረታ፣ኡስማን ሀሰን፣ስዩም አያሌው፣ታምራት ሱልጣን እናያሬድ ኦለቪሊያ ናቸው።
አውደ-ርዕዩ እስከ የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ለተከታታይ አንድ ወር ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል ተብሏል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
❤6👍4
📌የጆኒ ራጋ ጀማው ኮንሰርት ተሰርዟል
የድምጻዊ ጆኒ ራጋ "ጀማው" ኮንሰርት በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት እንደተሰርዘ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከድምጻዊው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።የተሰረዘው ኮንሰርትም የፊታችን አርብ ጥር 15 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ጆኒ ራጋ ስለጉዳዩ ተከታዩን ብሏል"እስካሁን ትኬት ቆርጣችሁ በመጠበቅ ላይ ያላችሁትን ሁሉ በታላቅ ትህትና ይቅርታ እየጠየቅን በአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት ጀማው ኮንሰርትን ለመጪው አርብ ጥር 15 ማዘውራችንን ለሁሉም ጀማ እንድታደርሱልን በአክብሮት እንጠይቃለን"
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
የድምጻዊ ጆኒ ራጋ "ጀማው" ኮንሰርት በአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት እንደተሰርዘ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከድምጻዊው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።የተሰረዘው ኮንሰርትም የፊታችን አርብ ጥር 15 2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል።
ጆኒ ራጋ ስለጉዳዩ ተከታዩን ብሏል"እስካሁን ትኬት ቆርጣችሁ በመጠበቅ ላይ ያላችሁትን ሁሉ በታላቅ ትህትና ይቅርታ እየጠየቅን በአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ድንገተኛ ህልፈት ምክንያት ጀማው ኮንሰርትን ለመጪው አርብ ጥር 15 ማዘውራችንን ለሁሉም ጀማ እንድታደርሱልን በአክብሮት እንጠይቃለን"
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
👏16❤3👍2
📌 "ካሜራ አንፈልግም " የነፃነት ወርቅነህ ቤተሰብ
"ቀረፃም ሆነ የላይቭ ስርጭት ማድረግ የተከለከለ ነው"
ተከታዩ መልዕክት ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣የስራ ባልደረቦች፣ የቅርብ እና የሩቅ ዘመዶች ያገኘው መልዕክት ነው።
"በምንወደው ወንድማችን አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ የቀብር ሥነሥርዓት ላይ ዩቱበሮች፣ ቲክቶከሮች፣ እንዲሁም በተለያዩ ሚዲያዎች ምንም ዓይነት ቀረፃም ሆነ የላይቭ ስርጭት ማድረግ የተከለከለ ነው" ሲሉ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም "አሁን ልባችን ተሰብሯል የምንፈልገው ሀዘናችንን መወጣት ነው። የእናንተን ካሜራ ግርግር ዛሬን አንፈልግም እባካችሁ እንደ ባህላችን እንደ ወጋችን ሀዘናችንን በሚገባ እንወጣው። ነፃነታችንን አትጋፉ! በጣም ደክሞናል"ብለዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
"ቀረፃም ሆነ የላይቭ ስርጭት ማድረግ የተከለከለ ነው"
ተከታዩ መልዕክት ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከአርቲስት ነፃነት ወርቅነህ ቤተሰቦች፣ ጓደኞች፣የስራ ባልደረቦች፣ የቅርብ እና የሩቅ ዘመዶች ያገኘው መልዕክት ነው።
"በምንወደው ወንድማችን አርቲስት ነፃነት ወርቅነህ የቀብር ሥነሥርዓት ላይ ዩቱበሮች፣ ቲክቶከሮች፣ እንዲሁም በተለያዩ ሚዲያዎች ምንም ዓይነት ቀረፃም ሆነ የላይቭ ስርጭት ማድረግ የተከለከለ ነው" ሲሉ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም "አሁን ልባችን ተሰብሯል የምንፈልገው ሀዘናችንን መወጣት ነው። የእናንተን ካሜራ ግርግር ዛሬን አንፈልግም እባካችሁ እንደ ባህላችን እንደ ወጋችን ሀዘናችንን በሚገባ እንወጣው። ነፃነታችንን አትጋፉ! በጣም ደክሞናል"ብለዋል።
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
ለተጨማሪው: https://news.1rj.ru/str/EventAddis1
👍53❤16👏10👎2🙏1