TechVibe – Telegram
TechVibe
742 subscribers
460 photos
34 videos
33 files
208 links
I'm Eyob, a self-taught dev sharing my Tech journey, tips, tools, and real-world projects. Let’s grow together😊

DM for any project ideas @alnova19

Personal site: https://eyobsimachew.vercel.app
My Github: https://github.com/Eyob-smax
Download Telegram
43ኛው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሄደ፡፡
===========================
መጋቢት 16/2016 ዓ.ም (ትሚ) 43ኛው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሂዷል፡፡

ሙሉ ዜናው👇
https://www.facebook.com/share/p/4CyUSuffFwVaKnzr/?mibextid=Nif5oz
በድጋፍ የተገኙት የህክምና ቁሳቁሶች የህክምና ዘርፉን የመማር ማስተማር ተግባር ለማሻሻል ለሚደረገው ስራ የላቀ አስተዋፆ እንዳላቸው ተገለፀ፡፡
======================
ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የባዮሜዲካል ቴክኒሻኖችንና መሐንዲሶችን ስልጠና ለማሳደግ እና በሆስፒታሎች ውስጥ ያለውን የህክምና አገልግሎት ለማሻሻል በጀርመን የፋይናንስ ትብብር፣ በጀርመን ልማት ባንክ KFW የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡ ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፣
https://www.facebook.com/share/p/4azpZTEjtnR4P3VZ/?mibextid=oFDknk
ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ውጤታማነት አጋር አካላት የድርሻቸውን እንዲውጡ ጥሪ ቀረበ።

ዲቪቪ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት የ30 ዓመታት ጉዞን የተመለከተ ኮንፈረንስ ተካሂዷል።
-----------------------//--------------------------
በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማትር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሽቴ ሀገራችን መደበኛ ትምህርት ያላገኙ ዜጎችን የመማር መብት ለማረጋገጥና የተማሩ ዜጎችን ቁጥር ለማሳደግ ባለፉት ዓመታት የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራምን በመዘርጋት ውጤታማ ስራ ሰርታለች ብለዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0FxgzBbLxu3iLXRGFnDooGUNoaNN11JeBZGm7pYT5LLr1HaAfkpxQSKyCRssbnh2Ml&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ አብዱራህማን ኢድ ጣሂር ጋር በመሆን ‘Top Gravity’ ከተባለ የህትመት ተቋም ጋር በጋራ ለመስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጫኑ። https://www.linkedin.com/posts/toppan-gravity-ethiopia_industrialprinting-collaboration-innovation-ugcPost-7185654197235683329-d7XZ?utm_source=share&utm_medium=member_android
እና
https://www.linkedin.com/posts/toppan-gravity_toppan-eih-innovation-activity-7188069238941638656-TVHw?utm_source=share&utm_medium=member_android


ከዚሁ ጋር በተያያዘ ክቡር ሚኒስትሩ ጃፓን፣ ቶኪዮ በሚገኘው የ ‘Top Gravity ‘ዋና መስሪያ ቤት የስራ ጉብኝት በማድረግ ከተቋሙን ዋና ስራ አስፈጻሚ እና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት የሚከተሉትን ሊንኮች ይጫኑ፤
https://www.linkedin.com/posts/ethiopian-investment-holdings_ethiopia-partnership-globalbusiness-ugcPost-7185619860398219264-O1h0?utm_source=share&utm_medium=member_android
እና
https://www.linkedin.com/posts/ethiopian-investment-holdings_commencing-their-networking-and-collaboration-ugcPost-7188069533868261376-IycV?utm_source=share&utm_medium=member_android
በትምህርት ዘርፉ ውጤታማ ስራ ለመሥራት የተግባባ፣ የጋራ አስተሳሰብ ያለውና የወደፊቱን የተገናዘበ አመራር መስጠት እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለፁ።
--------------------------------------

የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የምክክር መድረክ የትምህርት ሚኒስቴርና የክልል የትምህርት ዘርፉ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።

በምክክር መድረኩ የተገኙት ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት የመምራት እድል እንደተሰጠው አመራር በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ያለውን ውስብስብ ችግር በመረዳት የተቀራረበ አመለካከት በመያዝ አመራር መስጠት ይገባል ብለዋል።

ከዚህ በፊት ትምህርትን እያየን ባለንበት መንገድ መሥራት አንችልም ያሉት ሚኒሰትሩ በረጅም ጊዜ አቅደን ብቁ ተወዳዳሪ እና በስነ-ምግባር የታነፁ ልጆች ለማፍራት የሚያስችል ትምህርት እየሰጠን ነው የሚለውን ማሰብና መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በትምህርት ዘርፍ በርካታ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ የጋራ አስተሳሰብ በአዲስ መልክና ማዕቀፍ መያዝ ይገባል ብለዋል።

አክለውም ከአጭር ጊዜ አስተሳሰብ ወጥተን የሚቀጥለውን ትውልድ በዓለም ተወዳዳሪ፣ ክህሎት ያለው፣ ግብረ ገብነትን የተላበሰ እንዲሆን ለማድረግ የጋራ አስተሳሰብ ይዞ መሄድ እንደሚገባም አሳስበዋል።

አሁን ዓለም ያለችበትን ሁኔታ በመረዳት የተሻለ ብቃትና ክህሎት ያላቸው እንዲሁም በስነ ምግባር የታነፁ ተማሪዎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ መሥራት እንደሚገባ በመድረኩ ተገልጿል።

በመድረኩም የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴን ጨምሮ፣ የህዝብ ተወካዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች፣ የሁሉም ክልልና ሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
ሁሉንም ለማስደሰት እንደሚጥር ሰው ከንቱ የለም!  ሁሉም ሰው በተመሳሳይ ነገር አይደሰትም እኮ ፤ በተለያየ ነገር ለሚደሰቱ ሰዎች ስንል ደግሞ እኛ እንደ ወረቀት መተታጠፍ የለብንም። ሁሉንም ለማስደሰት ስንሞክር ሁሉንም እናሳዝናለን !

🌟ምን እናርግ ታዲያ? ህሊናችን የሚነግረንን አይምሮአችን የሚያዘንን ልባችንን በደስታ የሚቀበለውን ብቻ መርጦ ማድረግ፤ ያኔ ሰዎች ቢደሰቱም ባይደሰቱም ህሊናችን ግን ምን ነካህ እያለ አያስጨንቀንም። ለህሊናው እንደሚታመን ሰው ሰላም የከበበው የለም!

🌐JOIN :
@mayaofficial19