TechVibe – Telegram
TechVibe
741 subscribers
461 photos
34 videos
33 files
208 links
I'm Eyob, a self-taught dev sharing my Tech journey, tips, tools, and real-world projects. Let’s grow together😊

DM for any project ideas @alnova19

Personal site: https://eyobsimachew.vercel.app
My Github: https://github.com/Eyob-smax
Download Telegram
https://youtu.be/j71wDoLfA3Q

🌟በጥያቄችሁ መሰረት እነሆ🌟

- የExitExamAI አጠቃቀም ሙሉ ቪዲዮ ተለቋል!
የመውጫ ፈተናን በAI በመታገዝ በውጤት እናሸብርቅ!

🌟You asked and here it is🌟

- ExitExamAI Full Video Tutorial Released!
- A step by step video guide for you to master ExitExam with tailored AI Models.

Ace your Exit Exam with AI brilliance

Website: ExitExamAI
Telegram: @ExitExamAI
መምህራኑ ላለፉት 2 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም አሉ።

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎጃም ዞን፣ ጎንጂ ቆለላ ወረዳ ፣ ላለፉት 2 ወራት ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው የገለጹ መምህራን የከፋ ችግር ላይ እንደሚገኙ ገለጹ።

መምህራኑ በቁጥር ከ1 ሺሕ በላይ ይሆናሉ።

በወረዳው በሚገኙ 52 የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩት እኚህ መምህራን ፤ ኑሯቸውን የሚገፉት በወርሃዊ ደመወዛቸው ብቻ በመሆኑ ፣ ዩኒቨርሲቲ ለሚማሩ ልጆቻቸው የሚላክ ገንዘብን ጨምሮ ቤተሰቦቻቸውን ለመደገፍ እንደተሳናቸው ገልጸዋል፡፡

የቆንጂ ቆለላ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት ጌታቸው ደገፋው ችግሩ መሆኑን አምነዋል።

በአካባቢው ባለው የጸጥታ ችግር የሒሳብ ሠራተኞች ወደ ቢሮ ገብተው ለመሥራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የተፈጠረ እንደሆነ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት፣ ከመምህራን ማኅበር ጋራ በመነጋገር አዲስ ሠራተኞች ተመድበው ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል። #ቪኦኤ

 
            Share share🙏🙏
ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇
╔═══════════╗
♨️ ♦️ @mayaofficial19  ♨️
♨️ ♦️ @mayaofficial19 ♨️
♨️ ♦️ @mayaofficial19♨️
╚═══════════╝
እንኳን ለ128ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሰን!

የአድዋ ድል የጥቁር ሕዝብ ነጻነት የታወጀበት ኢትዮጵያውያን ቅኝ ሊገዛ የወረራቸውን የጣሊያን ጦር ድል አድርገው አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የከፈቱበት ታሪካዊና የአሸናፊነት ተምሳሌት ነው።

ጀግኖች አባቶቻቸን በዘርና ቋንቋ ሳይከፋፈሉ በአንድነት ድልን ተቀዳጅተው የጥቁር ህዝቦች ኩራት የሆነውን የድል ታሪክ፣ በደማቅ ጽፈው አልፈዋል።

የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር!

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://news.1rj.ru/str/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
በመውጫ ፈተና ኩረጃና ሌሎች የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ ተሰረዘ
....................................................
መጋቢት 2/2016ዓ.ም (ትሚ) በመውጫ ፈተና ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት፣ መኮረጅና የተለያዩ የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም ለሁሉም የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙት 114 (አንድ መቶ አስራ አራት) ተፈታኞች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ መሠረዙንና የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች በቀጣይ የሚገለጽ መሆኑ በደብዳቤው ተመልክቷል ።

ከየካቲት 6-11/2016 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት በተሰጠው ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተና 119, 145 ተፈታኞች ተፈትነዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ጥራትን ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ሪፎርሞች አንዱ የሆነው መውጫ ፈተና ተመራቂዎች በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው ተገቢውን እውቀትና ክህሎት መቅሰማቸውንና ብቁ መሆናቸውን ዒላማ ያደረገ በመሆኑ ፈተናው በጥብቅ ዲስፕሊን የሚመራ ነው።

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://news.1rj.ru/str/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም እየተካሄደ ነው::
-------------------------//--------------

መጋቢት 7/2016 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም “ከፍተኛ ትምህርት ከፍ ላለ ተጽዕኖ/Higher Education for Higher Impacts” በሚል መሪ ቃል በጅማ ዩኒቨርሲቲ በዘርፉ የሚተገበሩ አዳዲስ ሪፎርሞች ላይ ትኩረት ያደረገ ውይይት በማካሄድ ላይ ነው::

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሸኔ በውይይት መድረኩ ተገኝተው ካለፈው ተሞክሮ ስለተገኙ ቁም ነገሮችና ዘርፉ ያለበትን ቁመና አስመልክቶ ንግግር አድርገዋል::

ሚኒስትር ዴኤታው ባስተላለፉት መልዕክት የከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ለሃገር ከፍ ያለ አበርክቶ እንዳይኖረው አንቀው ከያዙት ማነቆዎች ሊላቀቅ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለፎረሙ ተሳታፊዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማቂ ነጻነት ፍኖተካርታ፣የዩኒቨርስቲ ትኩረት መስክና ተልዕኮ ልየታ፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና፣ የምርምር
ተቋማት እና የኢንዱስትሪ ትስስር አዋጅ 1298/2015 ጨምሮ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፉ ላይ የተከናወኑና በመከናወን ላይ ስላሉ አዳዲስ ትግበራዎችና የለውጥ አጀንዳዎች ዙሪያ የውይይት አጀንዳዎች ቀርበዋል::

በፎረሙ ላይ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንቶችና
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ ሃላፊዎች፣የትምህርት ሚኒስቴርና የጅማ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ሙሉ ዜናው👇

https://www.facebook.com/share/p/9C4VF3Qk5MwsoM85/?mibextid=Nif5oz
የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም ተጠናቀቀ

............................................
መጋቢት 8/2016 ዓ.ም (ትሚ) መሪ ቃሉን “ከፍተኛ ትምህርት ከፍ ላለ ተጽዕኖ” (Higher Education for Higher Impacts) ያረገው የከፍተኛ ትምህርት ፕሬዝዳንቶች ፎረም ትናንት ተጠናቀቀ፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በፎረሙ ማጠቃለያ ከፍተኛ ትምህርት ላይ እየተተገበሩ ያሉት ቁልፍ የለውጥ ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የዘርፉ ሃላፊዎች በትኩረት በመሰራት የድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባቸውና የሁሉንም ባለድርሻዎች የላቀ ተሳትፎ እንደሚጠይቅ አሳስበዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ጨምሮ ከመላው የሃገራችን ዩኒቨርስቲዎች የተውጣጡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚደንቶችና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች አንዲሁም ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ፎረም በተጀመሩ የለውጥ መርሃ-ግብሮች አተገባበር፣የለውጥ ስኬቶችና ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ጥልቅ ውይይት ሲያደርግ የቆየ ሲሆን የቀጣይ ስራ አቅጣጫዎች ላይ በመምከር ተጠናቋል፡፡

በዕለቱ በጅማ ዩኒቨርስቲ (@ Jimma University ) የተዘጋጀ አውደርዕይ፣ የዲጂታል ትምህርት ስቱዲዮና Ict መረጃ ማዕከል እንዲሁም ሌሎች ካምፓሶች በፎረሙ ተሳታፊዎች ተኀብኝተዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://news.1rj.ru/str/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ!
43ኛው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሄደ፡፡
===========================
መጋቢት 16/2016 ዓ.ም (ትሚ) 43ኛው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ህብረት መደበኛ ጉባኤ “ጠንካራ የተማሪዎች አደረጃጀት ለተሻለች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ አስተናጋጅነት ተካሂዷል፡፡

ሙሉ ዜናው👇
https://www.facebook.com/share/p/4CyUSuffFwVaKnzr/?mibextid=Nif5oz
በድጋፍ የተገኙት የህክምና ቁሳቁሶች የህክምና ዘርፉን የመማር ማስተማር ተግባር ለማሻሻል ለሚደረገው ስራ የላቀ አስተዋፆ እንዳላቸው ተገለፀ፡፡
======================
ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የባዮሜዲካል ቴክኒሻኖችንና መሐንዲሶችን ስልጠና ለማሳደግ እና በሆስፒታሎች ውስጥ ያለውን የህክምና አገልግሎት ለማሻሻል በጀርመን የፋይናንስ ትብብር፣ በጀርመን ልማት ባንክ KFW የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡ ሙሉ ዜናውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፣
https://www.facebook.com/share/p/4azpZTEjtnR4P3VZ/?mibextid=oFDknk
ለጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ውጤታማነት አጋር አካላት የድርሻቸውን እንዲውጡ ጥሪ ቀረበ።

ዲቪቪ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ በጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት የ30 ዓመታት ጉዞን የተመለከተ ኮንፈረንስ ተካሂዷል።
-----------------------//--------------------------
በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር አጠቃላይ ትምህርት ልማትር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሽቴ ሀገራችን መደበኛ ትምህርት ያላገኙ ዜጎችን የመማር መብት ለማረጋገጥና የተማሩ ዜጎችን ቁጥር ለማሳደግ ባለፉት ዓመታት የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ፕሮግራምን በመዘርጋት ውጤታማ ስራ ሰርታለች ብለዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0FxgzBbLxu3iLXRGFnDooGUNoaNN11JeBZGm7pYT5LLr1HaAfkpxQSKyCRssbnh2Ml&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz