ጊዜና ወቅት ያልገደበው የበጎ አገልግሎት
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ድህነት ጥላውን ላጠላባቸው ነፍሶች ቤት ከመጠለያም በላይ ነው። ቤት ገመናን ሸፋኝ፣ የዘመናት እንባን አባሽ፣ ሀዘንን መርሻ፣ ዞሮ መግቢያ ነው። የክረምቱን መግባት ተከትሎ በበጎ ፈቃድ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል የአረጋውያንን እና የአቅመ ደካሞችን ቤቶች ማደስ አንዱ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሃኒት፣ የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣንም በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የብዙዎችን ቤት ጎብኝቷል።ኢኮኖሚያዊ አቅማቸው ዝቅ ብሎ እጃቸው ላጠረባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ቤታቸውን አድሶ ለባለቤቶቹ አስተላልፏል።
ወይዘሮ አብነት ቢሻው ይባላሉ፤ የመኖሪያ ጎጇቸውን በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለምዶ አዲሱ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ቀልሰዋል። ቤታቸው ወደ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85575
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ድህነት ጥላውን ላጠላባቸው ነፍሶች ቤት ከመጠለያም በላይ ነው። ቤት ገመናን ሸፋኝ፣ የዘመናት እንባን አባሽ፣ ሀዘንን መርሻ፣ ዞሮ መግቢያ ነው። የክረምቱን መግባት ተከትሎ በበጎ ፈቃድ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል የአረጋውያንን እና የአቅመ ደካሞችን ቤቶች ማደስ አንዱ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሃኒት፣ የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣንም በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የብዙዎችን ቤት ጎብኝቷል።ኢኮኖሚያዊ አቅማቸው ዝቅ ብሎ እጃቸው ላጠረባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ቤታቸውን አድሶ ለባለቤቶቹ አስተላልፏል።
ወይዘሮ አብነት ቢሻው ይባላሉ፤ የመኖሪያ ጎጇቸውን በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በተለምዶ አዲሱ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ቀልሰዋል። ቤታቸው ወደ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85575
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽንን ለማቋቋም በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሲካሄዱ የቆዩት ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ የመጨረሻ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በተደራጀ ኃይል ውስጥ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ፣ በአገሪቱ የልማት፣ የሰላም እና የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት እንዲሳተፉ ለማስቻል ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
2. ምክር ቤቱ በመቀጠል የተወያየው በመከላከያ ሠራዊት ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ መከላከያ ሠራዊቱ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆኖ የአገርን ሉአላዊነትና የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ተልዕኮውን በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲወጣ የሚያስችል የሪፎርም ስራ ውስጥ እንደሚገኝ፣ በዚህም አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህንን ሪፎርም የበለጠ ለማጎልበት እና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ከመከላከያ ሠራዊቱ ወቅታዊ እና የወደፊት ግዳጆች ጋር የሚጣጣም የህግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ በሥራ ላይ ያለውን አዋጅ የሚተካ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ይጸድቅ ዘንድ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ የአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እንዲፋጠን ችግር ፈቺ የአቅም ግንባታ፣ የፋይናንስ፣ የማምረቻ መሳሪያ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምክር አገልግሎት፣ የማምረቻ ቦታና መሰረተ-ልማት፣ የግብዓትና የገበያ ትስስር ድጋፎች በመስጠት ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን የማስፋፋትና የማሸጋገር ተልዕኮ ያለው ተቋም በማስፈለጉ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማትን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽንን ለማቋቋም በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሲካሄዱ የቆዩት ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ የመጨረሻ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በተደራጀ ኃይል ውስጥ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ፣ በአገሪቱ የልማት፣ የሰላም እና የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት እንዲሳተፉ ለማስቻል ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
2. ምክር ቤቱ በመቀጠል የተወያየው በመከላከያ ሠራዊት ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ መከላከያ ሠራዊቱ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆኖ የአገርን ሉአላዊነትና የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ተልዕኮውን በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲወጣ የሚያስችል የሪፎርም ስራ ውስጥ እንደሚገኝ፣ በዚህም አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህንን ሪፎርም የበለጠ ለማጎልበት እና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ከመከላከያ ሠራዊቱ ወቅታዊ እና የወደፊት ግዳጆች ጋር የሚጣጣም የህግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ በሥራ ላይ ያለውን አዋጅ የሚተካ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ይጸድቅ ዘንድ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ የአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እንዲፋጠን ችግር ፈቺ የአቅም ግንባታ፣ የፋይናንስ፣ የማምረቻ መሳሪያ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምክር አገልግሎት፣ የማምረቻ ቦታና መሰረተ-ልማት፣ የግብዓትና የገበያ ትስስር ድጋፎች በመስጠት ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን የማስፋፋትና የማሸጋገር ተልዕኮ ያለው ተቋም በማስፈለጉ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማትን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡