የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ15ኛ መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽንን ለማቋቋም በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሲካሄዱ የቆዩት ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ የመጨረሻ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በተደራጀ ኃይል ውስጥ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ፣ በአገሪቱ የልማት፣ የሰላም እና የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት እንዲሳተፉ ለማስቻል ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
2. ምክር ቤቱ በመቀጠል የተወያየው በመከላከያ ሠራዊት ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ መከላከያ ሠራዊቱ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆኖ የአገርን ሉአላዊነትና የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ተልዕኮውን በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲወጣ የሚያስችል የሪፎርም ስራ ውስጥ እንደሚገኝ፣ በዚህም አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህንን ሪፎርም የበለጠ ለማጎልበት እና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ከመከላከያ ሠራዊቱ ወቅታዊ እና የወደፊት ግዳጆች ጋር የሚጣጣም የህግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ በሥራ ላይ ያለውን አዋጅ የሚተካ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ይጸድቅ ዘንድ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ የአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እንዲፋጠን ችግር ፈቺ የአቅም ግንባታ፣ የፋይናንስ፣ የማምረቻ መሳሪያ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምክር አገልግሎት፣ የማምረቻ ቦታና መሰረተ-ልማት፣ የግብዓትና የገበያ ትስስር ድጋፎች በመስጠት ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን የማስፋፋትና የማሸጋገር ተልዕኮ ያለው ተቋም በማስፈለጉ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማትን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽንን ለማቋቋም በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች ሲካሄዱ የቆዩት ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ የመጨረሻ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣ በተደራጀ ኃይል ውስጥ ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኃይሎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደማህበረሰቡ በዘላቂነት እንዲቀላቀሉና ሰላማዊ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ለማድረግ፣ በአገሪቱ የልማት፣ የሰላም እና የዲሞክራሲ ግንባታ ሂደት እንዲሳተፉ ለማስቻል ብሔራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
2. ምክር ቤቱ በመቀጠል የተወያየው በመከላከያ ሠራዊት ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ መከላከያ ሠራዊቱ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆኖ የአገርን ሉአላዊነትና የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ተልዕኮውን በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲወጣ የሚያስችል የሪፎርም ስራ ውስጥ እንደሚገኝ፣ በዚህም አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህንን ሪፎርም የበለጠ ለማጎልበት እና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ከመከላከያ ሠራዊቱ ወቅታዊ እና የወደፊት ግዳጆች ጋር የሚጣጣም የህግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ በሥራ ላይ ያለውን አዋጅ የሚተካ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ይጸድቅ ዘንድ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምጽ እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
3. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ የአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እንዲፋጠን ችግር ፈቺ የአቅም ግንባታ፣ የፋይናንስ፣ የማምረቻ መሳሪያ፣ የቴክኖሎጂ፣ የምክር አገልግሎት፣ የማምረቻ ቦታና መሰረተ-ልማት፣ የግብዓትና የገበያ ትስስር ድጋፎች በመስጠት ማኑፋክቸሪንግ ኢንተርፕራይዞችን የማስፋፋትና የማሸጋገር ተልዕኮ ያለው ተቋም በማስፈለጉ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማትን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር ለመወሰን ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡
"ኢትዮጵያ በትዕግስት እና በጥንቃቄ የምታደርገው ውሳኔ ለሁሉም ልጆቿ ጥቅም ስትል ነው" - ዶክተር ለገሰ ቱሉ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በትዕግስት እና በጥንቃቄ የምታደርገው ውሳኔ ለሁሉም ልጆቿ ጥቅም ስትል መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ተናገሩ።
ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ "ከታሪክና ተግባራዊ ልምምድ አንጻር ነገሮችን ከተመለከትን ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላም የሚደረግ ሽግግር በሰጥቶ መቀበል መርህ፣ በትዕግስትና በብልሃት የሚመሩ መሆኑን ያመለክተናል" ብለዋል።
ለዘላቂ ሰላም ጥቅሞችን ማጣጣም የግድ እንደሆነም ነው ያመለከቱት።
ይህ ጉዳይ ውስጣዊ ከሆነ ደግሞ የተለየ ትኩረት እና ማስተዋልን እንደሚጠይቅ ዶክተር ለገሰ ገልፀዋል።
"ኢትዮጵያ በትዕግስት እና በጥንቃቄ የምታደርገው ውሳኔ ለሁሉም ልጆቿ ጥቅም ስትል ነው" ብለዋል።
"ጉዳቶቻችንና ሃዘናችንን የምንረሳው ይቅር ስንባባል ነው" ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ለዚህ መሳካት ልጆቿም ይተባበራሉ ብላ ኢትዮጵያ በእኛ ላይ እምነት ጥላለች ያሉት ሚኒስትሩ፥ "ከዚህ አኳያ የጀመርነው መንገድ መልካም ይመስላል፤ ልጆቿ ከተባበሩ ይሳካል" ብለዋል።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በትዕግስት እና በጥንቃቄ የምታደርገው ውሳኔ ለሁሉም ልጆቿ ጥቅም ስትል መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ተናገሩ።
ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ "ከታሪክና ተግባራዊ ልምምድ አንጻር ነገሮችን ከተመለከትን ከግጭት ወደ ዘላቂ ሰላም የሚደረግ ሽግግር በሰጥቶ መቀበል መርህ፣ በትዕግስትና በብልሃት የሚመሩ መሆኑን ያመለክተናል" ብለዋል።
ለዘላቂ ሰላም ጥቅሞችን ማጣጣም የግድ እንደሆነም ነው ያመለከቱት።
ይህ ጉዳይ ውስጣዊ ከሆነ ደግሞ የተለየ ትኩረት እና ማስተዋልን እንደሚጠይቅ ዶክተር ለገሰ ገልፀዋል።
"ኢትዮጵያ በትዕግስት እና በጥንቃቄ የምታደርገው ውሳኔ ለሁሉም ልጆቿ ጥቅም ስትል ነው" ብለዋል።
"ጉዳቶቻችንና ሃዘናችንን የምንረሳው ይቅር ስንባባል ነው" ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
ለዚህ መሳካት ልጆቿም ይተባበራሉ ብላ ኢትዮጵያ በእኛ ላይ እምነት ጥላለች ያሉት ሚኒስትሩ፥ "ከዚህ አኳያ የጀመርነው መንገድ መልካም ይመስላል፤ ልጆቿ ከተባበሩ ይሳካል" ብለዋል።
የሰላም ስምምነቱ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲሻሻል ያደርጋል
******************
(ኢ ፕ ድ)
“በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል የተደረገው የሰላም ስምምነት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲሻሻል ያደርጋል” ሲሉ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር አቶ እንዳለ ንጉሴ አስታወቁ።
መምህር እንዳለ ንጉሴ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል የተደረገው ስምምነት ለኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሲደረግባት የነበረውን ዲፕሎማሲያዊ ጫና በአሸናፊነት የተወጣች በመሆኑ ምዕራባውያን ያላቸውን ግንኙነት እንዲፈትሹ ይገደዳሉ ነው ያሉት።
እንደ አቶ እንዳለ ገለፃ፤ምዕራባውያን የጥቅምና የአመለካከት ጉዳይ በመኖሩ ከዚህ በኋላ ባለው ሂደት አርፈው ይቀመጣሉ ማለት አይደለም፤ ነገር ግን በቀጥታ ጫና የሚያደርጉበት መንገድ ይቀንሳል፤ኢትዮጵያን ለማፍረስ ይጠቀሙበት የነበረው ግጭት ወደ ስምምነት በመምጣቱ የጸጥታው ምክር ቤትና የአውሮፓ ኅብረት በየጊዜው ስብሰባ ማድረግ አይችሉም። ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሚዲያዎቻቸውን ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85655
ትዊተር 👇
https://twitter.com/PressEthio
******************
(ኢ ፕ ድ)
“በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል የተደረገው የሰላም ስምምነት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲሻሻል ያደርጋል” ሲሉ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር አቶ እንዳለ ንጉሴ አስታወቁ።
መምህር እንዳለ ንጉሴ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል የተደረገው ስምምነት ለኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሲደረግባት የነበረውን ዲፕሎማሲያዊ ጫና በአሸናፊነት የተወጣች በመሆኑ ምዕራባውያን ያላቸውን ግንኙነት እንዲፈትሹ ይገደዳሉ ነው ያሉት።
እንደ አቶ እንዳለ ገለፃ፤ምዕራባውያን የጥቅምና የአመለካከት ጉዳይ በመኖሩ ከዚህ በኋላ ባለው ሂደት አርፈው ይቀመጣሉ ማለት አይደለም፤ ነገር ግን በቀጥታ ጫና የሚያደርጉበት መንገድ ይቀንሳል፤ኢትዮጵያን ለማፍረስ ይጠቀሙበት የነበረው ግጭት ወደ ስምምነት በመምጣቱ የጸጥታው ምክር ቤትና የአውሮፓ ኅብረት በየጊዜው ስብሰባ ማድረግ አይችሉም። ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሚዲያዎቻቸውን ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=85655
ትዊተር 👇
https://twitter.com/PressEthio