በኢትዮ- ኬኒያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዛሬ በይፋ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ተጀምሯል
********
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ ዛሬ በይፋ የኤላክትሪክ ሽያጭ ጀምሯል፡፡
በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ ከጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲከናወን ቆይቷል፡፡
ዛሬ በይፋ ኃይል ማስተላለፍ የጀመረው የኢትዮ - ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር በዓመት እስከ አንድ መቶ ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ማስገባት አቅም ያለው ሲሆን ከኬንያ አሌፎ ከታንዛኒያ እስከ ደቡብ አፍሪካ ላሉት ሀገራት እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት ኤላክትክ የማስተላለፍ አቅም አለው፡፡
የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት ለአማካሪ ድርጅቱ፣ ለካሳ ክፍያና የተሰረቁ መሰረተ ሌማቶችን ለመተካት የወጣውን ወጪ ጨምሮ ወደ አምስት መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶሊር ወጪ ተደርጎበታል፡፡
ከዚህ ውስጥ 214 ነጥብ 5 ሚሉዮን ዶላሩ ለኮንቨርተር ስቴሽኑና ለግራውንድ ኤላክትሮድ መስመር የግንባታ ሥራ እንዲሁም 120 ሚሉዮን ዶላሩ ደግሞ ለማስተላለፊያ መስመሩ የዋለ ነው፡፡
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ "CET" በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያውና የግራውንድ ኤላክትሮድ መስመሩ ደግሞ ሲመንስ በተሰኘ ኩባንያ ተከናውኗል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል የተዘረጋው የማስተላለፊያ መስመር እና የፕሮቴክሽንና የዳታ ኮሙዩኒኬሽን መስመር (ኦፕቲካሌ ግራውንድ ፋይበር) 440 ኪል ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን 994 የከፍተኛ ኃይሌ ተሸካሚ የብረት ታወሮች አሉት።
ኢትዮጵያ የምታስተላልፈው ኃይል ያልተቆራረጠና አስተማማኝ እንዲሆን የሚያግዙ ተግባራትን ያጠናቀቀች ሲሆን በኬንያ በኩል ተመሳሳይ ሥራዎች ተሰርተው በቅርቡ ወደተግባር እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ ከደቡብ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወላይታ፣ ጋሞ እና ኮንሶ ዞን እንዲሁም ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክሌሊዊ መንግስት የቦረና ዞን አቋርጦ ነው ወደ ኬንያ ኃይል የሚያስተላልፈው።
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ከጅቡቲ ጋር የኃይሌ ሽያጭ እያካሔደች ሲሆን ከሶማሌላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤላክትሪክ ኃይሌ ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርማለች።
ባለፈው ዓመት ለሱዳን እና ለጅቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገው የኤላክትሪክ ኃይሌ 95 ነጥብ 4 ሚሉየን የአሜሪካን ዶሊር ገቢ ተገኝቷል፡፡
(ፎቶ ፋይል)
********
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ ዛሬ በይፋ የኤላክትሪክ ሽያጭ ጀምሯል፡፡
በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ ከጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲከናወን ቆይቷል፡፡
ዛሬ በይፋ ኃይል ማስተላለፍ የጀመረው የኢትዮ - ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር በዓመት እስከ አንድ መቶ ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ማስገባት አቅም ያለው ሲሆን ከኬንያ አሌፎ ከታንዛኒያ እስከ ደቡብ አፍሪካ ላሉት ሀገራት እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት ኤላክትክ የማስተላለፍ አቅም አለው፡፡
የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት ለአማካሪ ድርጅቱ፣ ለካሳ ክፍያና የተሰረቁ መሰረተ ሌማቶችን ለመተካት የወጣውን ወጪ ጨምሮ ወደ አምስት መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶሊር ወጪ ተደርጎበታል፡፡
ከዚህ ውስጥ 214 ነጥብ 5 ሚሉዮን ዶላሩ ለኮንቨርተር ስቴሽኑና ለግራውንድ ኤላክትሮድ መስመር የግንባታ ሥራ እንዲሁም 120 ሚሉዮን ዶላሩ ደግሞ ለማስተላለፊያ መስመሩ የዋለ ነው፡፡
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ "CET" በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያውና የግራውንድ ኤላክትሮድ መስመሩ ደግሞ ሲመንስ በተሰኘ ኩባንያ ተከናውኗል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል የተዘረጋው የማስተላለፊያ መስመር እና የፕሮቴክሽንና የዳታ ኮሙዩኒኬሽን መስመር (ኦፕቲካሌ ግራውንድ ፋይበር) 440 ኪል ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን 994 የከፍተኛ ኃይሌ ተሸካሚ የብረት ታወሮች አሉት።
ኢትዮጵያ የምታስተላልፈው ኃይል ያልተቆራረጠና አስተማማኝ እንዲሆን የሚያግዙ ተግባራትን ያጠናቀቀች ሲሆን በኬንያ በኩል ተመሳሳይ ሥራዎች ተሰርተው በቅርቡ ወደተግባር እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ ከደቡብ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወላይታ፣ ጋሞ እና ኮንሶ ዞን እንዲሁም ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክሌሊዊ መንግስት የቦረና ዞን አቋርጦ ነው ወደ ኬንያ ኃይል የሚያስተላልፈው።
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ከጅቡቲ ጋር የኃይሌ ሽያጭ እያካሔደች ሲሆን ከሶማሌላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤላክትሪክ ኃይሌ ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርማለች።
ባለፈው ዓመት ለሱዳን እና ለጅቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገው የኤላክትሪክ ኃይሌ 95 ነጥብ 4 ሚሉየን የአሜሪካን ዶሊር ገቢ ተገኝቷል፡፡
(ፎቶ ፋይል)
አምስተኛው አዲስ ቻምበር አለም አቀፍ የማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ ንግድ ትርኢት ተከፈተ
******
(ኢ ፕ ድ)
11 አጋራት የሚሳተፉበት አምስተኛው አዲስ ቻምበር አለም አቀፍ የማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ ንግድ ትርኢት ዛሬ በኤግዚቢሽን ማእከል ተከፍቷል።
የንግድ ትርኢቱን የከፈቱት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የአገርን ምርትና ገበያ ለወጪው አለም ለማስተዋወቅ እንዲሁም የወጪውን ለማወቅ ትርኢቱ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል።
በዘርፉ በአገራት መከካል ልምድ ለመለዋወጥና የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደሚረዳም ጠቅሰዋል።
ንግድ ትርኢት "manufacturing for enhanced employment" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ ቴክኖሎጂ ተኮር የማኑፋክቸሪንግ ግበአቶች ከአምራች ኩባንያዎች ለሸማቹ ማህበረሰብ እንደሚቀርብ ተጠቅሷል።
በንግድ ትርኢቱ ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ዩጋንዳ፣ ህንድ፣ ጆርዳን፣ ፓኪስታን ሳኡዲ አርቢያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስና ቻይና ተሳታፊ ናቸው።
በአዲሱ ገረመው
******
(ኢ ፕ ድ)
11 አጋራት የሚሳተፉበት አምስተኛው አዲስ ቻምበር አለም አቀፍ የማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ ንግድ ትርኢት ዛሬ በኤግዚቢሽን ማእከል ተከፍቷል።
የንግድ ትርኢቱን የከፈቱት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የአገርን ምርትና ገበያ ለወጪው አለም ለማስተዋወቅ እንዲሁም የወጪውን ለማወቅ ትርኢቱ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል።
በዘርፉ በአገራት መከካል ልምድ ለመለዋወጥና የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደሚረዳም ጠቅሰዋል።
ንግድ ትርኢት "manufacturing for enhanced employment" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ ቴክኖሎጂ ተኮር የማኑፋክቸሪንግ ግበአቶች ከአምራች ኩባንያዎች ለሸማቹ ማህበረሰብ እንደሚቀርብ ተጠቅሷል።
በንግድ ትርኢቱ ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ዩጋንዳ፣ ህንድ፣ ጆርዳን፣ ፓኪስታን ሳኡዲ አርቢያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስና ቻይና ተሳታፊ ናቸው።
በአዲሱ ገረመው
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ለአፋር ክልል የ285 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
******
(ኢ ፕ ድ)
በሰሜኑ ጦርነት የተነሳ ለችግር የተጋለጡና በአፋር የሚገኙ 24 ሺህ 200 ተፈናቃዮችን ለመርዳት 170 ሚሊዮን ብር መመደቡን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በተጨማሪ በአፋር ክልል በከተሞች ለሚተገበረው ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት 115 ሚሊዮን ብር ተመድቧል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ድጋፉ በአጠቃላይ 285 ሚሊዮን ብር ነው፤ ገንዘቡ ቀጥታ ለተጎጂዎች በአካውንት የሚደርስ ነው ብለዋል።
ድጋፉን የተቀበሉት የአፋር ክልል ፕሬዚዳንት ሃጂ አወል አርባ ሚኒስቴሩ ከተፈናቃዮች ድጋፍ ባለፈ በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ገንዘብ መመደቡን አድንቀው ምስጋና አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
******
(ኢ ፕ ድ)
በሰሜኑ ጦርነት የተነሳ ለችግር የተጋለጡና በአፋር የሚገኙ 24 ሺህ 200 ተፈናቃዮችን ለመርዳት 170 ሚሊዮን ብር መመደቡን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በተጨማሪ በአፋር ክልል በከተሞች ለሚተገበረው ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት 115 ሚሊዮን ብር ተመድቧል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ድጋፉ በአጠቃላይ 285 ሚሊዮን ብር ነው፤ ገንዘቡ ቀጥታ ለተጎጂዎች በአካውንት የሚደርስ ነው ብለዋል።
ድጋፉን የተቀበሉት የአፋር ክልል ፕሬዚዳንት ሃጂ አወል አርባ ሚኒስቴሩ ከተፈናቃዮች ድጋፍ ባለፈ በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ገንዘብ መመደቡን አድንቀው ምስጋና አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም