በመጀመሪያው ሩብ አመቱ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች መቋቋማቸውን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አስታወቀ
*********************
(ኢ ፕ ድ )
በተያዘው የበጀት አመት የመጀመሪያው ሩብ አመቱ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች መቋቋማቸውን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት ከክልል ኢንተርፕራይዝ ቢሮዎች ጋር የሩብ አመቱን አፈጻጸም በአዳማ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኢንተርፔራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ የሩብ አመቱን የእቅድ አፈጻጸምን ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት
በበጀት አመቱ አራት ሽህ 62 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ለማቋቋም እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው።
እንደ አቶ አብዱልፈታ ገለጻ፤ በሩብ አመቱ 551 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ለማቋቋም ታልሞ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ማቋቋም ተችሏል።
በሩብ አመቱ 258 ሚሊዮን ብር የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ለአምራች ኢንተርፕራይዞች መሰራጨቱንም አቶ አብዱልፈታ የሱፍ ተናግረዋል።
በሙሐመድ ሁሴን (አዳማ)
*********************
(ኢ ፕ ድ )
በተያዘው የበጀት አመት የመጀመሪያው ሩብ አመቱ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች መቋቋማቸውን የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት ከክልል ኢንተርፕራይዝ ቢሮዎች ጋር የሩብ አመቱን አፈጻጸም በአዳማ ከተማ እየገመገመ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኢንተርፔራይዝ ልማት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አብዱልፈታ የሱፍ የሩብ አመቱን የእቅድ አፈጻጸምን ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት
በበጀት አመቱ አራት ሽህ 62 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ለማቋቋም እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው።
እንደ አቶ አብዱልፈታ ገለጻ፤ በሩብ አመቱ 551 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ለማቋቋም ታልሞ 419 አዳዲስ ኢንተርፕራይዞች ማቋቋም ተችሏል።
በሩብ አመቱ 258 ሚሊዮን ብር የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ለአምራች ኢንተርፕራይዞች መሰራጨቱንም አቶ አብዱልፈታ የሱፍ ተናግረዋል።
በሙሐመድ ሁሴን (አዳማ)
ልማት ባንክ የሦስተኛ ደረጃ ሕክምና ለሚሰጡ ተቋማት ብድር ሊሰጥ ነው
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁና በውጭ ሀገራት የሚሰጡ የሦስተኛ ደረጃ የሕክምና አገልግሎቶችን በሀገር ውስጥ መስጠት ለሚችሉ የጤና ተቋማት ብድር መስጠት ሊጀምር መሆኑን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው እንደገለጹት፤ ባንኩ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁና በውጭ የሚደረጉ የሕክምና አገልግሎቶች በሀገር ውስጥ እንዲጀመሩ ለማስቻል የሦስተኛ ደረጃ ሕክምና የሚሰጡ ተቋማትን ለመደገፍ ተዘጋጅቷል። በዘርፉ ድጋፍ ለማግኘት ጥያቄ ያቀረቡ የጤና ተቋማት መኖራቸውን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ የብድር ፕሮጀክቱን በቀጣዮቹ አራት ወራት ለማፅደቅና ወደ ሥራ ለመግባት መታቀዱን ተናግረዋል።
እንደ ዶክተር ዮሐንስ ገለጻ፤ የጤናው ዘርፍ የፋይናንስ ድጋፍ ያስፈልገዋል። ለዚህ ደግሞ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ የሚገኘው የልማት ባንክ የፋይናንስ አጋር ሆኖ ለመቅረብ...
https://www.press.et/?p=85938
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁና በውጭ ሀገራት የሚሰጡ የሦስተኛ ደረጃ የሕክምና አገልግሎቶችን በሀገር ውስጥ መስጠት ለሚችሉ የጤና ተቋማት ብድር መስጠት ሊጀምር መሆኑን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው እንደገለጹት፤ ባንኩ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁና በውጭ የሚደረጉ የሕክምና አገልግሎቶች በሀገር ውስጥ እንዲጀመሩ ለማስቻል የሦስተኛ ደረጃ ሕክምና የሚሰጡ ተቋማትን ለመደገፍ ተዘጋጅቷል። በዘርፉ ድጋፍ ለማግኘት ጥያቄ ያቀረቡ የጤና ተቋማት መኖራቸውን ያነሱት ፕሬዚዳንቱ፤ የብድር ፕሮጀክቱን በቀጣዮቹ አራት ወራት ለማፅደቅና ወደ ሥራ ለመግባት መታቀዱን ተናግረዋል።
እንደ ዶክተር ዮሐንስ ገለጻ፤ የጤናው ዘርፍ የፋይናንስ ድጋፍ ያስፈልገዋል። ለዚህ ደግሞ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ የሚገኘው የልማት ባንክ የፋይናንስ አጋር ሆኖ ለመቅረብ...
https://www.press.et/?p=85938
ከአንድ ማዕከል የኤሌክትሪክ አገልግሎትን መከታተል የሚያስችል ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ሊደረግ ነው
******
(ኢ.ፕ.ድ)
ከአንድ ማዕከል በመሆን የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለመከታተል የሚያስችል የስካዳ አውቶሜሽን አገልግሎት ተግባራዊ እንደሚያደርግ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። ተቋሙ ከመሠረተ ልማት ግንባታና ጥገና ጎን ለጎን የኤሌክትሪክ አገልግሎቱ ፈጣንና ተደራሽ እንዲሆን እየሠራ መሆኑን አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ገበየሁ ሊካሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በመብራት አገልግሎት ላይ የሚታዩ የጥራት ችግሮች ተለይተው ሥራዎች እየተሠሩ ነው።
ሥራዎቹ በአጠቃላይ በ2017 ዓ.ም ሲጠናቀቁ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፈጣን፣ ተደራሽ እና እንከን የለሽ ይሆናል ብለዋል።
የመብራት አገልግሎት ጥራት እንዳይኖር ከሚያደርጉት ችግሮች አንዱ የመብራት መቆራረጥ እና ለረጅም ጊዜ ጠፍቶ መቆየት መሆኑን ያነሱት ዋና ሥራ....
https://www.press.et/?p=85937
******
(ኢ.ፕ.ድ)
ከአንድ ማዕከል በመሆን የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለመከታተል የሚያስችል የስካዳ አውቶሜሽን አገልግሎት ተግባራዊ እንደሚያደርግ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ። ተቋሙ ከመሠረተ ልማት ግንባታና ጥገና ጎን ለጎን የኤሌክትሪክ አገልግሎቱ ፈጣንና ተደራሽ እንዲሆን እየሠራ መሆኑን አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ገበየሁ ሊካሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በመብራት አገልግሎት ላይ የሚታዩ የጥራት ችግሮች ተለይተው ሥራዎች እየተሠሩ ነው።
ሥራዎቹ በአጠቃላይ በ2017 ዓ.ም ሲጠናቀቁ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኤሌክትሪክ አገልግሎት ፈጣን፣ ተደራሽ እና እንከን የለሽ ይሆናል ብለዋል።
የመብራት አገልግሎት ጥራት እንዳይኖር ከሚያደርጉት ችግሮች አንዱ የመብራት መቆራረጥ እና ለረጅም ጊዜ ጠፍቶ መቆየት መሆኑን ያነሱት ዋና ሥራ....
https://www.press.et/?p=85937
በኢትዮ- ኬኒያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዛሬ በይፋ የኤሌክትሪክ ሽያጭ ተጀምሯል
********
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ ዛሬ በይፋ የኤላክትሪክ ሽያጭ ጀምሯል፡፡
በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ ከጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲከናወን ቆይቷል፡፡
ዛሬ በይፋ ኃይል ማስተላለፍ የጀመረው የኢትዮ - ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር በዓመት እስከ አንድ መቶ ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ማስገባት አቅም ያለው ሲሆን ከኬንያ አሌፎ ከታንዛኒያ እስከ ደቡብ አፍሪካ ላሉት ሀገራት እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት ኤላክትክ የማስተላለፍ አቅም አለው፡፡
የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት ለአማካሪ ድርጅቱ፣ ለካሳ ክፍያና የተሰረቁ መሰረተ ሌማቶችን ለመተካት የወጣውን ወጪ ጨምሮ ወደ አምስት መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶሊር ወጪ ተደርጎበታል፡፡
ከዚህ ውስጥ 214 ነጥብ 5 ሚሉዮን ዶላሩ ለኮንቨርተር ስቴሽኑና ለግራውንድ ኤላክትሮድ መስመር የግንባታ ሥራ እንዲሁም 120 ሚሉዮን ዶላሩ ደግሞ ለማስተላለፊያ መስመሩ የዋለ ነው፡፡
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ "CET" በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያውና የግራውንድ ኤላክትሮድ መስመሩ ደግሞ ሲመንስ በተሰኘ ኩባንያ ተከናውኗል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል የተዘረጋው የማስተላለፊያ መስመር እና የፕሮቴክሽንና የዳታ ኮሙዩኒኬሽን መስመር (ኦፕቲካሌ ግራውንድ ፋይበር) 440 ኪል ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን 994 የከፍተኛ ኃይሌ ተሸካሚ የብረት ታወሮች አሉት።
ኢትዮጵያ የምታስተላልፈው ኃይል ያልተቆራረጠና አስተማማኝ እንዲሆን የሚያግዙ ተግባራትን ያጠናቀቀች ሲሆን በኬንያ በኩል ተመሳሳይ ሥራዎች ተሰርተው በቅርቡ ወደተግባር እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ ከደቡብ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወላይታ፣ ጋሞ እና ኮንሶ ዞን እንዲሁም ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክሌሊዊ መንግስት የቦረና ዞን አቋርጦ ነው ወደ ኬንያ ኃይል የሚያስተላልፈው።
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ከጅቡቲ ጋር የኃይሌ ሽያጭ እያካሔደች ሲሆን ከሶማሌላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤላክትሪክ ኃይሌ ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርማለች።
ባለፈው ዓመት ለሱዳን እና ለጅቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገው የኤላክትሪክ ኃይሌ 95 ነጥብ 4 ሚሉየን የአሜሪካን ዶሊር ገቢ ተገኝቷል፡፡
(ፎቶ ፋይል)
********
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያ ዛሬ በይፋ የኤላክትሪክ ሽያጭ ጀምሯል፡፡
በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሥራ ከጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ሲከናወን ቆይቷል፡፡
ዛሬ በይፋ ኃይል ማስተላለፍ የጀመረው የኢትዮ - ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር በዓመት እስከ አንድ መቶ ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ማስገባት አቅም ያለው ሲሆን ከኬንያ አሌፎ ከታንዛኒያ እስከ ደቡብ አፍሪካ ላሉት ሀገራት እስከ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት ኤላክትክ የማስተላለፍ አቅም አለው፡፡
የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት ለአማካሪ ድርጅቱ፣ ለካሳ ክፍያና የተሰረቁ መሰረተ ሌማቶችን ለመተካት የወጣውን ወጪ ጨምሮ ወደ አምስት መቶ ሚሊየን የአሜሪካ ዶሊር ወጪ ተደርጎበታል፡፡
ከዚህ ውስጥ 214 ነጥብ 5 ሚሉዮን ዶላሩ ለኮንቨርተር ስቴሽኑና ለግራውንድ ኤላክትሮድ መስመር የግንባታ ሥራ እንዲሁም 120 ሚሉዮን ዶላሩ ደግሞ ለማስተላለፊያ መስመሩ የዋለ ነው፡፡
የኢትዮ- ኬኒያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ "CET" በተሰኘ የቻይና ኩባንያ የተከናወነ ሲሆን የኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያውና የግራውንድ ኤላክትሮድ መስመሩ ደግሞ ሲመንስ በተሰኘ ኩባንያ ተከናውኗል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል የተዘረጋው የማስተላለፊያ መስመር እና የፕሮቴክሽንና የዳታ ኮሙዩኒኬሽን መስመር (ኦፕቲካሌ ግራውንድ ፋይበር) 440 ኪል ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን 994 የከፍተኛ ኃይሌ ተሸካሚ የብረት ታወሮች አሉት።
ኢትዮጵያ የምታስተላልፈው ኃይል ያልተቆራረጠና አስተማማኝ እንዲሆን የሚያግዙ ተግባራትን ያጠናቀቀች ሲሆን በኬንያ በኩል ተመሳሳይ ሥራዎች ተሰርተው በቅርቡ ወደተግባር እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ ከደቡብ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የወላይታ፣ ጋሞ እና ኮንሶ ዞን እንዲሁም ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክሌሊዊ መንግስት የቦረና ዞን አቋርጦ ነው ወደ ኬንያ ኃይል የሚያስተላልፈው።
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከሱዳን እና ከጅቡቲ ጋር የኃይሌ ሽያጭ እያካሔደች ሲሆን ከሶማሌላንድ፣ ታንዛኒያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤላክትሪክ ኃይሌ ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርማለች።
ባለፈው ዓመት ለሱዳን እና ለጅቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገው የኤላክትሪክ ኃይሌ 95 ነጥብ 4 ሚሉየን የአሜሪካን ዶሊር ገቢ ተገኝቷል፡፡
(ፎቶ ፋይል)
አምስተኛው አዲስ ቻምበር አለም አቀፍ የማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ ንግድ ትርኢት ተከፈተ
******
(ኢ ፕ ድ)
11 አጋራት የሚሳተፉበት አምስተኛው አዲስ ቻምበር አለም አቀፍ የማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ ንግድ ትርኢት ዛሬ በኤግዚቢሽን ማእከል ተከፍቷል።
የንግድ ትርኢቱን የከፈቱት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የአገርን ምርትና ገበያ ለወጪው አለም ለማስተዋወቅ እንዲሁም የወጪውን ለማወቅ ትርኢቱ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል።
በዘርፉ በአገራት መከካል ልምድ ለመለዋወጥና የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደሚረዳም ጠቅሰዋል።
ንግድ ትርኢት "manufacturing for enhanced employment" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ ቴክኖሎጂ ተኮር የማኑፋክቸሪንግ ግበአቶች ከአምራች ኩባንያዎች ለሸማቹ ማህበረሰብ እንደሚቀርብ ተጠቅሷል።
በንግድ ትርኢቱ ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ዩጋንዳ፣ ህንድ፣ ጆርዳን፣ ፓኪስታን ሳኡዲ አርቢያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስና ቻይና ተሳታፊ ናቸው።
በአዲሱ ገረመው
******
(ኢ ፕ ድ)
11 አጋራት የሚሳተፉበት አምስተኛው አዲስ ቻምበር አለም አቀፍ የማኑፋክቸሪንግ ቴክኖሎጂ ንግድ ትርኢት ዛሬ በኤግዚቢሽን ማእከል ተከፍቷል።
የንግድ ትርኢቱን የከፈቱት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የአገርን ምርትና ገበያ ለወጪው አለም ለማስተዋወቅ እንዲሁም የወጪውን ለማወቅ ትርኢቱ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል።
በዘርፉ በአገራት መከካል ልምድ ለመለዋወጥና የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንደሚረዳም ጠቅሰዋል።
ንግድ ትርኢት "manufacturing for enhanced employment" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ ቴክኖሎጂ ተኮር የማኑፋክቸሪንግ ግበአቶች ከአምራች ኩባንያዎች ለሸማቹ ማህበረሰብ እንደሚቀርብ ተጠቅሷል።
በንግድ ትርኢቱ ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ዩጋንዳ፣ ህንድ፣ ጆርዳን፣ ፓኪስታን ሳኡዲ አርቢያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት አረብ ኢሜሬትስና ቻይና ተሳታፊ ናቸው።
በአዲሱ ገረመው
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ለአፋር ክልል የ285 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
******
(ኢ ፕ ድ)
በሰሜኑ ጦርነት የተነሳ ለችግር የተጋለጡና በአፋር የሚገኙ 24 ሺህ 200 ተፈናቃዮችን ለመርዳት 170 ሚሊዮን ብር መመደቡን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በተጨማሪ በአፋር ክልል በከተሞች ለሚተገበረው ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት 115 ሚሊዮን ብር ተመድቧል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ድጋፉ በአጠቃላይ 285 ሚሊዮን ብር ነው፤ ገንዘቡ ቀጥታ ለተጎጂዎች በአካውንት የሚደርስ ነው ብለዋል።
ድጋፉን የተቀበሉት የአፋር ክልል ፕሬዚዳንት ሃጂ አወል አርባ ሚኒስቴሩ ከተፈናቃዮች ድጋፍ ባለፈ በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ገንዘብ መመደቡን አድንቀው ምስጋና አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
******
(ኢ ፕ ድ)
በሰሜኑ ጦርነት የተነሳ ለችግር የተጋለጡና በአፋር የሚገኙ 24 ሺህ 200 ተፈናቃዮችን ለመርዳት 170 ሚሊዮን ብር መመደቡን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በተጨማሪ በአፋር ክልል በከተሞች ለሚተገበረው ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት 115 ሚሊዮን ብር ተመድቧል።
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ ድጋፉ በአጠቃላይ 285 ሚሊዮን ብር ነው፤ ገንዘቡ ቀጥታ ለተጎጂዎች በአካውንት የሚደርስ ነው ብለዋል።
ድጋፉን የተቀበሉት የአፋር ክልል ፕሬዚዳንት ሃጂ አወል አርባ ሚኒስቴሩ ከተፈናቃዮች ድጋፍ ባለፈ በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ገንዘብ መመደቡን አድንቀው ምስጋና አቅርበዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም