የኮንስትራክሽን ኤክስፖና አውደ ርዕይ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከዲ ኤም ጂ ኢቨንትስ፣ከኢትኤል ኢቨንትስና ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን ያዘጋጁት የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ኤክስፖ በሚሊኒየም አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል።
ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት በሚቆየው ኤክስፖ የሀገሪቱን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለማነቃቃትና የዘርፉን ችግሮች ለመፍታት እንደሚረዳ ተጠቁሟል።
መድረኩ የዘርፉን ተዋናዮች ለማገናኘትና አብሮ የመስራት ባህልን ለማጎልበት የላቀ ሚና ይኖረዋል። ከ24 ሀገራት የተውጣጡ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
ኤክስፖው ለኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ እድገት ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ለማግኘት፣ ለልምድ ልውውጥ፣ በዘርፉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለማስተዋወቅ እንደሚያግዝ ተመላክቷል፡፡
በኤክስፖው ማስጀመሪያ ሥነስርዓት ላይ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ከኤክስፖው ጎን ለጎን በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የተዘጋጀ የሚኒስትሮች የጋራ ፎረም እየተካሄደ ይገኛል።
መላኩ ኤሮሴ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከዲ ኤም ጂ ኢቨንትስ፣ከኢትኤል ኢቨንትስና ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን ያዘጋጁት የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ኤክስፖ በሚሊኒየም አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል።
ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት በሚቆየው ኤክስፖ የሀገሪቱን የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለማነቃቃትና የዘርፉን ችግሮች ለመፍታት እንደሚረዳ ተጠቁሟል።
መድረኩ የዘርፉን ተዋናዮች ለማገናኘትና አብሮ የመስራት ባህልን ለማጎልበት የላቀ ሚና ይኖረዋል። ከ24 ሀገራት የተውጣጡ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
ኤክስፖው ለኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ እድገት ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ለማግኘት፣ ለልምድ ልውውጥ፣ በዘርፉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለማስተዋወቅ እንደሚያግዝ ተመላክቷል፡፡
በኤክስፖው ማስጀመሪያ ሥነስርዓት ላይ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። ከኤክስፖው ጎን ለጎን በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የተዘጋጀ የሚኒስትሮች የጋራ ፎረም እየተካሄደ ይገኛል።
መላኩ ኤሮሴ
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት‼️
የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍራንሲያ ማርኬዝን ዛሬ አግኝቻቸዋለሁ። በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን ለማጠናከር እና በተለያዩ ዘርፎች የትብብር ዕድሎችን ለማስፋት አብረን እንሠራለን።
የኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍራንሲያ ማርኬዝን ዛሬ አግኝቻቸዋለሁ። በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን ለማጠናከር እና በተለያዩ ዘርፎች የትብብር ዕድሎችን ለማስፋት አብረን እንሠራለን።
የዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሐምሌ 03 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ይሰጣል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሐምሌ 03 ቀን ጀምሮ እስከ ሐምሌ 13 2015 ዓ.ም ድረስ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሰታወቀ።
የ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ፈተናውን እንደሚወስዱም ተገልጿል ።
በ2014 ዓ.ም የህግ መውጫ ፈተና ተፈትነው ማለፊያ ነጥብ ያላስመዘገቡ ተማሪዎችም በዚሁ ጊዜ ፈተናውን መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።
ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናን ለመሥጠት የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሐምሌ 03 ቀን ጀምሮ እስከ ሐምሌ 13 2015 ዓ.ም ድረስ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሰታወቀ።
የ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ፈተናውን እንደሚወስዱም ተገልጿል ።
በ2014 ዓ.ም የህግ መውጫ ፈተና ተፈትነው ማለፊያ ነጥብ ያላስመዘገቡ ተማሪዎችም በዚሁ ጊዜ ፈተናውን መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።
ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናን ለመሥጠት የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት ‼️
በተቋማዊ አሠራር ላይ ያለውን ሂደት ለመገምገም ባለን ቁርጠኝነት ዛሬ የሚኒስትሮችን የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸምን ግምገማ ጀምረናል። የግምገማ ሂደቱም በአጠቃላይ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚውን እና የሴክተሮች ልዩ አፈጻጸምንም ይዳስሳል።
በተቋማዊ አሠራር ላይ ያለውን ሂደት ለመገምገም ባለን ቁርጠኝነት ዛሬ የሚኒስትሮችን የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸምን ግምገማ ጀምረናል። የግምገማ ሂደቱም በአጠቃላይ የዘጠኝ ወር የማክሮ ኢኮኖሚውን እና የሴክተሮች ልዩ አፈጻጸምንም ይዳስሳል።