በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር እስካሁን ከ25 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
"አረንጓዴ አሻራችን ለዘላቂ ልማታችን" በሚል መሪ ሀሳብ አረንጓዴ አሻራ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት በሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ነው።
መርሃግብሩን በንግግር የከፈቱት የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ አንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በቂ መሬት፣ አመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞችና አምራች ሃይል እያላት ለምግብ እህል ግዢ ቢሊዮን ዶላሮችን ስታወጣ ቆይታለች። ይህን ሁኔታ ለመቀየር የአረንጋዴ ልማት ስትራቴጂ ተቀርጾ እየተተገበረ ይገኛል።
ከዚህ ጋር በተያያዝ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጭነት በተጀመረው አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ከ2011እስከ 2014 ባሉት ዓመታት 20 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ በተከናወነው የአረንጋዴ አሻራ መርሃግብር ከ25 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል፤ አቶ አደም።
አረንጓዴ አሻራ የተሻለች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን ለማውረስ የምንሰራበት እሳቤ ነው ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ በአረንጋዴ አሻራ የተገኘው ውጤት ከአባይ ግድብ ቀጥሎ ኢትዮጵያ ታላላቅ ፕሮጀክቶን አቅዳ መፈጸም እንደምትችል ያረጋገጠችበት ነው ብለዋል።
የእስካሁኑ የአረንጋዴ አሻራ መርሃ ግብር በስኬት መጠናቀቁን አመልክተው፤ ለዘንድሮው ዓመት በሚጀመረው ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብርም እስካሁን የተገኙ ልምዶችን ቀምሮ አገርንና ሕዝብን በሚጠቅም መልኩ በላቀ መልኩ ለመተግበር እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህ መርሃግብር ስኬትም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል።
የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት በተከናወነው አረንጋዴ አሻራ ኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት አስመዝግባለች ብለዋል።
ይህን መልካም ተሞክሮ ወደ ጎረቤት ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቁመው፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸውን እንዲሁም ኢትዮጵያ ልምድ እንድታካፍላቸው በይፋ ልምድ የጠየቁ አገራት መኖራቸውንም ገልጸዋል።
ባለፉት አራት ዓመታት በተከናወነው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ900ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ እድል ተፈጥሯል ነው ያሉት።
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ሰባት ቢሊዮን በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ግብርና ሚኒስቴር መግለጹ ይታወሳል።
በፋንታነሽ ክንዴ
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
"አረንጓዴ አሻራችን ለዘላቂ ልማታችን" በሚል መሪ ሀሳብ አረንጓዴ አሻራ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት በሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ነው።
መርሃግብሩን በንግግር የከፈቱት የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ አንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በቂ መሬት፣ አመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞችና አምራች ሃይል እያላት ለምግብ እህል ግዢ ቢሊዮን ዶላሮችን ስታወጣ ቆይታለች። ይህን ሁኔታ ለመቀየር የአረንጋዴ ልማት ስትራቴጂ ተቀርጾ እየተተገበረ ይገኛል።
ከዚህ ጋር በተያያዝ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ሀሳብ አመንጭነት በተጀመረው አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ከ2011እስከ 2014 ባሉት ዓመታት 20 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ በተከናወነው የአረንጋዴ አሻራ መርሃግብር ከ25 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል፤ አቶ አደም።
አረንጓዴ አሻራ የተሻለች ኢትዮጵያን ለልጆቻችን ለማውረስ የምንሰራበት እሳቤ ነው ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ በአረንጋዴ አሻራ የተገኘው ውጤት ከአባይ ግድብ ቀጥሎ ኢትዮጵያ ታላላቅ ፕሮጀክቶን አቅዳ መፈጸም እንደምትችል ያረጋገጠችበት ነው ብለዋል።
የእስካሁኑ የአረንጋዴ አሻራ መርሃ ግብር በስኬት መጠናቀቁን አመልክተው፤ ለዘንድሮው ዓመት በሚጀመረው ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብርም እስካሁን የተገኙ ልምዶችን ቀምሮ አገርንና ሕዝብን በሚጠቅም መልኩ በላቀ መልኩ ለመተግበር እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህ መርሃግብር ስኬትም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል።
የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አነሳሽነት በተከናወነው አረንጋዴ አሻራ ኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት አስመዝግባለች ብለዋል።
ይህን መልካም ተሞክሮ ወደ ጎረቤት ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቁመው፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸውን እንዲሁም ኢትዮጵያ ልምድ እንድታካፍላቸው በይፋ ልምድ የጠየቁ አገራት መኖራቸውንም ገልጸዋል።
ባለፉት አራት ዓመታት በተከናወነው አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከ900ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ እድል ተፈጥሯል ነው ያሉት።
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ሰባት ቢሊዮን በላይ ችግኞች መዘጋጀታቸውን ግብርና ሚኒስቴር መግለጹ ይታወሳል።
በፋንታነሽ ክንዴ
የአፍሪካ ኅብረት 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ከግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ ም ጀምሮ ይከበራል
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ኅብረት 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ከግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ዓመት እንደሚከበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኅብረቱ አባል ሀገራት በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች በየሀገራቸው እንደሚያከብሩም ጠቁመዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ በዓሉን የምታከብረው የኅብረቱን ዓላማ ለማሳካት እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን በማጉላትና የአዲስ አበባን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ለማፅናት በሚያስችል ሁኔታ እንደሆነ ገልጸዋል።
ባለፉት 60 ዓመታት የአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ጉዞ፣ እንቅስቃሴ፣ ስኬቶችና ፈተናዎች ተዳስሰው አፍሪካውያን ለተሻለ ሥራ የሚንቀሳቀሱበት ይሆናል ብለዋል።
ከሱዳን ቀውስ ጋር በተገናኘ የኢትዮጵያና የሌሎች አገራት ዜጎችን የማስወጣቱ ሂደት ቀጥሏል። መረጃው እስከተሰበሰበበት ጊዜ ድረስ በመተማና በኩምሩክ በኩል በድምሩ 17 ሺህ 885 ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። የሱዳን ችግርም በሰላም እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት የጸና አቋም እንዳለው ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99837
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ኅብረት 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ከግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ዓመት እንደሚከበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኅብረቱ አባል ሀገራት በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች በየሀገራቸው እንደሚያከብሩም ጠቁመዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ በዓሉን የምታከብረው የኅብረቱን ዓላማ ለማሳካት እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን በማጉላትና የአዲስ አበባን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ለማፅናት በሚያስችል ሁኔታ እንደሆነ ገልጸዋል።
ባለፉት 60 ዓመታት የአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ጉዞ፣ እንቅስቃሴ፣ ስኬቶችና ፈተናዎች ተዳስሰው አፍሪካውያን ለተሻለ ሥራ የሚንቀሳቀሱበት ይሆናል ብለዋል።
ከሱዳን ቀውስ ጋር በተገናኘ የኢትዮጵያና የሌሎች አገራት ዜጎችን የማስወጣቱ ሂደት ቀጥሏል። መረጃው እስከተሰበሰበበት ጊዜ ድረስ በመተማና በኩምሩክ በኩል በድምሩ 17 ሺህ 885 ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። የሱዳን ችግርም በሰላም እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት የጸና አቋም እንዳለው ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99837
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት ፍራንሲያ ማርኩዌዝ ጋር ብሄራዊ ሙዚየምን ጎበኙ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍራንሲያ ማርኩዌዝ ጋር ብሄራዊ ሙዚየምን ጎብኝተዋል፡፡
በኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት የተመራው የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየምን ጨምሮ በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን መጎብኘታቸው የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የጉብኝቱ መርሀግብር በቱሪዝም ሚኒስቴር እና በዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነዉ ተብሏል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍራንሲያ ማርኩዌዝ ጋር ብሄራዊ ሙዚየምን ጎብኝተዋል፡፡
በኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት የተመራው የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየምን ጨምሮ በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን መጎብኘታቸው የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የጉብኝቱ መርሀግብር በቱሪዝም ሚኒስቴር እና በዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነዉ ተብሏል።