የአፍሪካ ኅብረት 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ከግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ ም ጀምሮ ይከበራል
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ኅብረት 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ከግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ዓመት እንደሚከበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኅብረቱ አባል ሀገራት በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች በየሀገራቸው እንደሚያከብሩም ጠቁመዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ በዓሉን የምታከብረው የኅብረቱን ዓላማ ለማሳካት እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን በማጉላትና የአዲስ አበባን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ለማፅናት በሚያስችል ሁኔታ እንደሆነ ገልጸዋል።
ባለፉት 60 ዓመታት የአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ጉዞ፣ እንቅስቃሴ፣ ስኬቶችና ፈተናዎች ተዳስሰው አፍሪካውያን ለተሻለ ሥራ የሚንቀሳቀሱበት ይሆናል ብለዋል።
ከሱዳን ቀውስ ጋር በተገናኘ የኢትዮጵያና የሌሎች አገራት ዜጎችን የማስወጣቱ ሂደት ቀጥሏል። መረጃው እስከተሰበሰበበት ጊዜ ድረስ በመተማና በኩምሩክ በኩል በድምሩ 17 ሺህ 885 ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። የሱዳን ችግርም በሰላም እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት የጸና አቋም እንዳለው ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99837
**************************
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ኅብረት 60ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ከግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ዓመት እንደሚከበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኅብረቱ አባል ሀገራት በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች በየሀገራቸው እንደሚያከብሩም ጠቁመዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ በዓሉን የምታከብረው የኅብረቱን ዓላማ ለማሳካት እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን በማጉላትና የአዲስ አበባን የዲፕሎማሲ ማዕከልነት ለማፅናት በሚያስችል ሁኔታ እንደሆነ ገልጸዋል።
ባለፉት 60 ዓመታት የአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ጉዞ፣ እንቅስቃሴ፣ ስኬቶችና ፈተናዎች ተዳስሰው አፍሪካውያን ለተሻለ ሥራ የሚንቀሳቀሱበት ይሆናል ብለዋል።
ከሱዳን ቀውስ ጋር በተገናኘ የኢትዮጵያና የሌሎች አገራት ዜጎችን የማስወጣቱ ሂደት ቀጥሏል። መረጃው እስከተሰበሰበበት ጊዜ ድረስ በመተማና በኩምሩክ በኩል በድምሩ 17 ሺህ 885 ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። የሱዳን ችግርም በሰላም እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግሥት የጸና አቋም እንዳለው ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99837
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዚዳንት ፍራንሲያ ማርኩዌዝ ጋር ብሄራዊ ሙዚየምን ጎበኙ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍራንሲያ ማርኩዌዝ ጋር ብሄራዊ ሙዚየምን ጎብኝተዋል፡፡
በኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት የተመራው የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየምን ጨምሮ በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን መጎብኘታቸው የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የጉብኝቱ መርሀግብር በቱሪዝም ሚኒስቴር እና በዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነዉ ተብሏል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ፍራንሲያ ማርኩዌዝ ጋር ብሄራዊ ሙዚየምን ጎብኝተዋል፡፡
በኮሎምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት የተመራው የልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየምን ጨምሮ በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን መጎብኘታቸው የቱሪዝም ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
የጉብኝቱ መርሀግብር በቱሪዝም ሚኒስቴር እና በዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነዉ ተብሏል።