የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት ከህወሃት ታጣቂ ሀይሎች የቡድን መሳሪያዎችን ተረከበ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች በፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ዛሬ መቀለ አቅራቢያ በሚገኘው ላጪ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የቡድን መሳሪያዎችን ለመከላከያ ሰራዊት ተወካዮች ዛሬ አስረክበዋል።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በእጃቸው የነበረ የቡድን መሳሪያ ማለትም ዲሽቃ፣ አርፒጂ፣ መትረየስና ሞርታር የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስረክበዋል።
በርክክቡ ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ እንዳሉት፤ ርክክብቡ የሰላም ስምምነቱ አንዱ አካል ነው።
የህወሓት ታጣቂ ሀይሎች ተወካይ ብርጋዲየር ጀነራል ምግበይ ሃይለ በበኩላቸው ርክክቡ በሰላም ስምምነት መሰረት መሰረት መፈጸሙን ተናግረዋል። ሰላም የመጀመሪያና የመጨረሻ ግባችን ነውም ብለዋል።
ርክክቡ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ስምምነቱ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ማረጋገጥ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ተከናውነናል።
ከቡድን መሳሪያዎቹ ርክክብ በኋላ መግለጫ የሰጡት በአፍሪካ ሕብረት ታዛቢ እና አረካካቢ ኮሚቴ አባል ብርጋዴር ጀነራል ቴፎ ሰኮሌ የርክክብ ሂደቱ የሰላም ስምምነቱ በጥሩ መልኩ እየሄደ መሆኑን አንዱ ማሳያ ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች በፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ዛሬ መቀለ አቅራቢያ በሚገኘው ላጪ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የቡድን መሳሪያዎችን ለመከላከያ ሰራዊት ተወካዮች ዛሬ አስረክበዋል።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በእጃቸው የነበረ የቡድን መሳሪያ ማለትም ዲሽቃ፣ አርፒጂ፣ መትረየስና ሞርታር የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስረክበዋል።
በርክክቡ ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ እንዳሉት፤ ርክክብቡ የሰላም ስምምነቱ አንዱ አካል ነው።
የህወሓት ታጣቂ ሀይሎች ተወካይ ብርጋዲየር ጀነራል ምግበይ ሃይለ በበኩላቸው ርክክቡ በሰላም ስምምነት መሰረት መሰረት መፈጸሙን ተናግረዋል። ሰላም የመጀመሪያና የመጨረሻ ግባችን ነውም ብለዋል።
ርክክቡ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ስምምነቱ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ማረጋገጥ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ተከናውነናል።
ከቡድን መሳሪያዎቹ ርክክብ በኋላ መግለጫ የሰጡት በአፍሪካ ሕብረት ታዛቢ እና አረካካቢ ኮሚቴ አባል ብርጋዴር ጀነራል ቴፎ ሰኮሌ የርክክብ ሂደቱ የሰላም ስምምነቱ በጥሩ መልኩ እየሄደ መሆኑን አንዱ ማሳያ ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
#ከኢፕድ_ማህደር
ሁለት ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው 2 ዓመት እስራት ተፈረደበት
ሊጠጣ ገብቶ ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው መላኩ ምህረቴ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡
በሌብነት ወንጀል ተከሶ ስምንት ጊዜ የተቀጣው መላኩ ምህረቴ ዘጠነኛውን የስርቆት ወንጀል ሲፈጽም የተያዘው በደሴ ከተማ ባለፈው ሐምሌ 27 ቀን 1962 ዓ.ም ነው፡፡
ተከሳሹ በዚሁ ቀን እመት የሺ ነዋይ ከተባሉት ሴት መጠጥ ቤት ገብቶ ሁለት ጠርሙስ አረቄ ስረቆ መውሰዱን እራሱም ከማመኑም በላይ በማስረጃም ተረጋግጦበታል፡፡
በዚህ አድራጎቱ ተከሶ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ የደሴ ዙሪያ አውራጃ ፈርድ ቤት በዋለው ችሎት ወስኖበታል፡፡
መስከረም 7 ቀን 1963 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የታተመ
ሁለት ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው 2 ዓመት እስራት ተፈረደበት
ሊጠጣ ገብቶ ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው መላኩ ምህረቴ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡
በሌብነት ወንጀል ተከሶ ስምንት ጊዜ የተቀጣው መላኩ ምህረቴ ዘጠነኛውን የስርቆት ወንጀል ሲፈጽም የተያዘው በደሴ ከተማ ባለፈው ሐምሌ 27 ቀን 1962 ዓ.ም ነው፡፡
ተከሳሹ በዚሁ ቀን እመት የሺ ነዋይ ከተባሉት ሴት መጠጥ ቤት ገብቶ ሁለት ጠርሙስ አረቄ ስረቆ መውሰዱን እራሱም ከማመኑም በላይ በማስረጃም ተረጋግጦበታል፡፡
በዚህ አድራጎቱ ተከሶ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ የደሴ ዙሪያ አውራጃ ፈርድ ቤት በዋለው ችሎት ወስኖበታል፡፡
መስከረም 7 ቀን 1963 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የታተመ
ክልሎች በመጋዘን የሚገኘውን የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶአደሩ በወቅቱ እንዲያደርሱ ግብርና ሚኒስቴር አሳሰበ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በክልሎች በመጋዘን የሚገኘው ሰባት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶአደሩ በወቅቱ ማድረስ እንደሚገባ ግብርና ሚኒስቴር አሳሰበ።
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ እንደገለጹት፤ ለ2015/16 ምርት ዘመን 12 ነጥብ 87 ሚሊዮን ኩንታል በመግዛት እና የከረመውን ሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ጨምሮ በምርት ዘመኑ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100618
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በክልሎች በመጋዘን የሚገኘው ሰባት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶአደሩ በወቅቱ ማድረስ እንደሚገባ ግብርና ሚኒስቴር አሳሰበ።
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ እንደገለጹት፤ ለ2015/16 ምርት ዘመን 12 ነጥብ 87 ሚሊዮን ኩንታል በመግዛት እና የከረመውን ሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ጨምሮ በምርት ዘመኑ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100618
በትግራይ ክልል በሁለት ወራት የእናቶችና ሕፃናት ክትባት ሽፋንን 83 በመቶ ማድረስ ተችሏል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የትግራይ ክልል ጤና ዘርፍ ከሰላም ስምምነቱ ወዲህ በሁለት ወራት ውስጥ በተከናወኑ ስራዎች የእናቶችና ሕፃናት ክትባት 83 በመቶ መድረሱን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ተስፋይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ የክልሉ የጤና ዘርፍ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት ምንም አይነት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100629
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የትግራይ ክልል ጤና ዘርፍ ከሰላም ስምምነቱ ወዲህ በሁለት ወራት ውስጥ በተከናወኑ ስራዎች የእናቶችና ሕፃናት ክትባት 83 በመቶ መድረሱን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ተስፋይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ የክልሉ የጤና ዘርፍ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት ምንም አይነት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100629
ለአርሶ አደሮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው
- የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
የዲጂታል ግብርና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ በሚል መሪ ሀሳብ የፖናል ወይይት በመካሄድ ላይ ነው፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ለአርሶና አርብቶ አደሮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት ለመዘርጋትና በግብርናው ዘርፍ የዲጂታል ቴክኖሎጂን ተደራሽነትን እውን ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የግብርናው ዘርፍ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አገራዊ የኢኖሚያዊ እድገትን ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው፡፡
የኢኖቨሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ሁሪያ አሊን በበኩላቸው እንደ አገር በግብርናውን ዘርፍ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለአርሶ አደሩ መረጃ ተደራሽ በማድረግ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ይረዳል፡፡
በተለይም እንደ አገር ዘርፋ የተሻለ ቴክኖሎጂ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በውይይቱ የፌድራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎችን ጨምሮ ከ200 በላይ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
በማርቆስ በላይ
- የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
የዲጂታል ግብርና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ በሚል መሪ ሀሳብ የፖናል ወይይት በመካሄድ ላይ ነው፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ለአርሶና አርብቶ አደሮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት ለመዘርጋትና በግብርናው ዘርፍ የዲጂታል ቴክኖሎጂን ተደራሽነትን እውን ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የግብርናው ዘርፍ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አገራዊ የኢኖሚያዊ እድገትን ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው፡፡
የኢኖቨሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ሁሪያ አሊን በበኩላቸው እንደ አገር በግብርናውን ዘርፍ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለአርሶ አደሩ መረጃ ተደራሽ በማድረግ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ይረዳል፡፡
በተለይም እንደ አገር ዘርፋ የተሻለ ቴክኖሎጂ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በውይይቱ የፌድራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎችን ጨምሮ ከ200 በላይ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
በማርቆስ በላይ