Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት ከህወሃት ታጣቂ ሀይሎች የቡድን መሳሪያዎችን ተረከበ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የሕወሓት ታጣቂ ኃይሎች በፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ዛሬ መቀለ አቅራቢያ በሚገኘው ላጪ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የቡድን መሳሪያዎችን ለመከላከያ ሰራዊት ተወካዮች ዛሬ አስረክበዋል።
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች በእጃቸው የነበረ የቡድን መሳሪያ ማለትም ዲሽቃ፣ አርፒጂ፣ መትረየስና ሞርታር የተባሉ የጦር መሳርያዎችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አስረክበዋል።
በርክክቡ ወቅት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያ እንዳሉት፤ ርክክብቡ የሰላም ስምምነቱ አንዱ አካል ነው።
የህወሓት ታጣቂ ሀይሎች ተወካይ ብርጋዲየር ጀነራል ምግበይ ሃይለ በበኩላቸው ርክክቡ በሰላም ስምምነት መሰረት መሰረት መፈጸሙን ተናግረዋል። ሰላም የመጀመሪያና የመጨረሻ ግባችን ነውም ብለዋል።
ርክክቡ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ስምምነቱ ክትትል፣ ቁጥጥር እና ማረጋገጥ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ተከናውነናል።
ከቡድን መሳሪያዎቹ ርክክብ በኋላ መግለጫ የሰጡት በአፍሪካ ሕብረት ታዛቢ እና አረካካቢ ኮሚቴ አባል ብርጋዴር ጀነራል ቴፎ ሰኮሌ የርክክብ ሂደቱ የሰላም ስምምነቱ በጥሩ መልኩ እየሄደ መሆኑን አንዱ ማሳያ ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
#ከኢፕድ_ማህደር

ሁለት ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው 2 ዓመት እስራት ተፈረደበት

ሊጠጣ ገብቶ ጠርሙስ አረቄ የሰረቀው መላኩ ምህረቴ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡

በሌብነት ወንጀል ተከሶ ስምንት ጊዜ የተቀጣው መላኩ ምህረቴ ዘጠነኛውን የስርቆት ወንጀል ሲፈጽም የተያዘው በደሴ ከተማ ባለፈው ሐምሌ 27 ቀን 1962 ዓ.ም ነው፡፡

ተከሳሹ በዚሁ ቀን እመት የሺ ነዋይ ከተባሉት ሴት መጠጥ ቤት ገብቶ ሁለት ጠርሙስ አረቄ ስረቆ መውሰዱን እራሱም ከማመኑም በላይ በማስረጃም ተረጋግጦበታል፡፡

በዚህ አድራጎቱ ተከሶ በ2 ዓመት እስራት እንዲቀጣ የደሴ ዙሪያ አውራጃ ፈርድ ቤት በዋለው ችሎት ወስኖበታል፡፡

መስከረም 7 ቀን 1963 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የታተመ
የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ እግድ መነሳቱን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታወቀ
ክልሎች በመጋዘን የሚገኘውን የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶአደሩ በወቅቱ እንዲያደርሱ ግብርና ሚኒስቴር አሳሰበ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በክልሎች በመጋዘን የሚገኘው ሰባት ነጥብ አንድ ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶአደሩ በወቅቱ ማድረስ እንደሚገባ ግብርና ሚኒስቴር አሳሰበ።
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ እንደገለጹት፤ ለ2015/16 ምርት ዘመን 12 ነጥብ 87 ሚሊዮን ኩንታል በመግዛት እና የከረመውን ሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኩንታል ጨምሮ በምርት ዘመኑ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100618
በትግራይ ክልል በሁለት ወራት የእናቶችና ሕፃናት ክትባት ሽፋንን 83 በመቶ ማድረስ ተችሏል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የትግራይ ክልል ጤና ዘርፍ ከሰላም ስምምነቱ ወዲህ በሁለት ወራት ውስጥ በተከናወኑ ስራዎች የእናቶችና ሕፃናት ክትባት 83 በመቶ መድረሱን የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ተስፋይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ የክልሉ የጤና ዘርፍ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት ምንም አይነት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100629
ለአርሶ አደሮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው
- የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
የዲጂታል ግብርና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ በሚል መሪ ሀሳብ የፖናል ወይይት በመካሄድ ላይ ነው፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ለአርሶና አርብቶ አደሮች በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የመረጃ ሥርዓት ለመዘርጋትና በግብርናው ዘርፍ የዲጂታል ቴክኖሎጂን ተደራሽነትን እውን ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የግብርናው ዘርፍ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት አገራዊ የኢኖሚያዊ እድገትን ለማረጋገጥ የሚረዳ ነው፡፡
የኢኖቨሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ ሁሪያ አሊን በበኩላቸው እንደ አገር በግብርናውን ዘርፍ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለአርሶ አደሩ መረጃ ተደራሽ በማድረግ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ይረዳል፡፡
በተለይም እንደ አገር ዘርፋ የተሻለ ቴክኖሎጂ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በውይይቱ የፌድራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎችን ጨምሮ ከ200 በላይ ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው፡፡
በማርቆስ በላይ
የአዲስ ዘመን ጋዜጣ የግንቦት 19 ቀን 2015 ዓ.ም የስራ ማስታወቂያ፣ መልካም ዕድል‼️
ዶክተር አረጋዊ በርሄ የህዳሴው ግድብ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ይናገራሉ‼️

👉 ኢትዮጵያ ዓባይን ፍትሐዊ በሆነ መልኩ መጠቀሟን ትቀጥላለች፣

👉 ዓባይን የመጠቀም ጉዳይ ዓባይ በሚደርስባቸው የተፋሰሱ አገሮች ብቻ መታየት ይኖርበታል፣

👉 የዓረብ ሊግም ጉዳዩን ሲያይ በሐቅ እና በፍትሐዊነት ላይ ተመሥርቶ አልነበረም፤ ከግብፅ ጋር ያለውን የጠበቀ ግንኙነት በሚያንፀባርቅ መልኩ አድሏዊ በሆነ መንገድ ነው፤ ይህ በዓለም አቀፍ የውኃ ሕግ ተቀባይነት የለውም፣

👉 በየትኛውም የሕግ መለኪያ የዓረብ አገሮችም ሆኑ ምክር ቤቱ በምንም መልኩ ከዓባይ ወንዝ ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች በሚመለከታቸው የተፋሰሱ አገሮች ላይ ጣልቃ መግባት አይችሉም፣

👉 ግብፅ ከድሮ ጀምሮ የዓባይን ውሃ ለመቆጣጠርና የበላይነቷን ለማረጋገጥ በየትኛውም መልኩ ጥረት ታደርጋለች፣ የዓባይን ውሃ ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር ኢትዮጵያ ላይ ጦርነት እስከ መክፈት የደረሰችበት ጊዜም ነበር፣

👉 በፍትሐዊነት መንገድ ሦስቱ አገሮች ቁጭ ብለው ተወያይተው ችግሩን መፍታት ይችላሉ፣

👉 የአፍሪካን ችግር በአፍሪካውያን የሚለውን መርሕ ተከትላ አስፈላጊም ከሆነ ሁለተኛ ወገን ጨምራ በመወያየት የጋራ ጥቅምን ማስከበር ይቻላል፣

👉 ከመነሻው ግብፅ ፍትሐዊ የሆነ የውሃ ክፍፍልን አትፈልግም፤ ይህንን ፍትሐዊ ያልሆነ ክፍፍል ሊደግፍና ተግባራዊ እንዲሆን ሃሳብ ሊሰነዝርላት የሚችለው የዓረብ ሊግ ወይም ዓረብ አገራት ናቸው ብላ ታምናለች፣

👉 ግብፆችን ወዳልተገባ አካሔድ የሚገፋቸው በአንድ በኩል ፍራቻ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ውሃውን ተጠቅማ ማደግ ከጀመረች ወደ ፊት የበላይነትን ትይዛለች ከሚል ስጋት እንጂ ሌላ ተጨባጭ ምክንያት የላቸውም፣

👉 ለሦስተኛ ጊዜ ውሃው የተሞላ ሲሆን፣ በሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ተጀምሯል፣

👉 ከሚመነጨው ኃይል ወደ ሱዳን ፣ ጅቡቲ እና ኬንያ በመሸጥ ላይ ነው፣

ሙሉ ቃለምልልሱን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100635
የሃስት ሰነዶችን ሲያዘጋጁ የነበሩ ወንጀል ፈጻሚዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
****************
(ኢ.ፕ.ድ)

ማህተሞችን በመጠቀም የሃስት ሰነዶች ሲያዘጋጁ የነበሩ ወንጀል ፈጻሚዎች የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ዘርፍና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጋራ ባደረጉት ክትትል በቁጥጥር ሥር ዋሉ።

አቶ አሻግሬ በለጠ አለሙ የተባለው ግለሰብና ግብረአበሮቹ በአራዳ ክፍለ ከተማ 511 ማህተሞችን በመጠቀም የሃሰት የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ሰነዶች ሲያዘጋጅ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

ከ1500 እስከ 4500 ብር በማስከፈል የሃስት ሰነዶችን በማዘጋጀት የወንጀል ተግባር ሲፈፅሙ እንደነበር ተገልጿል።

ወንጀል ፈጻሚው አቶ አሻግሬ በለጠ አለሙ እና ግብረአበሮቹ ሃስተኛ የሆኑ የመከላኪያ ሠራዊት የስንብት ወረቀት፣ የመከላከያ የፍቃድ ወረቀት፣ የብሔራዊ መረጃ መታወቂያ፣ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ፣ የመከላከያ ልዩ ዘመቻ ም/አዛዥ ሻ/ቃ፣ የመከላከያ ሠራዊት መታወቂያ አዘጋጅተው ተይዟል።

በተጨማሪም ግለሰቦቹ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የፌደራል አስተዳደር ፓሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዳይሬክቶሬት፣ የፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ፣ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ማዕከላዊ፣ 31ኛ ክፍለ ጦር መምሪያ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሉ የሃስት ሰነዶችን በማዘጋጀት ለወንጀል መፈጸሚያ እንዲውሉ ሲሰሩ እንደነበረ በኤግዚቢትነት የተያዙ ማስረጃዎች ያሳያሉ ሲል የአዲስ አበባ ኮምንኬሽን ቢሮ ዘግቧል።