Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተካሄደ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎችና ከተሞች ተካሂዷል።

ሰልፈኞቹ በኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ላይ የሚፈፀመውን ስም ማጥፋት በፅኑ በመቃወም ድጋፋቸውን ገልጸዋል።

ለመከላከያ ሠራዊቱ ያላቸውን ፍቅር እና አክብሮት የገለጹት ሰልፈኞቹ  “ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያዊያን ዋስትና በመሆኑ ሁሌም ከሠራዊታችን ጎን እንቆማለን” ሲሉ ድጋፋቸውን አሳይተዋል።

ጀግናው የመከላከያ ሠራዊትን የሚያጥላሉና የስም ማጥፋት የሚፈፅሙ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል።
የግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም የስራ ማስታወቂያ፣ መልካም ዕድል‼️
የኢትዮጵያ የወጪ ምርቶች መዳረሻቸውን በጓንዦ ከተማ እንዲያደርጉ ለኢትዮጵያ አምራቾች ጥሪ ቀረበ
*********************
(ኢ ፕ ድ)

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የጓንዦ ከተማን ከኢትዮጵያ ከተሞች ጋር ለማቀናጀት መንግስት ፍላጎት ያለው መሆኑንም ገልጸዋል።

በቻይና ጉብኝት እያደረጉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጓንዦ ከተማ ከንቲባ ጉዎ ዮንጋንግ ባደረጉላቸው የእንኳን ደህና መጡ ግብዣ ላይ እንደተናገሩት የህዝብ ለህዝብ ትስስሩ የበለጠ እንዲጠናከር በጓንዦና በኢትዮጵያ ከተሞች ማካከል ጉድኝት መፍጠር ጠቃሚ ነው ብለዋል፡፡

የጓንዦ ከተማ 16 ሚሊዬን ነዋሪ ያላት ስትሆን የቻይና የቢዝነስ መናኸሪያ የሆነው ጓንዶንግ ግዛት ዋና ከተማ ናት፡፡

የከተማው ከንቲባ የኢትዮጵያ የወጪ ምርቶች መዳረሻቸውን በጓንዦ እንዲያደርጉ ለኢትዮጵያ አምራቾች ጥሪ ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ጓንዦ በመብረር ሁለቱን አገሮች ብቻ ሳይሆን ቻይናና አፍሪካን አንዳስተሳሰረ ጠቅሰው በተለይም የኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት በጓንዦ የሚያደርገውን በረራ ባለማቋረጡ አመስግነዋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጓንዦ ቆይታቸው የኤሌክትሮኒክስ፣ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ እና ከሃይል ማመንጫ ጋር የተያያዙ ኩባንያዎችን በመጎብኘት በኢትዮጵያ እንዲሰማሩ ጋብዘዋል፡፡
#ኢፕድ

በስድስት ቋንቋዎች መረጃዎችን እያደረሰ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አሁን ደግሞ በአፋርኛ ቋንቋ እና በአፍ ሶማሌ ወደ እናንተ መረጃዎችን ማድረስ ጀምሯል።

በእነዚህ ቋንቋዎች ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የፌስቡክ ቻናሎቹ ይቀላቀላሉ፣ ላይክ፣ ፎሎ፣ ሼር ያድርጉ‼️

👉 https://www.facebook.com/profile.php?id=100092595632078

👉 https://www.facebook.com/profile.php?id=100092677890373&mibextid=ZbWKwL