በጣሊያን ሊጉሪያ፣ ቪያሌ ዲአወስታና ቱስካኒ ክልሎች የሚሸፍን የኢትዮጵያ የክብር ቆንስላ በጄኖአ ከተማ ተከፈተ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ከ150 በላይ የሚሆኑ ከሶስቱ ክልሎችና ከጄኖአ ከተማ የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ የጄኖአ ከተማ አስተዳደርና አመራሮች፣ ትላልቅ ባለሀብቶችና የጄኖአ ወደብ አመራሮችና ተቆጣጣሪዎች በተገኙበት በጄኖአ ከተማ ስለኢትዮጵያ አሁናዊ ጉዳዮችና የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄዷል።
በውይይቱ ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰላም ሁኔታና አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና በኢትዮጵያ ስላለው ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ውይይቱን የመሩት በጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ እና የክብር ቆንስል ሆነው የተሾሙት አቶ ጃንፔሮ ሱቺ ሲሆኑ፣ በመድረኩ የጣሊያን የውጭና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አምባሳደር ጂዩሴፔ ሚስትሬታ የክብር እንግዳ ሆነው ተገኝተዋል።
በመድረኩ በኢትዮጵያ በሎጂስቲክና ታዳሽ ኃይል ኢንቨስት እያደረጉ ያሉት ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ስላለው ሰላም አስተማማኝና ሰፊ ገበያ ያለ መሆኑን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የጣሊያን ንግድ ማህበር የሆነው Confindustria Assafrica ተወካዮች ማንኛውንም የኢንቨስትመንትና ንግድ እንቅስቃሴ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለማጠናከር የሚፈለግባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ከ150 በላይ የሚሆኑ ከሶስቱ ክልሎችና ከጄኖአ ከተማ የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ የጄኖአ ከተማ አስተዳደርና አመራሮች፣ ትላልቅ ባለሀብቶችና የጄኖአ ወደብ አመራሮችና ተቆጣጣሪዎች በተገኙበት በጄኖአ ከተማ ስለኢትዮጵያ አሁናዊ ጉዳዮችና የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄዷል።
በውይይቱ ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰላም ሁኔታና አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና በኢትዮጵያ ስላለው ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ውይይቱን የመሩት በጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ እና የክብር ቆንስል ሆነው የተሾሙት አቶ ጃንፔሮ ሱቺ ሲሆኑ፣ በመድረኩ የጣሊያን የውጭና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አምባሳደር ጂዩሴፔ ሚስትሬታ የክብር እንግዳ ሆነው ተገኝተዋል።
በመድረኩ በኢትዮጵያ በሎጂስቲክና ታዳሽ ኃይል ኢንቨስት እያደረጉ ያሉት ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ስላለው ሰላም አስተማማኝና ሰፊ ገበያ ያለ መሆኑን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የጣሊያን ንግድ ማህበር የሆነው Confindustria Assafrica ተወካዮች ማንኛውንም የኢንቨስትመንትና ንግድ እንቅስቃሴ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለማጠናከር የሚፈለግባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#የአፍሪካ ቀን‼️
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት የተመሠረተበት 60ኛ ዓመት በእስራኤል ተከበረ።
በእስራኤል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ተስፋዩ ይታይህ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንድነት ድርጅትና በአፍሪካ ህብረት ምስረታ ላይ የመሪነት ሚና እንደነበራት አስታወሰው አሁንም ለህብረቱ ግቦች መሳካት ለምታደርገው አስተዋጽኦ በሚመለከት ገለፃ አድርገዋል።
በዕለቱ ባህላዊ ምግብ፣ ሙዚቃና የሀገሪቱን መልካም ገፅታ የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ምስሎች ለእይታ ቀርበዋል። የተለያዩ የአፍሪካ አገራትም የየራሳቸውን የባሕል ምግብና ሙዚቃ ትርኢት ለታዳሚዎች አቅርበዋል።
ተቀማጭነታቸው በእስራኤል ያደረጉ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የእስራኤል የሠራተኛ ሚኒስትር፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ታላላቅ ኩባንያ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት የተመሠረተበት 60ኛ ዓመት በእስራኤል ተከበረ።
በእስራኤል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ተስፋዩ ይታይህ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንድነት ድርጅትና በአፍሪካ ህብረት ምስረታ ላይ የመሪነት ሚና እንደነበራት አስታወሰው አሁንም ለህብረቱ ግቦች መሳካት ለምታደርገው አስተዋጽኦ በሚመለከት ገለፃ አድርገዋል።
በዕለቱ ባህላዊ ምግብ፣ ሙዚቃና የሀገሪቱን መልካም ገፅታ የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ምስሎች ለእይታ ቀርበዋል። የተለያዩ የአፍሪካ አገራትም የየራሳቸውን የባሕል ምግብና ሙዚቃ ትርኢት ለታዳሚዎች አቅርበዋል።
ተቀማጭነታቸው በእስራኤል ያደረጉ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የእስራኤል የሠራተኛ ሚኒስትር፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ታላላቅ ኩባንያ አመራሮች ተሳትፈዋል።
በዓባይ ሃይቅ ላይ አሳ ማስገር ተጀምሯል
**************
(ኢ ፕ ድ)
በዓባይ ግድብ ሰው ሠራሽ ሐይቅ ላይ አሳ ማስገር መጀመሩንና በቀን በአማካኝ አሥራ ሁለት ኩንታል የዓሣ ምርት እየተገኘ መሆኑን የቤንሻንጉል ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ካሊፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ክልሉ በአንፃራዊነት ከሌሎች ክልሎች የተሻለ የዓሣ ምርት የሚገኝበት ነው። የክልሉ ነዋሪዎችም የዓሣ ምርቱን ለምግብነት ብቻ ሳይሆን ለገበያ በማዋል በገቢ ምንጭነት ይጠቀሙበታል።
የቤንሻንጉል ክልል የዓባይ ግድብ መገኛ መሆኑን ያወሱት ኃላፊው፤ አሁን ላይ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100852
**************
(ኢ ፕ ድ)
በዓባይ ግድብ ሰው ሠራሽ ሐይቅ ላይ አሳ ማስገር መጀመሩንና በቀን በአማካኝ አሥራ ሁለት ኩንታል የዓሣ ምርት እየተገኘ መሆኑን የቤንሻንጉል ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ካሊፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ክልሉ በአንፃራዊነት ከሌሎች ክልሎች የተሻለ የዓሣ ምርት የሚገኝበት ነው። የክልሉ ነዋሪዎችም የዓሣ ምርቱን ለምግብነት ብቻ ሳይሆን ለገበያ በማዋል በገቢ ምንጭነት ይጠቀሙበታል።
የቤንሻንጉል ክልል የዓባይ ግድብ መገኛ መሆኑን ያወሱት ኃላፊው፤ አሁን ላይ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100852
እንጀራ ከማጀት - ወደ ኢንዱስትሪ
****************
(ኢ ፕ ድ)
ለሚ የእንጀራ ማዕከል በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በተንጣለለ ሥፍራ ላይ በውስጣቸው በርካታ የእንጀራ መጋገሪያ ብሎኮችን ይዞ የተገነባ ማዕከል ነው፡፡ ብሎኮቹ እያንዳንዳቸው እስከ 250 የእንጀራ መጋገሪያ ምጣድ በውስጣቸው ይዘዋል፡፡
ይህ ማዕከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንጀራን ወደኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማስገባት ብሎም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማዋን ነዋሪዎች ለመደገፍ ከባለሃብቶች በማሰባሰብ የተገነባ ነው፡፡ ማዕከሉ በአሁኑ ወቅትም ሙሉ ለሙሉ ወደስራ ለመግባት ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የማዕከሉ ኃላፊዎች ይናገራሉ፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100887
****************
(ኢ ፕ ድ)
ለሚ የእንጀራ ማዕከል በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በተንጣለለ ሥፍራ ላይ በውስጣቸው በርካታ የእንጀራ መጋገሪያ ብሎኮችን ይዞ የተገነባ ማዕከል ነው፡፡ ብሎኮቹ እያንዳንዳቸው እስከ 250 የእንጀራ መጋገሪያ ምጣድ በውስጣቸው ይዘዋል፡፡
ይህ ማዕከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንጀራን ወደኢንዱስትሪ ዘርፍ ለማስገባት ብሎም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማዋን ነዋሪዎች ለመደገፍ ከባለሃብቶች በማሰባሰብ የተገነባ ነው፡፡ ማዕከሉ በአሁኑ ወቅትም ሙሉ ለሙሉ ወደስራ ለመግባት ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የማዕከሉ ኃላፊዎች ይናገራሉ፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100887
በቀጣዩ የመኸር ግብርና ከ508 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል
***********************
(ኢ ፕ ድ)
በአገር አቀፍ ደረጃ በ2015/16 የመኸር ምርት ዘመን ከ508 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በግብርና ሚኒስቴር የብርዕና አገዳ ሰብሎች ዴስክ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ቢረዳ እንደገለጹት፤ በፌዴራል ደረጃ በ2015/16 የመኸር ምርት ዘመን በክላስተርና በመደበኛ ግብርና ከሚሸፈነው 16 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ከ508 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል፡፡
እንደ አቶ ፍቃዱ ገለጻ፤ በዘንድሮው የመኸር ምርት ዘመን አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100850
***********************
(ኢ ፕ ድ)
በአገር አቀፍ ደረጃ በ2015/16 የመኸር ምርት ዘመን ከ508 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በግብርና ሚኒስቴር የብርዕና አገዳ ሰብሎች ዴስክ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ቢረዳ እንደገለጹት፤ በፌዴራል ደረጃ በ2015/16 የመኸር ምርት ዘመን በክላስተርና በመደበኛ ግብርና ከሚሸፈነው 16 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ከ508 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል፡፡
እንደ አቶ ፍቃዱ ገለጻ፤ በዘንድሮው የመኸር ምርት ዘመን አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100850
ኢትዮጵያ ከምስረታው ጀምሮ ለአፍሪካ ሕብረት መጠናከር የጎላ ሚና ተጫውታለች
****************************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ጀምሮ ለአፍሪካ ሕብረት መጠናከር የጎላ ሚና እንዳላት ምሁራን ተናገሩ፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር የሆኑት ዶክተር ሙሉጌታ ደበበ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከስልሳ አመት በፊት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና ከዚያ በኋላም የአፍሪካ ህብረት እውን እንዲሆን፤ እንዲሁም ለህብረቱ ቦታ በመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቷን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ በድርጅቱ ምስረታ ወቅት ቀደም ሲል ለፖሊስ አካዳሚ የተሰራውን....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100851
****************************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ጀምሮ ለአፍሪካ ሕብረት መጠናከር የጎላ ሚና እንዳላት ምሁራን ተናገሩ፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር የሆኑት ዶክተር ሙሉጌታ ደበበ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከስልሳ አመት በፊት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት እና ከዚያ በኋላም የአፍሪካ ህብረት እውን እንዲሆን፤ እንዲሁም ለህብረቱ ቦታ በመስጠት ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከቷን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ በድርጅቱ ምስረታ ወቅት ቀደም ሲል ለፖሊስ አካዳሚ የተሰራውን....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100851