አስተዳደራዊ በደልን ለመከላከል በተደረገ ቁጥጥር የሕግና አሠራር ክፍተቶች ተገኝተዋል
*****
(ኢ ፕ ድ)
አካል ጉዳተኞች እና ሴቶች ላይ የሚደርሰውን አስተዳደራዊ በደል ለመከላከል በተደረገ ጥናትና ቁጥጥር የተለያዩ የሕግና አሠራር ክፍተቶች መኖራቸውን የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ገለጸ።
ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ቆይታ ያደረጉት የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የሴቶች፣ ሕጻናት፣ የአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን ጉዳይ ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰብለወርቅ ታሪኩ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ የሴቶች እና አካል ጉዳተኞችን ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100796
*****
(ኢ ፕ ድ)
አካል ጉዳተኞች እና ሴቶች ላይ የሚደርሰውን አስተዳደራዊ በደል ለመከላከል በተደረገ ጥናትና ቁጥጥር የተለያዩ የሕግና አሠራር ክፍተቶች መኖራቸውን የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ገለጸ።
ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ቆይታ ያደረጉት የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም የሴቶች፣ ሕጻናት፣ የአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን ጉዳይ ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰብለወርቅ ታሪኩ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ የሴቶች እና አካል ጉዳተኞችን ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=100796
#ከአፕድ_ማህደር
ሚስቱን በሴንጢ የገደለው በስቅላት ተቀጣ
የቤት ክዳን ቆርቆሮ በመንኳኳቱ ምክንያት ጠብ ፈጥሮ በለጤ ገበየሁ የተባላች ሚስቱን በአውቶማቲክ ሴንጢ ወግቶ የገደለው በቀለ አረሩ፤ ወንጀሉን በፈፀመበት ቀበሌ በእቴጌ መስክ አቅራቢያ ከቀኑ በአምስት ሰዓት ላይ በስቅላት ተቀጣ፡፡
በቀለ አረሩ በለጤ ገበየሁ የተባለች ሚስቱን የገደለው ጥር 2 ቀን 1956 ዓ.ም ከቀኑ 11 ስዓት ላይ ሲሆን ለወንጀሉ አፈፃፀም መነሻ ያደረገው ከላይ በተጠቀሰው ቀን የቤት ክዳን ቆርቆሮ መንኳኳቱን ነበር፡፡
በዚሁ ጊዜ ቆርቆሮውን የመታሽው አንቺ ነሽ በማለት ስለተቆጣ ሟች ከፍርሃት የተነሳ ሸሽታ አቶ አለማየሁ የተባሉ ሰው ቤት ገብታ እንጀራ መጋጋሪያ ጓዲያ ውስጥ ተደበቀች፡፡ እርሱም ያለችበት ስፍራ ድረስ ተከታትሎ ሄዶ በአውቶማቲክ ሴንጢ ወግቶ ገደላት፡፡
ይህንን አሰቃቂ ወንጀል ከፈፀመ ብኋላ ለማምለጥ ሲሞክር በህዝብ እርዳታ ተከቦ ተያዘ ፡፡ ወዲያውም ክስ ቀርቦበት የፈፀመው ወንጀል በህግ ስለተረጋጋጠ የከፍተኛውና የጠቅላይ ንጉሰ ነገስት ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ በማለት የሰጡትን ፍርድ፤ ግርማዊ ንጉሰ ነገስት ስላፀኑበት ቅጣቱን በስቅላት የተቀበለ መሆኑ የፍርድ ሚኒስቴር የወንጀል ጉዳይ ፅሕፈት ቤት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ይህው ሰው ጥር 2 ቀን 1956 ዓ.ም ከላይ የተጠቀሰውን ወንጀል ከመፈፀሙ ሁለት ወር ያህል ቀደም ብሎ በጩቤ ወግቶ አቁስሏት እንደነበርና በዚያን ጊዜ የተለቀቀው እርሷ አልፈልገውም በማለቷ ምክንያት እንደነበር የፍርድ ወንጀለኛ ጉዳይ ፅ/ቤት በተጨማሪ አስረድቷል፡፡
መስከረም 9 ቀን 1963 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የታተመ
በሀይማኖት ከበደ
ሚስቱን በሴንጢ የገደለው በስቅላት ተቀጣ
የቤት ክዳን ቆርቆሮ በመንኳኳቱ ምክንያት ጠብ ፈጥሮ በለጤ ገበየሁ የተባላች ሚስቱን በአውቶማቲክ ሴንጢ ወግቶ የገደለው በቀለ አረሩ፤ ወንጀሉን በፈፀመበት ቀበሌ በእቴጌ መስክ አቅራቢያ ከቀኑ በአምስት ሰዓት ላይ በስቅላት ተቀጣ፡፡
በቀለ አረሩ በለጤ ገበየሁ የተባለች ሚስቱን የገደለው ጥር 2 ቀን 1956 ዓ.ም ከቀኑ 11 ስዓት ላይ ሲሆን ለወንጀሉ አፈፃፀም መነሻ ያደረገው ከላይ በተጠቀሰው ቀን የቤት ክዳን ቆርቆሮ መንኳኳቱን ነበር፡፡
በዚሁ ጊዜ ቆርቆሮውን የመታሽው አንቺ ነሽ በማለት ስለተቆጣ ሟች ከፍርሃት የተነሳ ሸሽታ አቶ አለማየሁ የተባሉ ሰው ቤት ገብታ እንጀራ መጋጋሪያ ጓዲያ ውስጥ ተደበቀች፡፡ እርሱም ያለችበት ስፍራ ድረስ ተከታትሎ ሄዶ በአውቶማቲክ ሴንጢ ወግቶ ገደላት፡፡
ይህንን አሰቃቂ ወንጀል ከፈፀመ ብኋላ ለማምለጥ ሲሞክር በህዝብ እርዳታ ተከቦ ተያዘ ፡፡ ወዲያውም ክስ ቀርቦበት የፈፀመው ወንጀል በህግ ስለተረጋጋጠ የከፍተኛውና የጠቅላይ ንጉሰ ነገስት ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ በማለት የሰጡትን ፍርድ፤ ግርማዊ ንጉሰ ነገስት ስላፀኑበት ቅጣቱን በስቅላት የተቀበለ መሆኑ የፍርድ ሚኒስቴር የወንጀል ጉዳይ ፅሕፈት ቤት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ይህው ሰው ጥር 2 ቀን 1956 ዓ.ም ከላይ የተጠቀሰውን ወንጀል ከመፈፀሙ ሁለት ወር ያህል ቀደም ብሎ በጩቤ ወግቶ አቁስሏት እንደነበርና በዚያን ጊዜ የተለቀቀው እርሷ አልፈልገውም በማለቷ ምክንያት እንደነበር የፍርድ ወንጀለኛ ጉዳይ ፅ/ቤት በተጨማሪ አስረድቷል፡፡
መስከረም 9 ቀን 1963 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የታተመ
በሀይማኖት ከበደ
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከአለም ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ
********************
(ኢ ፕ ድ)
በግብርናው ዘርፍ ላይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ ከአለም ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጋር በቅንጅት እየሰሩ እንደሚገኙ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከአለም ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጋር በተወያዩበት ወቅት ተናግረዋል፡፡
በውይይታቸው በአየር ንብረት ለውጥ፣ በምግብና የምግብ ደህንነት፣ በአፈር ጤንነትና በውሃ ሃብት አያያዝና አጠቃቀም፣ በግሉ ዘርፍ የኢንቨስትመንት ስራዎች፣ የገጠር የፋይናንስ አቅርቦትና አገልግሎትን ወደ አርሶና አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ተደራሽ የማድረግ ስራዎች ላይ በስፋት ተወያይተዋል፡፡
በባንኩ የገንዘብ ድጋፍ በግብርናው ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ፕሮጀክትና ፕሮግራሞች ላይ በሚሰሩት ስራ ላይ ተወያይተዋል፡፡
********************
(ኢ ፕ ድ)
በግብርናው ዘርፍ ላይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ ከአለም ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጋር በቅንጅት እየሰሩ እንደሚገኙ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ከአለም ባንክ የስራ ኃላፊዎች ጋር በተወያዩበት ወቅት ተናግረዋል፡፡
በውይይታቸው በአየር ንብረት ለውጥ፣ በምግብና የምግብ ደህንነት፣ በአፈር ጤንነትና በውሃ ሃብት አያያዝና አጠቃቀም፣ በግሉ ዘርፍ የኢንቨስትመንት ስራዎች፣ የገጠር የፋይናንስ አቅርቦትና አገልግሎትን ወደ አርሶና አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ ተደራሽ የማድረግ ስራዎች ላይ በስፋት ተወያይተዋል፡፡
በባንኩ የገንዘብ ድጋፍ በግብርናው ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ፕሮጀክትና ፕሮግራሞች ላይ በሚሰሩት ስራ ላይ ተወያይተዋል፡፡
በጣሊያን ሊጉሪያ፣ ቪያሌ ዲአወስታና ቱስካኒ ክልሎች የሚሸፍን የኢትዮጵያ የክብር ቆንስላ በጄኖአ ከተማ ተከፈተ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ከ150 በላይ የሚሆኑ ከሶስቱ ክልሎችና ከጄኖአ ከተማ የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ የጄኖአ ከተማ አስተዳደርና አመራሮች፣ ትላልቅ ባለሀብቶችና የጄኖአ ወደብ አመራሮችና ተቆጣጣሪዎች በተገኙበት በጄኖአ ከተማ ስለኢትዮጵያ አሁናዊ ጉዳዮችና የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄዷል።
በውይይቱ ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰላም ሁኔታና አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና በኢትዮጵያ ስላለው ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ውይይቱን የመሩት በጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ እና የክብር ቆንስል ሆነው የተሾሙት አቶ ጃንፔሮ ሱቺ ሲሆኑ፣ በመድረኩ የጣሊያን የውጭና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አምባሳደር ጂዩሴፔ ሚስትሬታ የክብር እንግዳ ሆነው ተገኝተዋል።
በመድረኩ በኢትዮጵያ በሎጂስቲክና ታዳሽ ኃይል ኢንቨስት እያደረጉ ያሉት ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ስላለው ሰላም አስተማማኝና ሰፊ ገበያ ያለ መሆኑን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የጣሊያን ንግድ ማህበር የሆነው Confindustria Assafrica ተወካዮች ማንኛውንም የኢንቨስትመንትና ንግድ እንቅስቃሴ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለማጠናከር የሚፈለግባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ከ150 በላይ የሚሆኑ ከሶስቱ ክልሎችና ከጄኖአ ከተማ የተውጣጡ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩንቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ የጄኖአ ከተማ አስተዳደርና አመራሮች፣ ትላልቅ ባለሀብቶችና የጄኖአ ወደብ አመራሮችና ተቆጣጣሪዎች በተገኙበት በጄኖአ ከተማ ስለኢትዮጵያ አሁናዊ ጉዳዮችና የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሄዷል።
በውይይቱ ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰላም ሁኔታና አዲሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና በኢትዮጵያ ስላለው ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ውይይቱን የመሩት በጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ እና የክብር ቆንስል ሆነው የተሾሙት አቶ ጃንፔሮ ሱቺ ሲሆኑ፣ በመድረኩ የጣሊያን የውጭና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አምባሳደር ጂዩሴፔ ሚስትሬታ የክብር እንግዳ ሆነው ተገኝተዋል።
በመድረኩ በኢትዮጵያ በሎጂስቲክና ታዳሽ ኃይል ኢንቨስት እያደረጉ ያሉት ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ስላለው ሰላም አስተማማኝና ሰፊ ገበያ ያለ መሆኑን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የጣሊያን ንግድ ማህበር የሆነው Confindustria Assafrica ተወካዮች ማንኛውንም የኢንቨስትመንትና ንግድ እንቅስቃሴ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለማጠናከር የሚፈለግባቸውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#የአፍሪካ ቀን‼️
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት የተመሠረተበት 60ኛ ዓመት በእስራኤል ተከበረ።
በእስራኤል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ተስፋዩ ይታይህ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንድነት ድርጅትና በአፍሪካ ህብረት ምስረታ ላይ የመሪነት ሚና እንደነበራት አስታወሰው አሁንም ለህብረቱ ግቦች መሳካት ለምታደርገው አስተዋጽኦ በሚመለከት ገለፃ አድርገዋል።
በዕለቱ ባህላዊ ምግብ፣ ሙዚቃና የሀገሪቱን መልካም ገፅታ የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ምስሎች ለእይታ ቀርበዋል። የተለያዩ የአፍሪካ አገራትም የየራሳቸውን የባሕል ምግብና ሙዚቃ ትርኢት ለታዳሚዎች አቅርበዋል።
ተቀማጭነታቸው በእስራኤል ያደረጉ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የእስራኤል የሠራተኛ ሚኒስትር፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ታላላቅ ኩባንያ አመራሮች ተሳትፈዋል።
የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት የተመሠረተበት 60ኛ ዓመት በእስራኤል ተከበረ።
በእስራኤል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ተስፋዩ ይታይህ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንድነት ድርጅትና በአፍሪካ ህብረት ምስረታ ላይ የመሪነት ሚና እንደነበራት አስታወሰው አሁንም ለህብረቱ ግቦች መሳካት ለምታደርገው አስተዋጽኦ በሚመለከት ገለፃ አድርገዋል።
በዕለቱ ባህላዊ ምግብ፣ ሙዚቃና የሀገሪቱን መልካም ገፅታ የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ምስሎች ለእይታ ቀርበዋል። የተለያዩ የአፍሪካ አገራትም የየራሳቸውን የባሕል ምግብና ሙዚቃ ትርኢት ለታዳሚዎች አቅርበዋል።
ተቀማጭነታቸው በእስራኤል ያደረጉ የአፍሪካ አገራት አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ የእስራኤል የሠራተኛ ሚኒስትር፣ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ታላላቅ ኩባንያ አመራሮች ተሳትፈዋል።