የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ መልእክት‼️
በሰሞኑ ዝናብ ቦረና ላይ በስፋት የእንስሳት መኖ እና ሰሊጥ ተመርቷል። ዓመት ባልሞላ ጊዜ ከድርቅ ወደ አምራችነት መቀየሩ ተስፋ ሰጪ ነው። ውኃን በማቆርና በመቆጠብ ብልሐት ከተጠቀምን የችግርን ጊዜ ሳንቸገርበት እናልፈዋለን።
በሰሞኑ ዝናብ ቦረና ላይ በስፋት የእንስሳት መኖ እና ሰሊጥ ተመርቷል። ዓመት ባልሞላ ጊዜ ከድርቅ ወደ አምራችነት መቀየሩ ተስፋ ሰጪ ነው። ውኃን በማቆርና በመቆጠብ ብልሐት ከተጠቀምን የችግርን ጊዜ ሳንቸገርበት እናልፈዋለን።
አገልግሎቱ ለእጀባ፣ ለበረራ ደኅንነት መኮንኖችና አመራሮች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን አስመረቀ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለሪፐብሊካን ጋርድና ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ እጀባ ፣ለበረራ ደኅንነት መኮንኖችና አመራሮች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን አስመርቋል።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢፕድ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፥ በትብብርና በአጋርነት አብረውት ከሚሰሩ የውጭ መረጃና ደኅንነት ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ስልጠና በዋናነት በቪ አይ ፒ ደኅንነት ጥበቃ፣ በፈንጂ ምህንድስና ፣ በድሮን አጠቃቀም ቅየሳና የአደጋ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፥ አደጋ መቼና እንዴት እንደሚከሰት በእርገጠኝነት መናገር ባይቻልም በማያቋርጥ ስልጠናና ልምምድ ብቁና ሁልጊዜም ዝግጁ ሆኖ መገኘት አስፈላጊ በመሆኑ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ይህ አይነቱን ስልጠና አዘጋጅቷል።
በመሆኑም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሀገር መሪዎችን ፣ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከአደጋ የመጠበቅ እንዲሁም የበረራ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮዎችን ለመፈጸም የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠና እንደሚያጠናክር ተናግረዋል።
ሰልጣኞችም በስልጠና ወቅት በንድፈ ሃሳብ፡ በተግባርና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠና ማግኘታቸው ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬታማ አፈፃፀም ወሳኝ መሆኑን ነው የተናገሩት።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዚዳንት አቶ ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው የቪ አይ ፒ ደኅንነት ጥበቃ መኮንኖች ከፍተኛ ደኅንነታዊ አንድምታ ያላቸውን ግለሰቦች ደኅንነት ለመጠበቅ ተገቢውን ዕውቀት፣ ክህሎት፣ አስተሳሰብ እና ስነምግባር ሊጨብጡ ይገባል ብለዋል።
እያንዳንዱ የቪ አይ ፒ ደኅንነት ጥበቃ ስምሪት ሊያጋጥሙ ከሚችሉ እንዲሁም ከሚገመቱና ካልተጠበቁ ስጋቶች እና ጥቃቶች የሀገር መሪዎችን፣ ቁልፍ የመሰረት ልማት ተቋማትን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የተሟላ ዕቅድ አዘጋጅቶ የመሰማራት ባህልን ማዳበር እንደሚገባም ገልፀዋል።
በብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በንደፈ-ሃሳብና በተግባር የተሰጠውን ስልጠና የተከታተሉ ሰልጣኞችም በስልጠና ያገኟቸውን ዕውቀትና ክህሎቶች በተግባር ልምምድ ማሳየታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መረጃ አመላክቷል።
*************************
(ኢ ፕ ድ)
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለሪፐብሊካን ጋርድና ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ እጀባ ፣ለበረራ ደኅንነት መኮንኖችና አመራሮች ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን አስመርቋል።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢፕድ በላከው መረጃ እንዳመለከተው፥ በትብብርና በአጋርነት አብረውት ከሚሰሩ የውጭ መረጃና ደኅንነት ተቋማት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ስልጠና በዋናነት በቪ አይ ፒ ደኅንነት ጥበቃ፣ በፈንጂ ምህንድስና ፣ በድሮን አጠቃቀም ቅየሳና የአደጋ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሲሳይ ቶላ በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት፥ አደጋ መቼና እንዴት እንደሚከሰት በእርገጠኝነት መናገር ባይቻልም በማያቋርጥ ስልጠናና ልምምድ ብቁና ሁልጊዜም ዝግጁ ሆኖ መገኘት አስፈላጊ በመሆኑ አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ይህ አይነቱን ስልጠና አዘጋጅቷል።
በመሆኑም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የሀገር መሪዎችን ፣ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከአደጋ የመጠበቅ እንዲሁም የበረራ ደኅንነትን የማረጋገጥ ተልዕኮዎችን ለመፈጸም የሰው ኃይሉን በተከታታይ ስልጠና እንደሚያጠናክር ተናግረዋል።
ሰልጣኞችም በስልጠና ወቅት በንድፈ ሃሳብ፡ በተግባርና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስልጠና ማግኘታቸው ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬታማ አፈፃፀም ወሳኝ መሆኑን ነው የተናገሩት።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዚዳንት አቶ ወንድወሰን ካሳ በበኩላቸው የቪ አይ ፒ ደኅንነት ጥበቃ መኮንኖች ከፍተኛ ደኅንነታዊ አንድምታ ያላቸውን ግለሰቦች ደኅንነት ለመጠበቅ ተገቢውን ዕውቀት፣ ክህሎት፣ አስተሳሰብ እና ስነምግባር ሊጨብጡ ይገባል ብለዋል።
እያንዳንዱ የቪ አይ ፒ ደኅንነት ጥበቃ ስምሪት ሊያጋጥሙ ከሚችሉ እንዲሁም ከሚገመቱና ካልተጠበቁ ስጋቶች እና ጥቃቶች የሀገር መሪዎችን፣ ቁልፍ የመሰረት ልማት ተቋማትን በብቃት ለመከላከል የሚያስችል የተሟላ ዕቅድ አዘጋጅቶ የመሰማራት ባህልን ማዳበር እንደሚገባም ገልፀዋል።
በብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በንደፈ-ሃሳብና በተግባር የተሰጠውን ስልጠና የተከታተሉ ሰልጣኞችም በስልጠና ያገኟቸውን ዕውቀትና ክህሎቶች በተግባር ልምምድ ማሳየታቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መረጃ አመላክቷል።
“ቦረና ዓመት ባልሞላ ጊዜ ከድርቅ ወደአምራችነት መቀየሩ ተስፋ ሰጪ ነው”- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ
***************************
(ኢ ፕ ድ)
ለአምስት ዓመታት ዝናብ ባለመዝነቡ በድርቅ ተጎድቶ የነበረው የቦረና ዞን ዓመት ባልሞላ ጊዜ ከድርቅ ወደ አምራችነት መቀየሩ ተስፋ ሰጪ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።
በቅርቡ የዘነበውን ዝናብ ተከትሎ 96 ሺህ 189 ሄክታር መሬት በሰብል መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት እንደገለጹት፤ በሰሞኑ ዝናብ ቦረና ላይ በስፋት የእንስሳት መኖ እና ሰሊጥ ተመርቷል። ውሃን በማቆርና በመቆጠብ ብልሐት ከተጠቀምን የችግርን ጊዜ ሳንቸገርበት እናልፈዋለን።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=101037
***************************
(ኢ ፕ ድ)
ለአምስት ዓመታት ዝናብ ባለመዝነቡ በድርቅ ተጎድቶ የነበረው የቦረና ዞን ዓመት ባልሞላ ጊዜ ከድርቅ ወደ አምራችነት መቀየሩ ተስፋ ሰጪ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።
በቅርቡ የዘነበውን ዝናብ ተከትሎ 96 ሺህ 189 ሄክታር መሬት በሰብል መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት እንደገለጹት፤ በሰሞኑ ዝናብ ቦረና ላይ በስፋት የእንስሳት መኖ እና ሰሊጥ ተመርቷል። ውሃን በማቆርና በመቆጠብ ብልሐት ከተጠቀምን የችግርን ጊዜ ሳንቸገርበት እናልፈዋለን።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=101037
የቦሌ ሚካኤል ተሸጋጋሪ ድልድይ ግንባታ አሁናዊ ሁኔታ‼️
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን የከተማዋን የትራፊክ ፍሰት የሚያሻሽሉ 6 የትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድዮችን በተለያዩ አካባቢዎች በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ የቦሌ ሚካኤል የመንገድ መጋጠሚያ አንዱ ነው፡፡
የቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ከተገነቡ አዳዲስ መንገዶች ጋር ተሳስሮ ከሳሪስ አቦ ወደ ቦሌ አቅጣጫ ከሚወስደው የቀለበት መንገድ ጋር በተለያዩ መጋጠሚያዎች የሚያገናኙ የመቃረቢያ መንገዶችን ጨምሮ የቦሌ ሚካኤል የትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድይ ፕሮጀክት ግንባታ እውን እንዲሆን ምክንያት ሆኗል፡፡
ፕሮጅክቱ ከ720 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ አሰር ኮንስትራክሽን የተባለ የሀገር ውስጥ የሥራ ተቋራጭ እየገነባው የሚገኝ ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ በሀይ ዌይ ኢንጂነርስ አማካሪ ኩባንያ እየተሰራ ይገኛል፡፡
ቀደም ሲል 600 ሜትር ርዝመት ያለው የቦሌ ሚካኤል ትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድይ ግንባታ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት የተደረገ ሲሆን፣ ከአጠቃላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ ክፍል 3.8 ኪሎ ሜትሩ የመጀመርያ አስፋልት ደረጃ ለብሷል።
በተጨማሪ በቀሪው 200 ሜትር በሚሆነው የመንገዱ ክፍል የአስፋልት ንጣፍ ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን የከተማዋን የትራፊክ ፍሰት የሚያሻሽሉ 6 የትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድዮችን በተለያዩ አካባቢዎች በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ የቦሌ ሚካኤል የመንገድ መጋጠሚያ አንዱ ነው፡፡
የቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ከተገነቡ አዳዲስ መንገዶች ጋር ተሳስሮ ከሳሪስ አቦ ወደ ቦሌ አቅጣጫ ከሚወስደው የቀለበት መንገድ ጋር በተለያዩ መጋጠሚያዎች የሚያገናኙ የመቃረቢያ መንገዶችን ጨምሮ የቦሌ ሚካኤል የትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድይ ፕሮጀክት ግንባታ እውን እንዲሆን ምክንያት ሆኗል፡፡
ፕሮጅክቱ ከ720 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ አሰር ኮንስትራክሽን የተባለ የሀገር ውስጥ የሥራ ተቋራጭ እየገነባው የሚገኝ ሲሆን፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ በሀይ ዌይ ኢንጂነርስ አማካሪ ኩባንያ እየተሰራ ይገኛል፡፡
ቀደም ሲል 600 ሜትር ርዝመት ያለው የቦሌ ሚካኤል ትራፊክ ማሳለጫ ተሸጋጋሪ ድልድይ ግንባታ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት የተደረገ ሲሆን፣ ከአጠቃላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ ክፍል 3.8 ኪሎ ሜትሩ የመጀመርያ አስፋልት ደረጃ ለብሷል።
በተጨማሪ በቀሪው 200 ሜትር በሚሆነው የመንገዱ ክፍል የአስፋልት ንጣፍ ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
በድሬዳዋ በመጪው ክረምት ሁለት ሚሊዮን ችግኞች ይተከላሉ
**************
(ኢ ፕ ድ)
በመጪው ክረምት ሁለት ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የአካባቢ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡
የባለሥልጣኑ የደን ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ማስረሻ ይመር ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ከ10 በላይ የችግኝ ጣቢያዎች የችግኝ ተከላ ዝግጅት እየተከናወነ ይገኛል።
ከሚተከሉት ሁለት ሚሊዮን ችግኞች መካከል ከ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ዝግጁ ተደርገዋል፡፡ በቀሪ ጊዜያት በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የተለያዩ የዛፍ ችግኞች ይዘጋጃሉ ብለዋል፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=101062
#የሐላላ ኬላ ሪዞርት‼️
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ’ገበታ ለሀገር’ ፕሮጄክት አካል የሆነውና በኮይሻ ፕሮጄክት ክላስተር ሥር የለማውን የሐላላ ኬላ ሪዞርትን ዛሬ በይፋ ተረክቧል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የ’ገበታ ለ ሀገር’ ፕሮጄክት አካል የሆነው እና በኮይሻ ፕሮጄክት ክላስተር ሥር የለማውን የሐላላ ኬላ ሪዞርት፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዛሬ መረከቡን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አሰታውቋል።
ሪዞርቱን ‘ሐላላ ኬላ ሪዞርት’ በሚል ስያሜ ለማስተዳደር የክልሉ መንግሥት ከፓራዳይዝ ሎጆች፤ ሪዞርቶችና ሆቴሎች ማኔጅመንት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር ስምምነት አድርጓል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ’ገበታ ለሀገር’ ፕሮጄክት አካል የሆነውና በኮይሻ ፕሮጄክት ክላስተር ሥር የለማውን የሐላላ ኬላ ሪዞርትን ዛሬ በይፋ ተረክቧል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የ’ገበታ ለ ሀገር’ ፕሮጄክት አካል የሆነው እና በኮይሻ ፕሮጄክት ክላስተር ሥር የለማውን የሐላላ ኬላ ሪዞርት፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ዛሬ መረከቡን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አሰታውቋል።
ሪዞርቱን ‘ሐላላ ኬላ ሪዞርት’ በሚል ስያሜ ለማስተዳደር የክልሉ መንግሥት ከፓራዳይዝ ሎጆች፤ ሪዞርቶችና ሆቴሎች ማኔጅመንት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር ስምምነት አድርጓል።