በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ዙሪያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ውይይት በሐምሌ ወር ይጠናቀቃል
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
👉ውይይቱ በሁሉም ክልሎች ይካሄዳል
👉መስከረም ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይቀርባል
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ዙሪያ እየተካሄደ ያለው ግብዓትን የማሰባሰብ ሃገራዊ ውይይት እስከ መጪው ሐምሌ ወር 2015ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ውይይቱ በሁሉም ክልሎች እንደሚካሄድና መስከረም ወር ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆን ተገልጿል::
በፍትህ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አወል ሱልጣን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲን ለማውጣት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=102817
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
👉ውይይቱ በሁሉም ክልሎች ይካሄዳል
👉መስከረም ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይቀርባል
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ዙሪያ እየተካሄደ ያለው ግብዓትን የማሰባሰብ ሃገራዊ ውይይት እስከ መጪው ሐምሌ ወር 2015ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ውይይቱ በሁሉም ክልሎች እንደሚካሄድና መስከረም ወር ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆን ተገልጿል::
በፍትህ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አወል ሱልጣን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲን ለማውጣት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=102817
በአዲስ አበባ ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሃ- ግብር እየተካሄደ ነው
****
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
በማስጀመሪያ መርሃ- ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፤ የሚተከሉት ችግኞች ዓለምን በከፍተኛ ደረጃ እያስጨነቀ ያለው የአየር ንብረት ለውጥ ለማስቀረትና እራስን በምግብ ለማስቻል ነው ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት በከተማ አስተዳደሩ ከ 41 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መትከል ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ በዘንድሮ ክረምት እስከ 17 ሚሊየን ችግኞች እንደሚተከሉ ተናግረዋል፡፡
ከንቲባዋ አክለውም የሐይማኖት ተቋማት ከላቸው ሰፊ ቦታ አኳያ ግንባር ቀደም በመሆን ችግኞች እንዲያስተክሉ ለሐይማኖት አባቶች ጥሪ አድርገዋል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው ሀገራት የሚያደርጉት ልማት ዘላቂ ከሚሆኑባቸው አብይ ጉዳዮች መካከል አካባቢን ያልበከለና ጽድ አካባቢ መፍጠር ነው ብለዋል፡፡
የሀገሪቱ በጣም ዝቅተኛ ከነበረበት የደን ሽፋን በመነሳት በሀገር አቀፍ ደረጃ 17 በመቶ መድረሱን የጠቀሙት ሚኒስትሩ፤ በዘንድሮ እንደሀገር ከስድስት ቢሊየን በላይ ችግኝ እንደሚተከል ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብርሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፣ የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ፣ የፌደራልና የከተማው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሐይማኖት አባቶች እንዲሁም በሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
እንደ አዲስ አበባ ከተማ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ካራ የተካሄደ ሲሆን፤ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል፡፡
<<ነገን ዛሬ እንትከል>> በሚል መሪ ሃሳብ የሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ መጀመሩ የሚታወስ ነው፡፡
በልጅዓለም ፍቅሬ
****
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
በማስጀመሪያ መርሃ- ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፤ የሚተከሉት ችግኞች ዓለምን በከፍተኛ ደረጃ እያስጨነቀ ያለው የአየር ንብረት ለውጥ ለማስቀረትና እራስን በምግብ ለማስቻል ነው ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት በከተማ አስተዳደሩ ከ 41 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መትከል ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ በዘንድሮ ክረምት እስከ 17 ሚሊየን ችግኞች እንደሚተከሉ ተናግረዋል፡፡
ከንቲባዋ አክለውም የሐይማኖት ተቋማት ከላቸው ሰፊ ቦታ አኳያ ግንባር ቀደም በመሆን ችግኞች እንዲያስተክሉ ለሐይማኖት አባቶች ጥሪ አድርገዋል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው ሀገራት የሚያደርጉት ልማት ዘላቂ ከሚሆኑባቸው አብይ ጉዳዮች መካከል አካባቢን ያልበከለና ጽድ አካባቢ መፍጠር ነው ብለዋል፡፡
የሀገሪቱ በጣም ዝቅተኛ ከነበረበት የደን ሽፋን በመነሳት በሀገር አቀፍ ደረጃ 17 በመቶ መድረሱን የጠቀሙት ሚኒስትሩ፤ በዘንድሮ እንደሀገር ከስድስት ቢሊየን በላይ ችግኝ እንደሚተከል ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብርሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፣ የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ፣ የፌደራልና የከተማው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሐይማኖት አባቶች እንዲሁም በሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
እንደ አዲስ አበባ ከተማ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ካራ የተካሄደ ሲሆን፤ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል፡፡
<<ነገን ዛሬ እንትከል>> በሚል መሪ ሃሳብ የሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ መጀመሩ የሚታወስ ነው፡፡
በልጅዓለም ፍቅሬ
የአፍሪካ ህጻናት ቀን በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በኢትዮጵያ ለ32ኛ ጊዜ "ሰላም፣ ፍቅር፣ እንክብካቤና ጥበቃ ለሁሉም ህፃናት" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
በበዓል አከባበር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬን ጨምሮ የፓርላማ ተወካዮች፣ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የህጻናት ፓርላማ ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ተገኝተዋል።
በዓሉ በማርሽ ባንድ አዝናኝ ትርዒቶች የተጀመረ ሲሆን ዕለቱን የተመለከቱ ጠቃሚ መልዕክቶችም በተለያዩ አካላት እየተላለፉ ይገኛል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በአፍሪካ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ የአፍሪካ ህብረት በወሰነው መሰረት "The Rights of Child in the Digital Environment" በሚል አህጉራዊ መሪ ቃል ይከበራል።
ሀገራት ህጻናትና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደህንነትን በተመለከተ በአፍሪካ የህጻናት መብቶችና ደህንነቶች ቻርተር ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎችን፣ ሌሎች ህጋዊ የአሰራር ማዕቀፎችን እና ሌሎች የአህጉሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ቀኑን አስበው መዋላቸውን ከሴቶች እና ማኅበራዊ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በኢትዮጵያ ለ32ኛ ጊዜ "ሰላም፣ ፍቅር፣ እንክብካቤና ጥበቃ ለሁሉም ህፃናት" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
በበዓል አከባበር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬን ጨምሮ የፓርላማ ተወካዮች፣ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የህጻናት ፓርላማ ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ተገኝተዋል።
በዓሉ በማርሽ ባንድ አዝናኝ ትርዒቶች የተጀመረ ሲሆን ዕለቱን የተመለከቱ ጠቃሚ መልዕክቶችም በተለያዩ አካላት እየተላለፉ ይገኛል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በአፍሪካ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ የአፍሪካ ህብረት በወሰነው መሰረት "The Rights of Child in the Digital Environment" በሚል አህጉራዊ መሪ ቃል ይከበራል።
ሀገራት ህጻናትና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደህንነትን በተመለከተ በአፍሪካ የህጻናት መብቶችና ደህንነቶች ቻርተር ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎችን፣ ሌሎች ህጋዊ የአሰራር ማዕቀፎችን እና ሌሎች የአህጉሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ቀኑን አስበው መዋላቸውን ከሴቶች እና ማኅበራዊ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።