ከ141 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
**********
(ኢ ፕ ድ)
የጉምሩክ ኮሚሽን ከሰኔ 2 እስከ 8/ 2015 ባደረገው ክትትል 76 ሚሊዮን የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ የወጭ፤ በድምሩ 141 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡
በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር የላቀ አፈጻጸም የተመዘገበ ሲሆን በዚህም ጅግጅጋ ፣ ሞያሌ እና አዋሽ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች በቅደም ተከተላቸው 21 ሚሊዮን፣ 18 ሚሊዮን እና 11 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎችን በመያዝ ከፍተኛውን ድርሻ ወስደዋል፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በበረራና በጥቆማ የተያዙ ሲሆን የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋዉሩ የተገኙ ስድስት ግለሰቦች እና አራት ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ የኮሚሽኑ ሰራተኞች ፣ የክልልና የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም ለመላው ህዝባችን ምስጋናውን ያደርሳል፡፡
የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡
**********
(ኢ ፕ ድ)
የጉምሩክ ኮሚሽን ከሰኔ 2 እስከ 8/ 2015 ባደረገው ክትትል 76 ሚሊዮን የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና ከ64 ሚሊዮን ብር በላይ የወጭ፤ በድምሩ 141 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡
በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር የላቀ አፈጻጸም የተመዘገበ ሲሆን በዚህም ጅግጅጋ ፣ ሞያሌ እና አዋሽ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች በቅደም ተከተላቸው 21 ሚሊዮን፣ 18 ሚሊዮን እና 11 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎችን በመያዝ ከፍተኛውን ድርሻ ወስደዋል፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በበረራና በጥቆማ የተያዙ ሲሆን የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋዉሩ የተገኙ ስድስት ግለሰቦች እና አራት ተሽከርካሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ የኮሚሽኑ ሰራተኞች ፣ የክልልና የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም ለመላው ህዝባችን ምስጋናውን ያደርሳል፡፡
የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡
መንግሥት የቴሌኮም ዘርፉን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረጉ የዘርፉን እድገት ለማስቀጠል ይረዳል
- የቴሌኮም ዘርፍ አማካሪ ሚሼል ጉንታ
********
(ኢ ፕ ድ)
መንግሥት የቴሌኮም ዘርፉን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረጉ የዘርፉን እድገት ለማስቀጠልና የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የቴሌኮም ዘርፍ አማካሪው ሚሼል ጉንታ ገለጹ።
አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በመንግሥት ብቻ ሲቀርብ የነበረውን አገልግሎት ለዓለም አቀፍ አገልግሎት አቅራቢዎች ክፍት መደረጉ ይታወሳል።
በዚህም ነባሩ አገልግሎት ሰጪ ኢትዮ-ቴሌኮምን ጨምሮ ሁለት አዳዲስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲኖሩ አቅጣጫ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
ይህንንም ተከትሎ መንግሥት ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቀጥሎ ሁለተኛውን አዲስ የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመሥጠት ዝግጅት እያደረገ ነው።
ይህም የመንግሥት ውሳኔ የሚደነቅና ለዘርፉ እድገት በርካታ ጥቅሞች ይዞ እየመጣ መሆኑን ነው የዘርፉ አማካሪ ሚሼል ጉንታ ለኢዜአ የገለጹት።
ይህ ለኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተሞክሮን በማጋራት አዳዲስ ቴክኖሎጂ በማስረጽ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን እድልና ተስፋ ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
ያም ብቻ ሳይሆን በአገሪቱ ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል በኩባንያዎች መካከል ውድድር እንዲዳብር ያስችላልም ነው ያሉት። ይህም ደግሞ የቴሌኮም ዘርፍ ተደራሽነትን ለማስፋት እንደሚያስችል በመጠቆም።
ኢትዮጵያ አሁን እያደረገች ያለው የዲጂታል ሥርዓት ግንባታና የቴሌኮም ዘርፍ እንቅስቃሴ በአፍሪካ ወደ ላቀ ደረጃ የሚወስዳት መሆኑንም እምነታቸውን ገልጸዋል።
እንዲያም ሆኖ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ ይበልጥ በማጠናከር የዘርፉን እድገት ማስቀጠል እንደሚገባ ምከረ ኃሳብ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለሥልጣን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቀጥሎ ሁለተኛውን አዲስ የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት በያዝነው ሰኔ ወር ጨረታ እንደሚወጣ መግለጹ ይታወሳል።
- የቴሌኮም ዘርፍ አማካሪ ሚሼል ጉንታ
********
(ኢ ፕ ድ)
መንግሥት የቴሌኮም ዘርፉን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረጉ የዘርፉን እድገት ለማስቀጠልና የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማስፋት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የቴሌኮም ዘርፍ አማካሪው ሚሼል ጉንታ ገለጹ።
አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በመንግሥት ብቻ ሲቀርብ የነበረውን አገልግሎት ለዓለም አቀፍ አገልግሎት አቅራቢዎች ክፍት መደረጉ ይታወሳል።
በዚህም ነባሩ አገልግሎት ሰጪ ኢትዮ-ቴሌኮምን ጨምሮ ሁለት አዳዲስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲኖሩ አቅጣጫ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
ይህንንም ተከትሎ መንግሥት ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቀጥሎ ሁለተኛውን አዲስ የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመሥጠት ዝግጅት እያደረገ ነው።
ይህም የመንግሥት ውሳኔ የሚደነቅና ለዘርፉ እድገት በርካታ ጥቅሞች ይዞ እየመጣ መሆኑን ነው የዘርፉ አማካሪ ሚሼል ጉንታ ለኢዜአ የገለጹት።
ይህ ለኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ተሞክሮን በማጋራት አዳዲስ ቴክኖሎጂ በማስረጽ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን እድልና ተስፋ ከፍ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
ያም ብቻ ሳይሆን በአገሪቱ ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል በኩባንያዎች መካከል ውድድር እንዲዳብር ያስችላልም ነው ያሉት። ይህም ደግሞ የቴሌኮም ዘርፍ ተደራሽነትን ለማስፋት እንደሚያስችል በመጠቆም።
ኢትዮጵያ አሁን እያደረገች ያለው የዲጂታል ሥርዓት ግንባታና የቴሌኮም ዘርፍ እንቅስቃሴ በአፍሪካ ወደ ላቀ ደረጃ የሚወስዳት መሆኑንም እምነታቸውን ገልጸዋል።
እንዲያም ሆኖ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ ይበልጥ በማጠናከር የዘርፉን እድገት ማስቀጠል እንደሚገባ ምከረ ኃሳብ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለሥልጣን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቀጥሎ ሁለተኛውን አዲስ የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት በያዝነው ሰኔ ወር ጨረታ እንደሚወጣ መግለጹ ይታወሳል።
አዲሱ”ዓባይ ፪” መርከብ በነዳጅ ጫኝ መርከቦቻችን ሲደርስብን የነበረውን ኪሳራ ማስቀረት ያስቻለ ነው
***
(ኢ.ፕ.ድ)
👉 በቀን 11 ሺህ ዶላር ገቢ ያስገኛል
አዲሱ “ዓባይ ፪” መርከብ በሁለቱ ነዳጅ ጫኝ መርከቦቹ ሲደርስ የነበረውን ኪሳራ ማስቀረት እንደሚያስችል የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አስታወቀ፡፡
በቀን አስራ አንድ ሺህ ዶላር የተጣራ ትርፍ ገቢ የሚያስገኝ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምሰው በንቲ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ አዲሱ”ዓባይ ፪” ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=102814
***
(ኢ.ፕ.ድ)
👉 በቀን 11 ሺህ ዶላር ገቢ ያስገኛል
አዲሱ “ዓባይ ፪” መርከብ በሁለቱ ነዳጅ ጫኝ መርከቦቹ ሲደርስ የነበረውን ኪሳራ ማስቀረት እንደሚያስችል የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አስታወቀ፡፡
በቀን አስራ አንድ ሺህ ዶላር የተጣራ ትርፍ ገቢ የሚያስገኝ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ደምሰው በንቲ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ አዲሱ”ዓባይ ፪” ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=102814
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ዙሪያ እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ውይይት በሐምሌ ወር ይጠናቀቃል
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
👉ውይይቱ በሁሉም ክልሎች ይካሄዳል
👉መስከረም ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይቀርባል
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ዙሪያ እየተካሄደ ያለው ግብዓትን የማሰባሰብ ሃገራዊ ውይይት እስከ መጪው ሐምሌ ወር 2015ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ውይይቱ በሁሉም ክልሎች እንደሚካሄድና መስከረም ወር ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆን ተገልጿል::
በፍትህ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አወል ሱልጣን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲን ለማውጣት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=102817
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
👉ውይይቱ በሁሉም ክልሎች ይካሄዳል
👉መስከረም ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይቀርባል
በሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ዙሪያ እየተካሄደ ያለው ግብዓትን የማሰባሰብ ሃገራዊ ውይይት እስከ መጪው ሐምሌ ወር 2015ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ውይይቱ በሁሉም ክልሎች እንደሚካሄድና መስከረም ወር ላይ ያለቀለት የፖሊሲ ሰነድ ለሕዝብ ይፋ እንደሚሆን ተገልጿል::
በፍትህ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አወል ሱልጣን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲን ለማውጣት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=102817
በአዲስ አበባ ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሃ- ግብር እየተካሄደ ነው
****
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
በማስጀመሪያ መርሃ- ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፤ የሚተከሉት ችግኞች ዓለምን በከፍተኛ ደረጃ እያስጨነቀ ያለው የአየር ንብረት ለውጥ ለማስቀረትና እራስን በምግብ ለማስቻል ነው ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት በከተማ አስተዳደሩ ከ 41 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መትከል ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ በዘንድሮ ክረምት እስከ 17 ሚሊየን ችግኞች እንደሚተከሉ ተናግረዋል፡፡
ከንቲባዋ አክለውም የሐይማኖት ተቋማት ከላቸው ሰፊ ቦታ አኳያ ግንባር ቀደም በመሆን ችግኞች እንዲያስተክሉ ለሐይማኖት አባቶች ጥሪ አድርገዋል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው ሀገራት የሚያደርጉት ልማት ዘላቂ ከሚሆኑባቸው አብይ ጉዳዮች መካከል አካባቢን ያልበከለና ጽድ አካባቢ መፍጠር ነው ብለዋል፡፡
የሀገሪቱ በጣም ዝቅተኛ ከነበረበት የደን ሽፋን በመነሳት በሀገር አቀፍ ደረጃ 17 በመቶ መድረሱን የጠቀሙት ሚኒስትሩ፤ በዘንድሮ እንደሀገር ከስድስት ቢሊየን በላይ ችግኝ እንደሚተከል ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብርሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፣ የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ፣ የፌደራልና የከተማው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሐይማኖት አባቶች እንዲሁም በሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
እንደ አዲስ አበባ ከተማ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ካራ የተካሄደ ሲሆን፤ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል፡፡
<<ነገን ዛሬ እንትከል>> በሚል መሪ ሃሳብ የሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ መጀመሩ የሚታወስ ነው፡፡
በልጅዓለም ፍቅሬ
****
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ ሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ነው፡፡
በማስጀመሪያ መርሃ- ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፤ የሚተከሉት ችግኞች ዓለምን በከፍተኛ ደረጃ እያስጨነቀ ያለው የአየር ንብረት ለውጥ ለማስቀረትና እራስን በምግብ ለማስቻል ነው ብለዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት በከተማ አስተዳደሩ ከ 41 ሚሊዮን በላይ ችግኞች መትከል ተችሏል ያሉት ከንቲባዋ፤ በዘንድሮ ክረምት እስከ 17 ሚሊየን ችግኞች እንደሚተከሉ ተናግረዋል፡፡
ከንቲባዋ አክለውም የሐይማኖት ተቋማት ከላቸው ሰፊ ቦታ አኳያ ግንባር ቀደም በመሆን ችግኞች እንዲያስተክሉ ለሐይማኖት አባቶች ጥሪ አድርገዋል፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በበኩላቸው ሀገራት የሚያደርጉት ልማት ዘላቂ ከሚሆኑባቸው አብይ ጉዳዮች መካከል አካባቢን ያልበከለና ጽድ አካባቢ መፍጠር ነው ብለዋል፡፡
የሀገሪቱ በጣም ዝቅተኛ ከነበረበት የደን ሽፋን በመነሳት በሀገር አቀፍ ደረጃ 17 በመቶ መድረሱን የጠቀሙት ሚኒስትሩ፤ በዘንድሮ እንደሀገር ከስድስት ቢሊየን በላይ ችግኝ እንደሚተከል ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብርሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አበቤ፣ የግብርና ሚኒስትሩ ዶክተር ግርማ አመንቴ፣ የፌደራልና የከተማው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሐይማኖት አባቶች እንዲሁም በሁሉም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
እንደ አዲስ አበባ ከተማ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ካራ የተካሄደ ሲሆን፤ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል፡፡
<<ነገን ዛሬ እንትከል>> በሚል መሪ ሃሳብ የሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ መጀመሩ የሚታወስ ነው፡፡
በልጅዓለም ፍቅሬ
የአፍሪካ ህጻናት ቀን በአዲስ አበባ እየተከበረ ነው
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በኢትዮጵያ ለ32ኛ ጊዜ "ሰላም፣ ፍቅር፣ እንክብካቤና ጥበቃ ለሁሉም ህፃናት" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
በበዓል አከባበር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬን ጨምሮ የፓርላማ ተወካዮች፣ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የህጻናት ፓርላማ ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ተገኝተዋል።
በዓሉ በማርሽ ባንድ አዝናኝ ትርዒቶች የተጀመረ ሲሆን ዕለቱን የተመለከቱ ጠቃሚ መልዕክቶችም በተለያዩ አካላት እየተላለፉ ይገኛል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በአፍሪካ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ የአፍሪካ ህብረት በወሰነው መሰረት "The Rights of Child in the Digital Environment" በሚል አህጉራዊ መሪ ቃል ይከበራል።
ሀገራት ህጻናትና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደህንነትን በተመለከተ በአፍሪካ የህጻናት መብቶችና ደህንነቶች ቻርተር ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎችን፣ ሌሎች ህጋዊ የአሰራር ማዕቀፎችን እና ሌሎች የአህጉሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ቀኑን አስበው መዋላቸውን ከሴቶች እና ማኅበራዊ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በኢትዮጵያ ለ32ኛ ጊዜ "ሰላም፣ ፍቅር፣ እንክብካቤና ጥበቃ ለሁሉም ህፃናት" በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
በበዓል አከባበር ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትሯ ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬን ጨምሮ የፓርላማ ተወካዮች፣ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የህጻናት ፓርላማ ተወካዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ተገኝተዋል።
በዓሉ በማርሽ ባንድ አዝናኝ ትርዒቶች የተጀመረ ሲሆን ዕለቱን የተመለከቱ ጠቃሚ መልዕክቶችም በተለያዩ አካላት እየተላለፉ ይገኛል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ህጻናት ቀን በአፍሪካ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ የአፍሪካ ህብረት በወሰነው መሰረት "The Rights of Child in the Digital Environment" በሚል አህጉራዊ መሪ ቃል ይከበራል።
ሀገራት ህጻናትና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደህንነትን በተመለከተ በአፍሪካ የህጻናት መብቶችና ደህንነቶች ቻርተር ላይ የሰፈሩ ድንጋጌዎችን፣ ሌሎች ህጋዊ የአሰራር ማዕቀፎችን እና ሌሎች የአህጉሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ቀኑን አስበው መዋላቸውን ከሴቶች እና ማኅበራዊ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።