በወላይታ ዞን እየተካሄደ የሚገኘው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ‼️
የወላይታ ዞን የድጋሚ ህዝበ ውሳኔ የድምፅ መስጠት ሂደት ዛሬ ማለዳ
12፡00 ተጀምሯል። ቦርዱ የድጋሚ ህዝበ ውሳኔውን የሚያከናውኑ የምርጫ አስፈፃሚዎችን በተለያየ መንገድ የመለመለ ሲሆን፤ ከአዲስ አበባ 5215 የምርጫ አስፈፃሚዎች እና ከወላይታ 3845 የምርጫ አስፈፃሚዎች ተሳትፈዋል።
በዛሬው እለት ሁሉም አስፈፃሚዎች በስራ ላይ ተሰማርተው መራጮችን በማስተናገድ ላይ ይገኛሉ። አንድ አንድ ሰልፎች የበዙባቸው ጣቢያዎች ላይ ቦርዱ አሰልጥኖ በተጠባባቂነት የያዛቸውን አስፈፃሚዎችን አሰማርቷል። በ1812 የምርጫ ጣቢያዎች የተሟላ የምርጫ ቁሳቁሶች መድረሳቸውን ቦርዱ አረጋግጧል።
ከጠዋት 12፡00 ሰዓት እንከ 6፡00 ሰዓት በተገኘው መረጃ 370,552 መራጭ ድምፅ ሰጥቷል። በተያያዘም የድምፅ መስጠት ሂደት ቦርዱ ለሶስት የሀገር ውስጥ ተቋማት የታዛቢነት እውቅና ሰጥቶ በዞኑ የተለያዩ ጣቢያዎች ላይ 214 ታዛቢዎች ተሰማርተዋል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ በርከት ያሉ መራጮች ከተሠጣቸው 6 ወር ያልሞላው መታወቂያ ሆኖ ተገኝቷል። ነገር ግን የቦርዱ መመሪያ አንድ ዜጋ ድምፅ መስጠት የሚችለው በመኖርያ ስፍራው ቢያንስ ለስድስት ወር እና ከዚያ በላይ መኖሩ መረጋገጥ እንዳለበት ተጠቅሷል። ስለዚህ እነዚህ መራጮች ከያዙት የነዋሪነት መታወቂያ በተጨማሪ ነዋሪነታቸውን የሚያረጋግጡበት የሶስት ሰዎች ምስክርነት ወይም ሌሎች የሠነድ ማስረጃዎችን በማቅረብ ድምፅ እንዲሰጡ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም
የወላይታ ዞን የድጋሚ ህዝበ ውሳኔ የድምፅ መስጠት ሂደት ዛሬ ማለዳ
12፡00 ተጀምሯል። ቦርዱ የድጋሚ ህዝበ ውሳኔውን የሚያከናውኑ የምርጫ አስፈፃሚዎችን በተለያየ መንገድ የመለመለ ሲሆን፤ ከአዲስ አበባ 5215 የምርጫ አስፈፃሚዎች እና ከወላይታ 3845 የምርጫ አስፈፃሚዎች ተሳትፈዋል።
በዛሬው እለት ሁሉም አስፈፃሚዎች በስራ ላይ ተሰማርተው መራጮችን በማስተናገድ ላይ ይገኛሉ። አንድ አንድ ሰልፎች የበዙባቸው ጣቢያዎች ላይ ቦርዱ አሰልጥኖ በተጠባባቂነት የያዛቸውን አስፈፃሚዎችን አሰማርቷል። በ1812 የምርጫ ጣቢያዎች የተሟላ የምርጫ ቁሳቁሶች መድረሳቸውን ቦርዱ አረጋግጧል።
ከጠዋት 12፡00 ሰዓት እንከ 6፡00 ሰዓት በተገኘው መረጃ 370,552 መራጭ ድምፅ ሰጥቷል። በተያያዘም የድምፅ መስጠት ሂደት ቦርዱ ለሶስት የሀገር ውስጥ ተቋማት የታዛቢነት እውቅና ሰጥቶ በዞኑ የተለያዩ ጣቢያዎች ላይ 214 ታዛቢዎች ተሰማርተዋል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ በርከት ያሉ መራጮች ከተሠጣቸው 6 ወር ያልሞላው መታወቂያ ሆኖ ተገኝቷል። ነገር ግን የቦርዱ መመሪያ አንድ ዜጋ ድምፅ መስጠት የሚችለው በመኖርያ ስፍራው ቢያንስ ለስድስት ወር እና ከዚያ በላይ መኖሩ መረጋገጥ እንዳለበት ተጠቅሷል። ስለዚህ እነዚህ መራጮች ከያዙት የነዋሪነት መታወቂያ በተጨማሪ ነዋሪነታቸውን የሚያረጋግጡበት የሶስት ሰዎች ምስክርነት ወይም ሌሎች የሠነድ ማስረጃዎችን በማቅረብ ድምፅ እንዲሰጡ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም
"በክልላችን ማንም ምንም አይነት ወንጀል ፈጽሞ ማምለጥ የማይችልበት ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር አደራጅተናል" የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሲዳማ ክልል ዉስጥ ማንም ምንም አይነት ወንጀል ፈጽሞ ማምለጥ የማይችልበት ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር አደራጅተናል ሲል የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ።
ሰሞኑን በሀዋሳ ከተማ ተጠለፈች የተባለችውን የ8ኛ ክፍል ተማሪ በተደረገዉ ክትትል ትላንት ማታ ከይርጋለም ከተማ ከእነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ማወላቸውን
የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ገልጸዋል።
በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ ተከሰቱ በተባሉ የጠለፋ ወንጀሎች ምክንያት ስም የሚያጠለሹ አካላት እንደነበሩ ገልጸዉ፤ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
የክልሉን ሰላም አስተማማኝነት ለማስቀጠል የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነዉ ያሉት ሀላፊው፤ በአሁኑ ወቅት በክልሉ አስተማማኝ የጸጥታ መዋቅር የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡም ሰላሙን ለማረጋገጥ ከፀጥታው ሀይል ጎን ሊቆም እንደሚገባም አሳስበዋል።
በአዲሱ አዶላ (ሀዋሳ)
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሲዳማ ክልል ዉስጥ ማንም ምንም አይነት ወንጀል ፈጽሞ ማምለጥ የማይችልበት ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር አደራጅተናል ሲል የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታወቀ።
ሰሞኑን በሀዋሳ ከተማ ተጠለፈች የተባለችውን የ8ኛ ክፍል ተማሪ በተደረገዉ ክትትል ትላንት ማታ ከይርጋለም ከተማ ከእነተጠርጣሪው በቁጥጥር ስር ማወላቸውን
የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ ገልጸዋል።
በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ ተከሰቱ በተባሉ የጠለፋ ወንጀሎች ምክንያት ስም የሚያጠለሹ አካላት እንደነበሩ ገልጸዉ፤ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
የክልሉን ሰላም አስተማማኝነት ለማስቀጠል የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነዉ ያሉት ሀላፊው፤ በአሁኑ ወቅት በክልሉ አስተማማኝ የጸጥታ መዋቅር የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡም ሰላሙን ለማረጋገጥ ከፀጥታው ሀይል ጎን ሊቆም እንደሚገባም አሳስበዋል።
በአዲሱ አዶላ (ሀዋሳ)
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር የተመራ ልዑክ የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ወቅታዊ እንቅስቃሴን ተመለከቱ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩአን፣ የቻይና የካውስል ሚኒስትር ሚስተር ያንግ እንዲሁም የሲሲሲሲ ( CCCC ) ኢትዮጵያ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክን ወቅታዊ የስራ እንቅስቃሴ ተዟዙረው ተመልክተዋል።
ልዑኩን የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስራ አስኪያጅ አቶ ፊሊሞን ተረፈ እና የፓርኩ የስራ ኃላፊዎች ልዑኩን ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን የቻይናው ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ( CCCC ) በፓርኩ እያከናወናቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ በጋራ ጉብኝት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ ፕሮጀክቱ በፓርኩ ስለሚያከናውናቸው ስራዎችም ውይይት ተካሂዷል።
ከዚህ ጋር በተያያዘም የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ወደ ስራ እየገባ መሆኑን ተከትሎ የቻይና ባለሀብቶች በፓርኩ በተለያዩ ዘርፎች በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ለአምባሳደር ዣኦ ዥዩአን ጥሪ ቀርቧል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክን ወደ ስራ ለመመለስ በአመራሮች የታገዘ ቡድን በማቋቋም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁ የሚታወስ ነው ሲል ኮርፓሬሽኑ ዘግቧል።
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዥዩአን፣ የቻይና የካውስል ሚኒስትር ሚስተር ያንግ እንዲሁም የሲሲሲሲ ( CCCC ) ኢትዮጵያ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክን ወቅታዊ የስራ እንቅስቃሴ ተዟዙረው ተመልክተዋል።
ልዑኩን የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስራ አስኪያጅ አቶ ፊሊሞን ተረፈ እና የፓርኩ የስራ ኃላፊዎች ልዑኩን ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን የቻይናው ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ( CCCC ) በፓርኩ እያከናወናቸው የሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ በጋራ ጉብኝት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ ፕሮጀክቱ በፓርኩ ስለሚያከናውናቸው ስራዎችም ውይይት ተካሂዷል።
ከዚህ ጋር በተያያዘም የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ወደ ስራ እየገባ መሆኑን ተከትሎ የቻይና ባለሀብቶች በፓርኩ በተለያዩ ዘርፎች በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ለአምባሳደር ዣኦ ዥዩአን ጥሪ ቀርቧል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክን ወደ ስራ ለመመለስ በአመራሮች የታገዘ ቡድን በማቋቋም አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁ የሚታወስ ነው ሲል ኮርፓሬሽኑ ዘግቧል።
በዩናይትድ ኪንግደም የንግድ ሚኒስቴር የተመራ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አደረገ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በዩናይትድ ኪንግደም የንግድ ሚኒስቴር ኒጌል ሀድልስቶን የተመራ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አደረገ።
የልዑካን ቡድኑ በቀጣይ የዩናይትድ ኪንግደም ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንደስትሪ ፓርኮች ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ በኢንቨስትመንት በሚሰማሩበት ሁኔታ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት በማድረግ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቀጣይ መስራት በሚችሉባቸው አንኳር ጉዳዮች ላይ ስምምነት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከአጎዋ እግድ ጋር ተያይዞ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ በኢንቨስትመንት ለተሰማሩ አለም አቀፍ አምራቾች ሰፊ የገበያ መዳረሻዎችን በማፈላለግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
ኮርፖሬሽኑ ከዩናይትድ ኪንግደም የንግድ ሚኒስቴር ጋር ዛሬ የሚያደርገው ስምምነትም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገኙ አምራቾች በዩናይትድ ኪንግደም ከታሪፍ ነፃ ገበያ እንዲያገኙ የሚያስችል ነውም ብሏል።
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በዩናይትድ ኪንግደም የንግድ ሚኒስቴር ኒጌል ሀድልስቶን የተመራ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አደረገ።
የልዑካን ቡድኑ በቀጣይ የዩናይትድ ኪንግደም ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንደስትሪ ፓርኮች ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን በማፍሰስ በኢንቨስትመንት በሚሰማሩበት ሁኔታ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት በማድረግ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቀጣይ መስራት በሚችሉባቸው አንኳር ጉዳዮች ላይ ስምምነት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከአጎዋ እግድ ጋር ተያይዞ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ በኢንቨስትመንት ለተሰማሩ አለም አቀፍ አምራቾች ሰፊ የገበያ መዳረሻዎችን በማፈላለግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።
ኮርፖሬሽኑ ከዩናይትድ ኪንግደም የንግድ ሚኒስቴር ጋር ዛሬ የሚያደርገው ስምምነትም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገኙ አምራቾች በዩናይትድ ኪንግደም ከታሪፍ ነፃ ገበያ እንዲያገኙ የሚያስችል ነውም ብሏል።
ለምርት ዘመኑ የሚያሰፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በ2015/16 ምርት ዘመን የሚውል 12 ነጥብ ስምንት ሚሊዮን የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ተፈጽሞ ወደ ሀገር ውስጥ የማጓኀጓዝ ስራ እየተሰራ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
እስከ ሰኔ 10/2015 ዓ.ም ድረስ ከሰባት ነጥብ አራት ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ የደረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ስድስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ሙሉ በሙሉ ሀገር ውስጥ ገብቶ እየተጓጓዘ ነው፡፡
የማጓጓዝ ስራው በመኪና እና በባቡር በፍጥነት እየተከናወነ ሲሆን አዳማ ካለው ባቡሩ ጣቢያ እንደደረሰ ወደ ኦሮሚያ፣ አማራና የሲዳማ ክልሎች ሲጓጓዝ የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
በክልሎች ያሉ የተለያዩ የህብረት ስራ ማህበራት የማጓጓዝ ስራውን በትኩረት እየሰሩ ነው ተብሏል፡፡
በቀጣይም ለምርት ዘመኑ የሚያስፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ እና አርብቶ አደሮች ለማቅረብ ግብርና ሚኒስቴር በትኩረት ይሰራል ብሏል፡፡
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በ2015/16 ምርት ዘመን የሚውል 12 ነጥብ ስምንት ሚሊዮን የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ተፈጽሞ ወደ ሀገር ውስጥ የማጓኀጓዝ ስራ እየተሰራ መሆኑን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
እስከ ሰኔ 10/2015 ዓ.ም ድረስ ከሰባት ነጥብ አራት ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ የደረሰ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ስድስት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ሙሉ በሙሉ ሀገር ውስጥ ገብቶ እየተጓጓዘ ነው፡፡
የማጓጓዝ ስራው በመኪና እና በባቡር በፍጥነት እየተከናወነ ሲሆን አዳማ ካለው ባቡሩ ጣቢያ እንደደረሰ ወደ ኦሮሚያ፣ አማራና የሲዳማ ክልሎች ሲጓጓዝ የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
በክልሎች ያሉ የተለያዩ የህብረት ስራ ማህበራት የማጓጓዝ ስራውን በትኩረት እየሰሩ ነው ተብሏል፡፡
በቀጣይም ለምርት ዘመኑ የሚያስፈልገውን የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ እና አርብቶ አደሮች ለማቅረብ ግብርና ሚኒስቴር በትኩረት ይሰራል ብሏል፡፡