የመዝናኛውን ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሻገር ኢቢሲ ልዩ ሥራ እና አሰራር ይዞ መምጣቱ ተገለጸ
*******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከተለያዩ አንጋፋና ወጣት የሀገራችን የጥበብ ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ያዘጋጃቸውን የቴሌቪዥን ድራማዎች ትናንት በሸራተን አዲስ ሆቴል በደማቅ ሥነ ስርዓት አስመርቋል።
ድራማዎቹ በተለያየ ዘውግ የተሰሩ ሲሆን ከቀናት በኋላ ማለትም ከሰኔ 18/2015 ዓ.ም ጀምሮ በየሳምንቱ ለህዝብ መቅረብ ይጀምራሉ።
የኢቢሲ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍሰሃ ይታገሱ በምርቃ ሥነስርዓቱ ባደረጉት ንግግር ኮርፖሬሽኑ በአሁኑ ወቅት የአድማጭ ተመልካች ፍላጎትን ለማርካት እና የተጣለበትን ማህበራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ከፍተኛና ሁለንተናዊ ተቋማዊ የሪፎርም ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አድማጭ ተመልካቹ የተሻለ አማራጭ እና ተመራጭ የሚዲያ ይዘት እንዲያገኝ ተቋሙ በተለያዩ ቻናሎቹ ከፍተኛ የለውጥ ሥራዎች እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።በመዝናኛው ዘርፍ ቀዳሚና ግንባር ቀደም የሀገሪቱ ሚዲያ ሆኖ እንዲቀጥል አዳዲስ የፕሮግራም እና የድራማ ይዘቶችን በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በውስጥ አቅም ከሚሰሩ በርካታ ፕሮግራሞች በተጨማሪ በሀገራችን ያሉ ዕንቁ የጥበብ ባለሙያዎችን በማስተባበርና በማሳተፍ የመዝናኛ ኢንዱስትሪውን የላቀ ደረጃ በማድረስ በሀገሪቱ ሁለንተናዊ ለውጥ ውስጥ ኢቢሲ ልዩ ሚና እንደሚወጣ አቶ ፍሰሃ ገልጸዋል።
የኢቲቪ መዝናኛ ቻናል ማኔጂንግ ኤዲተር አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ ተመርቀው በየሳምንቱ መታየት የሚጀምሩት ስድስት ድራማዎች ከፍተኛ ልምድና ዝና ያላቸው የሀገራችን የጥበብ ባለሙያዎች እንደተሳተፉበት ገልጸው፤ በይዘትና አቀራረብ ተመልካች እንዲወዳቸውና መርጦ እንዲመለከታቸው ከፍተኛ ጥንቃቄና ጊዜ ተወስዶ ዝግጅት የተደረገባቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ትናንት የደመቀ የመክፈቻና የማስመረቂያ ሥነስርዓት የተካሄደላቸው የኢቢሲ አዳዲስ ድራማዎች እና ሳምንታዊ የመተላለፊያ ቀንና ሰዓታቸው የሚከተለው ነው።
"ግራ ቀኝ"... እሁድ ቀን 8 ሰዓት በዜና ቻናል እንዲሁም ማታ 2 ሰዓት በመዝናኛ ቻናል
"በመሐል"...ሰኞ ማታ 2:20 በመዝናኛ ቻናል
"እቴጌ"...በሳምንት ሁለት ጊዜ ረቡዕ እና አርብ ማታ 2:20 በመዝናኛ ቻናል
"ደርዳሬ"(ኮሜድያን ደረጄ ሐይሌ)...እሁድ ቀን 9:30 በመዝናኛ ቻናል
"ሲምቦ"...አርብ ማታ 3:20 በአፋን ኦሮሞ ቻናል
"ሒርኮ"...እሁድ ከሰዓት በኋላ በአፋን ኦሮሞ ቻናል በዳንጋ የመዝናኛ ፕሮግራም እንደሚቀርቡ ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
*******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ከተለያዩ አንጋፋና ወጣት የሀገራችን የጥበብ ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ያዘጋጃቸውን የቴሌቪዥን ድራማዎች ትናንት በሸራተን አዲስ ሆቴል በደማቅ ሥነ ስርዓት አስመርቋል።
ድራማዎቹ በተለያየ ዘውግ የተሰሩ ሲሆን ከቀናት በኋላ ማለትም ከሰኔ 18/2015 ዓ.ም ጀምሮ በየሳምንቱ ለህዝብ መቅረብ ይጀምራሉ።
የኢቢሲ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍሰሃ ይታገሱ በምርቃ ሥነስርዓቱ ባደረጉት ንግግር ኮርፖሬሽኑ በአሁኑ ወቅት የአድማጭ ተመልካች ፍላጎትን ለማርካት እና የተጣለበትን ማህበራዊ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ከፍተኛና ሁለንተናዊ ተቋማዊ የሪፎርም ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አድማጭ ተመልካቹ የተሻለ አማራጭ እና ተመራጭ የሚዲያ ይዘት እንዲያገኝ ተቋሙ በተለያዩ ቻናሎቹ ከፍተኛ የለውጥ ሥራዎች እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።በመዝናኛው ዘርፍ ቀዳሚና ግንባር ቀደም የሀገሪቱ ሚዲያ ሆኖ እንዲቀጥል አዳዲስ የፕሮግራም እና የድራማ ይዘቶችን በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በውስጥ አቅም ከሚሰሩ በርካታ ፕሮግራሞች በተጨማሪ በሀገራችን ያሉ ዕንቁ የጥበብ ባለሙያዎችን በማስተባበርና በማሳተፍ የመዝናኛ ኢንዱስትሪውን የላቀ ደረጃ በማድረስ በሀገሪቱ ሁለንተናዊ ለውጥ ውስጥ ኢቢሲ ልዩ ሚና እንደሚወጣ አቶ ፍሰሃ ገልጸዋል።
የኢቲቪ መዝናኛ ቻናል ማኔጂንግ ኤዲተር አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ ተመርቀው በየሳምንቱ መታየት የሚጀምሩት ስድስት ድራማዎች ከፍተኛ ልምድና ዝና ያላቸው የሀገራችን የጥበብ ባለሙያዎች እንደተሳተፉበት ገልጸው፤ በይዘትና አቀራረብ ተመልካች እንዲወዳቸውና መርጦ እንዲመለከታቸው ከፍተኛ ጥንቃቄና ጊዜ ተወስዶ ዝግጅት የተደረገባቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ትናንት የደመቀ የመክፈቻና የማስመረቂያ ሥነስርዓት የተካሄደላቸው የኢቢሲ አዳዲስ ድራማዎች እና ሳምንታዊ የመተላለፊያ ቀንና ሰዓታቸው የሚከተለው ነው።
"ግራ ቀኝ"... እሁድ ቀን 8 ሰዓት በዜና ቻናል እንዲሁም ማታ 2 ሰዓት በመዝናኛ ቻናል
"በመሐል"...ሰኞ ማታ 2:20 በመዝናኛ ቻናል
"እቴጌ"...በሳምንት ሁለት ጊዜ ረቡዕ እና አርብ ማታ 2:20 በመዝናኛ ቻናል
"ደርዳሬ"(ኮሜድያን ደረጄ ሐይሌ)...እሁድ ቀን 9:30 በመዝናኛ ቻናል
"ሲምቦ"...አርብ ማታ 3:20 በአፋን ኦሮሞ ቻናል
"ሒርኮ"...እሁድ ከሰዓት በኋላ በአፋን ኦሮሞ ቻናል በዳንጋ የመዝናኛ ፕሮግራም እንደሚቀርቡ ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
በወላይታ ዞን ድጋሚ የተካሄደው የህዝበ ውሳኔ የመጨረሻ ውጤት ሰኔ 19 ቀን 2015 ይፋ እንደሚደረግ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
******
(ኢ.ፕ.ድ)
በወላይታ ዞን ድጋሚ በትናንትናው እለት ድጋሜ የተካሄደው የህዝበ ውሳኔ የመጨረሻ ውጤት ሰኔ 19 ቀን 2015 ይፋ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ አስታውቋል።
የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በወላይታ ዞን በድጋሚ የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ህዝበ ውሳኔው በተደረገው ቅድመ ዝግጅት መሰረት በሰላም መጠናቀቁንም ነው ሰብሳቢዋ የገለጹት።
በህዝበ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ላጋጠሙ መጠነኛ ችግሮች ተገቢ መፍትሄ በመስጠት መራጮች መብታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ መደረጉን ሰብሳቢዋ ትላንት ምሽት በሰጡት መግለጫ አመልክተዋል።
የህዝበ ውሳኔው የመጨረሻ ውጤት በተያዘው እቅድ መሰረት ሰኔ 19 ቀን 2015 ይፋ እንደሚደረግ የገለጹት ሰብሳቢዋ ከተቻለም አስቀድሞ ለመግለጽ ቦርዱና ሰራተኞቹ በትጋት እንደሚሰሩም አስታውቀዋል።
ሰብሳቢዋ በመግለጫቸው እንዳሉት በዞኑ በድጋሚ የተካሄደው ህዝበ ውሳኔ የተሳካ እንዲሆን ቦርዱ በሰው ሀይልና በሎጂስቲክስ በቂ ዝግጅት በማድረግ ወደ ተግባር ገብቷል።
የህዝበ ውሳኔ የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥ ስነ-ስርዓት በተመሳሳይ ሰዓት የሚካሄድ በሆኑ ለስኬቱ የምርጫ ማዕከላትና ጣቢያዎችን የማስፋት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።
በዚሁ መሰረት ከዚህ ቀደም ከነበረው የምርጫ ማእከላትን ከስምስት ወደ 12 እንዲሁም 1 ሺህ 112 የነበሩትን ምርጫ ጣቢያዎች ወደ 1 ሺህ 812 በማሳደግ ሂደቱ መከናወኑን ጠቅሰዋል።
"9 ሺህ 60 የምርጫ አስፈጻሚዎች ተመልምለውና በቂ ስልጠና ተሰጥቷቸው ሂደቱን አስፈጽመዋል" ብለዋል።
የድምጽ አሰጣጡ መደበኛ ሰዓት ከተጠናቀቀ በኃላ መብታቸውን መጠቀም የሚገባቸው መራጮች ሰልፍ ላይ ስለነበሩ በህጉ መሰረት ለአንድ ተጨማሪ ሰዓት በማራዘም መከናወኑን ተናግረዋል።
ሰብሳቢዋ አክለውም የምርጫው ሂደት ተአማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆኑን የሚታዘቡ ከሀገር ውስጥ ሁለት ተቋማት ከቦርዱ ዕውቅና ተሰጥቷቸው 168 ታዛቢዎችን አሰማርተው ሂደቱን መታዘባቸውን ገልጸዋል።
በዕለቱ የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥ ሂደት በተመሳሳይ ሰዓት መከናወኑን ያነሱት ሰብሳቢዋ በዚህም ቦርዱ ተግባሩን በሚያከናውንበት ጊዜ ያጋጠሙ ችግሮች እንደነበሩ አንስተዋል።
ከችግሮቹ መካከልም በብዙ ጣቢያዎች በአካባቢው ስድስት ወር መኖራቸውን የሚያረጋግጥ የህግ ቅድመ ሁኔታ የማያሟላና ህጋዊ መታወቂያ ሳይኖራቸው ድምፅ ለመስጠት የመጡ መገኘታቸውን ጠቅሰዋል።
በቦርዱ ህግና መመሪያ መሰረት የመራጮች የመምረጥ መብታቸው እንዲጠበቅ በማሰብ ነዋሪነታቸውን በሶስት ምስክርና በሌሎች ሰነዶች በማረጋገጥ መፍትሄ በመስጠት እንዲሳተፉ መደረጉን ተናግረዋል።
እንዲሁም በተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች ከ18 ዓመት በታች የሆኑ መራጮች መገኘታቸው ሌላው ችግር እንደነበር አንስተው "ግለሰቦቹ ህጉ ስለማይፈቅድላቸው እንዳይሳተፉ ተደርጓል" ብለዋል።
በተጨማሪም በሶዶ ዙሪያ በሚገኝ ድልቦ አውጥሮ 1 ምርጫ ጣቢያ ላይ ድምፅ ለመስጠት የመጣ አስፈጻሚ ባዶ መታወቂያ እየሞላ ሲያድል እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ መጀመሩን ተናግረዋል።
"በሁምቦ ምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚ ሳይሆን ነኝ በሚል ባጅ አንጠልጥሎ ለመግባት የሞከረ ግለሰብ መያዙንና እንዲሁም በገሱባ 01 ምርጫ ጣቢያ አምስት ስርዝ ድልዝ ያለበት የነዋሪነት መታወቂያ ይዘው የተገኙ ግለሰቦች እንዲመለሱ ተደርጓል" ብለዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ከፍተኛ የሆነ ጥሰት ሳይገኝ የህዝበ ውሳኔ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት በሰላማዊ ሁኔታ ተከናውኖ መጠናቀቁን ሰብሳቢዋ አስታውቀዋል።
******
(ኢ.ፕ.ድ)
በወላይታ ዞን ድጋሚ በትናንትናው እለት ድጋሜ የተካሄደው የህዝበ ውሳኔ የመጨረሻ ውጤት ሰኔ 19 ቀን 2015 ይፋ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ አስታውቋል።
የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በወላይታ ዞን በድጋሚ የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ህዝበ ውሳኔው በተደረገው ቅድመ ዝግጅት መሰረት በሰላም መጠናቀቁንም ነው ሰብሳቢዋ የገለጹት።
በህዝበ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ላጋጠሙ መጠነኛ ችግሮች ተገቢ መፍትሄ በመስጠት መራጮች መብታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ መደረጉን ሰብሳቢዋ ትላንት ምሽት በሰጡት መግለጫ አመልክተዋል።
የህዝበ ውሳኔው የመጨረሻ ውጤት በተያዘው እቅድ መሰረት ሰኔ 19 ቀን 2015 ይፋ እንደሚደረግ የገለጹት ሰብሳቢዋ ከተቻለም አስቀድሞ ለመግለጽ ቦርዱና ሰራተኞቹ በትጋት እንደሚሰሩም አስታውቀዋል።
ሰብሳቢዋ በመግለጫቸው እንዳሉት በዞኑ በድጋሚ የተካሄደው ህዝበ ውሳኔ የተሳካ እንዲሆን ቦርዱ በሰው ሀይልና በሎጂስቲክስ በቂ ዝግጅት በማድረግ ወደ ተግባር ገብቷል።
የህዝበ ውሳኔ የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥ ስነ-ስርዓት በተመሳሳይ ሰዓት የሚካሄድ በሆኑ ለስኬቱ የምርጫ ማዕከላትና ጣቢያዎችን የማስፋት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።
በዚሁ መሰረት ከዚህ ቀደም ከነበረው የምርጫ ማእከላትን ከስምስት ወደ 12 እንዲሁም 1 ሺህ 112 የነበሩትን ምርጫ ጣቢያዎች ወደ 1 ሺህ 812 በማሳደግ ሂደቱ መከናወኑን ጠቅሰዋል።
"9 ሺህ 60 የምርጫ አስፈጻሚዎች ተመልምለውና በቂ ስልጠና ተሰጥቷቸው ሂደቱን አስፈጽመዋል" ብለዋል።
የድምጽ አሰጣጡ መደበኛ ሰዓት ከተጠናቀቀ በኃላ መብታቸውን መጠቀም የሚገባቸው መራጮች ሰልፍ ላይ ስለነበሩ በህጉ መሰረት ለአንድ ተጨማሪ ሰዓት በማራዘም መከናወኑን ተናግረዋል።
ሰብሳቢዋ አክለውም የምርጫው ሂደት ተአማኒና ዴሞክራሲያዊ መሆኑን የሚታዘቡ ከሀገር ውስጥ ሁለት ተቋማት ከቦርዱ ዕውቅና ተሰጥቷቸው 168 ታዛቢዎችን አሰማርተው ሂደቱን መታዘባቸውን ገልጸዋል።
በዕለቱ የመራጮች ምዝገባና የድምጽ አሰጣጥ ሂደት በተመሳሳይ ሰዓት መከናወኑን ያነሱት ሰብሳቢዋ በዚህም ቦርዱ ተግባሩን በሚያከናውንበት ጊዜ ያጋጠሙ ችግሮች እንደነበሩ አንስተዋል።
ከችግሮቹ መካከልም በብዙ ጣቢያዎች በአካባቢው ስድስት ወር መኖራቸውን የሚያረጋግጥ የህግ ቅድመ ሁኔታ የማያሟላና ህጋዊ መታወቂያ ሳይኖራቸው ድምፅ ለመስጠት የመጡ መገኘታቸውን ጠቅሰዋል።
በቦርዱ ህግና መመሪያ መሰረት የመራጮች የመምረጥ መብታቸው እንዲጠበቅ በማሰብ ነዋሪነታቸውን በሶስት ምስክርና በሌሎች ሰነዶች በማረጋገጥ መፍትሄ በመስጠት እንዲሳተፉ መደረጉን ተናግረዋል።
እንዲሁም በተወሰኑ ምርጫ ጣቢያዎች ከ18 ዓመት በታች የሆኑ መራጮች መገኘታቸው ሌላው ችግር እንደነበር አንስተው "ግለሰቦቹ ህጉ ስለማይፈቅድላቸው እንዳይሳተፉ ተደርጓል" ብለዋል።
በተጨማሪም በሶዶ ዙሪያ በሚገኝ ድልቦ አውጥሮ 1 ምርጫ ጣቢያ ላይ ድምፅ ለመስጠት የመጣ አስፈጻሚ ባዶ መታወቂያ እየሞላ ሲያድል እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ መጀመሩን ተናግረዋል።
"በሁምቦ ምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚ ሳይሆን ነኝ በሚል ባጅ አንጠልጥሎ ለመግባት የሞከረ ግለሰብ መያዙንና እንዲሁም በገሱባ 01 ምርጫ ጣቢያ አምስት ስርዝ ድልዝ ያለበት የነዋሪነት መታወቂያ ይዘው የተገኙ ግለሰቦች እንዲመለሱ ተደርጓል" ብለዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ከፍተኛ የሆነ ጥሰት ሳይገኝ የህዝበ ውሳኔ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት በሰላማዊ ሁኔታ ተከናውኖ መጠናቀቁን ሰብሳቢዋ አስታውቀዋል።
በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚሰሩ ባለሀብቶች ወደ እንግሊዝ ሀገር ከታሪፍ ነፃ ገበያ ምርቶቻቸውን ሊያቀርቡ ነው
**************
(ኢፕ.ድ)
የታዳጊ ሀገራት አምራቾች በዩናይትድ ኪንግደም ገበያ ምርቶቻቸውን ከታሪፍ ነፃ እንዲያቀርቡ የሚያስችል የመክፈቻ መርሃ ግብር በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተካሂዷል።
በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ የተገኙት የዩናይትድ ኪንግደም የንግድ ሚኒስቴር ናይጄል ሀድልስተን የታዳጊ ሀገራት ነፃ የንግድ ፕሮግራም በ65 የዓለም ሀገራትና በ37 የአፍሪካ ሀገራት የሚጀመር መሆኑን ገልፀው በኢትዮጵያ በአልባሳትና ጨርቃ ጨርቅ እንዲሁም በሌሎች የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ምርት የተሰማሩ አምራቾች በዩናይትድ ኪንግደም ገበያ ላይ ምርቶቻቸውን በነፃ እንዲያቀርቡ ያግዛል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ በበኩላቸው ሂደቱ እየተስተዋለ ያለውን የተዛባ የዓለም አቀፍ የንግድ ምጣኔና ስርዓት በመረዳት ፍትሀዊና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያሰፍን ፤ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርግ የማበረታቻ ማዕቀፍ ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በ2030 የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ወደ 85 በመቶ በማሳደግ ከአምራች ኢንዲስትሪው ዘርፍ 5 ሚሊየን የስራ እድል እና 9 ቢሊየን ዶላር ለማሳካት አቅዶ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ሲተገብር ቆይቷል ያሉት አቶ ሀሰን ባለፉት ተከታታይ አመታት የCOVID , AGOA እና የሩስያና ዩክሬን ጦርነት እና በሌሎች ምክንያቶች ኢትዮጵያን ጨምሮ የአብዛኛው ሀገር ኢንዱስትሪ የመቀዝቀዝ አዝማሚያ አሳይቷል።
መንግስት ግን ኢትዮጵያ ታምርት የሚል ሀገራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ንቅናቄ አብዮት በመፍጠር አለማቀፍ ጫናን መቋቋም የሚችል አምራች ኢንዱስትሪ በመገንባት ላይ ነው ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ፣የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ሌሊሴ ነሜ እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና የዘርፉ ተዋናዮች ተገኝተዋል፡፡
**************
(ኢፕ.ድ)
የታዳጊ ሀገራት አምራቾች በዩናይትድ ኪንግደም ገበያ ምርቶቻቸውን ከታሪፍ ነፃ እንዲያቀርቡ የሚያስችል የመክፈቻ መርሃ ግብር በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተካሂዷል።
በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ የተገኙት የዩናይትድ ኪንግደም የንግድ ሚኒስቴር ናይጄል ሀድልስተን የታዳጊ ሀገራት ነፃ የንግድ ፕሮግራም በ65 የዓለም ሀገራትና በ37 የአፍሪካ ሀገራት የሚጀመር መሆኑን ገልፀው በኢትዮጵያ በአልባሳትና ጨርቃ ጨርቅ እንዲሁም በሌሎች የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎች ምርት የተሰማሩ አምራቾች በዩናይትድ ኪንግደም ገበያ ላይ ምርቶቻቸውን በነፃ እንዲያቀርቡ ያግዛል ብለዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ በበኩላቸው ሂደቱ እየተስተዋለ ያለውን የተዛባ የዓለም አቀፍ የንግድ ምጣኔና ስርዓት በመረዳት ፍትሀዊና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያሰፍን ፤ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርግ የማበረታቻ ማዕቀፍ ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በ2030 የፋብሪካዎችን የማምረት አቅም ወደ 85 በመቶ በማሳደግ ከአምራች ኢንዲስትሪው ዘርፍ 5 ሚሊየን የስራ እድል እና 9 ቢሊየን ዶላር ለማሳካት አቅዶ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ሲተገብር ቆይቷል ያሉት አቶ ሀሰን ባለፉት ተከታታይ አመታት የCOVID , AGOA እና የሩስያና ዩክሬን ጦርነት እና በሌሎች ምክንያቶች ኢትዮጵያን ጨምሮ የአብዛኛው ሀገር ኢንዱስትሪ የመቀዝቀዝ አዝማሚያ አሳይቷል።
መንግስት ግን ኢትዮጵያ ታምርት የሚል ሀገራዊ የአምራች ኢንዱስትሪ ንቅናቄ አብዮት በመፍጠር አለማቀፍ ጫናን መቋቋም የሚችል አምራች ኢንዱስትሪ በመገንባት ላይ ነው ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፓሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ፣የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ሌሊሴ ነሜ እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና የዘርፉ ተዋናዮች ተገኝተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል መልዕክት‼️
በቴክኒክና ሞያ ስልጠና ዘርፍ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያለንን አጋርነት እና ትብብር ለማጠናከር እና ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመቅሰም ያለመ የሥራ ጉብኝት በጀርመን ሙኒክ፡፡
በቆይታችን ከኢንዱስትሪ መሪዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና የማህበራት ተወካዮች ጋር በሰው ሃይል ልማት እና ጀርመን በምትታወቅበት የሁለትዮሽ የትብብር ሥልጠና አስፈላጊነት ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል፡፡
በሀገራችን በክህሎት ልማት ዘርፍ ትልቅ ሚና ያለው የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ከሙኒክ ቴክኒክኒካል ዩኒቨርሲቲ ጋር መስራት የሚችልበት ሁኔታ ላይ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር መክረናል፡፡ ይህ የትብብር ማዕቀፍ በሁለትዮሽ የትብብር ሥልጠና፣ በጥናትና ምርምር፣ በኢኖቬሽን ፣ የግሉን ሴክተር ተሳትፎ በማሳደግ እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያተኮረ ሲሆን ትብብሩ እንደ ሀገር በክህሎት ልማት ዘርፍ የጀመርነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማነት ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት !
በቴክኒክና ሞያ ስልጠና ዘርፍ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያለንን አጋርነት እና ትብብር ለማጠናከር እና ምርጥ ተሞክሮዎችን ለመቅሰም ያለመ የሥራ ጉብኝት በጀርመን ሙኒክ፡፡
በቆይታችን ከኢንዱስትሪ መሪዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና የማህበራት ተወካዮች ጋር በሰው ሃይል ልማት እና ጀርመን በምትታወቅበት የሁለትዮሽ የትብብር ሥልጠና አስፈላጊነት ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል፡፡
በሀገራችን በክህሎት ልማት ዘርፍ ትልቅ ሚና ያለው የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ከሙኒክ ቴክኒክኒካል ዩኒቨርሲቲ ጋር መስራት የሚችልበት ሁኔታ ላይ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር መክረናል፡፡ ይህ የትብብር ማዕቀፍ በሁለትዮሽ የትብብር ሥልጠና፣ በጥናትና ምርምር፣ በኢኖቬሽን ፣ የግሉን ሴክተር ተሳትፎ በማሳደግ እና በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያተኮረ ሲሆን ትብብሩ እንደ ሀገር በክህሎት ልማት ዘርፍ የጀመርነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማነት ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡
የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት !
ከሐምሌ ወር ጀምሮ 169 የፌደራል ተቋማት ግዥዎቻቸውን በኤሌክትርኒክስ ስርዓት ይፈፅማሉ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ 169 የሚሆኑ የፌዴራል የመንግስት ተቋማት ግዥዎቻቸውን በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት እንደሚፈጽሙ ተገለፀ።
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከአቅራቢና ከአቅራቢ ማህበራት ጋር በኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርአት ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ይገኛል።
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ ባደረጉት ንግግር፤ 169 የፌዴራል የመንግስት ተቋማት ከመጪው የሐምሌ ወር ጀምረው የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሰርአትን ይከተላሉ ብለዋል።
ባለፋት አስር ወራት 70 የፌዴራል የመንግስት ተቋማትና 10 ሺህ በላይ አቅራቢዎች በኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈፅመቸውን ጠቁመው በኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈፀማቸው ከ5 እሰከ 25 በመቶ የሚሆነውን የመንግስት በጀት ወጪ ማስቀረት ችለዋል ሲሉ ተናግረዋል።
ከመንግስት ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ60 እስከ 70 በመቶ የሚሆነው በጀት ለግዥ የሚውል በመሆኑ በጀቱ ለታለመለት አላማ እንዲውል በኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈጸም አስፈላጊ ነው ብለዋል።
አንድ የመንግስት ተቋም ከወረቀት ወደ ኤሌክትሮኒክስ ግዥ በመግባት ማንኘውንም ግዥ ሲፈፅም የበጀቱን 5 እሰከ 25 በመቶ ያተርፋል፤ በቀላሉ 5 በመቶ የሚሆን ወጪን ቢቆጠብ 40 ሚልየን ብር ቆጠበ ማለት ነው፤ ይህ ደግሞ ለመንግስት ዓመታዊ በጀት ትልቅ ድጋፍ ነው ሲሉ አብራርተዋል።
የክልል የመንግሰት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ ከወረቀት የግዥ ሰርአት በማላቀቅ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ሰርአትን እንዲከተሉ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው፤ በ2017 ዓ.ም ሁሉም ተቋማት ሙሉ ለሙሉ የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ስርአትን ተከትለው ግዥ እንደሚፈጽሙ አሳውቀዋል።
የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሰርአት ብልሹ የግዥ ሰርአትን በመቅረፍ የመንግስት በጀት በታለመለት አገልግሎት እንዲውል በማድረግ የሀገርን ስልጣኔ ያመጣል ሲሉ ገልፀዋል።
ከፌዴራል የመንግስት ተቋማት በተሻለ የግል አቅራቢዎች የግዥ ሰርአቱ ላይ በንቃት እየተሳተፉ ነው ያሉት ዋና ዳሬክተሩ፤ ተሳትፏችሁን በማጠናከር ሌብነትን ሙሉ ለሙሉ ማጥፋት ባይቻልም በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ይገባናል ሲሉም አመላክተዋል።
በታደሰ ብናልፈው
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ 169 የሚሆኑ የፌዴራል የመንግስት ተቋማት ግዥዎቻቸውን በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት እንደሚፈጽሙ ተገለፀ።
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ከአቅራቢና ከአቅራቢ ማህበራት ጋር በኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርአት ዙሪያ ውይይት እያካሄደ ይገኛል።
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ ባደረጉት ንግግር፤ 169 የፌዴራል የመንግስት ተቋማት ከመጪው የሐምሌ ወር ጀምረው የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሰርአትን ይከተላሉ ብለዋል።
ባለፋት አስር ወራት 70 የፌዴራል የመንግስት ተቋማትና 10 ሺህ በላይ አቅራቢዎች በኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈፅመቸውን ጠቁመው በኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈፀማቸው ከ5 እሰከ 25 በመቶ የሚሆነውን የመንግስት በጀት ወጪ ማስቀረት ችለዋል ሲሉ ተናግረዋል።
ከመንግስት ዓመታዊ በጀት ውስጥ ከ60 እስከ 70 በመቶ የሚሆነው በጀት ለግዥ የሚውል በመሆኑ በጀቱ ለታለመለት አላማ እንዲውል በኤሌክትሮኒክስ ግዥ መፈጸም አስፈላጊ ነው ብለዋል።
አንድ የመንግስት ተቋም ከወረቀት ወደ ኤሌክትሮኒክስ ግዥ በመግባት ማንኘውንም ግዥ ሲፈፅም የበጀቱን 5 እሰከ 25 በመቶ ያተርፋል፤ በቀላሉ 5 በመቶ የሚሆን ወጪን ቢቆጠብ 40 ሚልየን ብር ቆጠበ ማለት ነው፤ ይህ ደግሞ ለመንግስት ዓመታዊ በጀት ትልቅ ድጋፍ ነው ሲሉ አብራርተዋል።
የክልል የመንግሰት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ ከወረቀት የግዥ ሰርአት በማላቀቅ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ሰርአትን እንዲከተሉ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው፤ በ2017 ዓ.ም ሁሉም ተቋማት ሙሉ ለሙሉ የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ስርአትን ተከትለው ግዥ እንደሚፈጽሙ አሳውቀዋል።
የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሰርአት ብልሹ የግዥ ሰርአትን በመቅረፍ የመንግስት በጀት በታለመለት አገልግሎት እንዲውል በማድረግ የሀገርን ስልጣኔ ያመጣል ሲሉ ገልፀዋል።
ከፌዴራል የመንግስት ተቋማት በተሻለ የግል አቅራቢዎች የግዥ ሰርአቱ ላይ በንቃት እየተሳተፉ ነው ያሉት ዋና ዳሬክተሩ፤ ተሳትፏችሁን በማጠናከር ሌብነትን ሙሉ ለሙሉ ማጥፋት ባይቻልም በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ይገባናል ሲሉም አመላክተዋል።
በታደሰ ብናልፈው
የጥላቻ ንግግርን እና የሐሰተኛ መረጃን የተመለከተ ሀገራዊ ሪፖርት ይፋ ተደርጓል
****************
ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን በሚመለከት በጥናት ላይ የተመሰረተ ሪፖርት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት አቅርቧል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናታን ተስፋዬ እንደገለፁት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በአዋጅ ከተቋቋመበት ዓላማ አንፃር በሀገራችን የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ሀገራዊ ሪፓርት ያቀርባል።
በመሆኑም ሪፖርቱ ባለፈው አንድ ዓመት የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ምን መልክ ነበረው የሚለውን ያካተተ ሲሆን ለውይይት ቀርቦ የመፍትሄ ሃሳቦችንና አቅጣጫዎችን ለመውሰድ ያለመ ነው።
አቶ ዮናታን አክለውም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃን የመከላከል ስራ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን ሁሉም ዜጎችና የተለያዩ ተቋማትንም የሚመለከት በመሆኑ ሁላችንም ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የተገኙት ባለድርሻ አካላት በማህበራዊ ሚዲያ ስለሚሰራጭ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ አሁናዊ ሪፖርት ላይ በቂ ግንዛቤ አግኝተው ድርጊቱን ከመከላከል ረገድ በቂ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከባለሥልጣኑ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡
****************
ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን በሚመለከት በጥናት ላይ የተመሰረተ ሪፖርት የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት አቅርቧል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናታን ተስፋዬ እንደገለፁት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በአዋጅ ከተቋቋመበት ዓላማ አንፃር በሀገራችን የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ሀገራዊ ሪፓርት ያቀርባል።
በመሆኑም ሪፖርቱ ባለፈው አንድ ዓመት የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ምን መልክ ነበረው የሚለውን ያካተተ ሲሆን ለውይይት ቀርቦ የመፍትሄ ሃሳቦችንና አቅጣጫዎችን ለመውሰድ ያለመ ነው።
አቶ ዮናታን አክለውም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃን የመከላከል ስራ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን ብቻ የሚመለከት ሳይሆን ሁሉም ዜጎችና የተለያዩ ተቋማትንም የሚመለከት በመሆኑ ሁላችንም ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የተገኙት ባለድርሻ አካላት በማህበራዊ ሚዲያ ስለሚሰራጭ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ አሁናዊ ሪፖርት ላይ በቂ ግንዛቤ አግኝተው ድርጊቱን ከመከላከል ረገድ በቂ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከባለሥልጣኑ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡