ከ90 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የሐዋሳ ከተማ መግቢያ በር በነገው ዕለት ይመረቃል
************
(ኢ ፕ ድ)
ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ በነገው ዕለት እንደሚመረቅ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡
በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ታሪኩ ታመነ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በከተማው በ2014 ዓ.ም የተጀመሩትን አብዛኛዎቹን ፕሮጀክቶች በዚህ ዓመት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ ነው፡፡
በከተማ በተለይም በUNDP የሚደገፉ 29 ፕሮጀክቶች መኖራቸው ጠቁመው፣ ከአስፋልት መንገድ ግንባታ ውጪ ያሉት ሌሎች ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቁ ገልጸዋል፡፡
ከሁሉም ለየት የሚለውና ጥቁር ውሃ መግቢያ በር ላይ እየተገነባ የሚገኘው ሚሊኒየም ፓርክ ሪስቶሬሽን ፕሮጀክት ለከተማውና ለክልሉ እንዲሁም እንደ ሀገርም ትልቅ ትርጉም ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡
ሰኔ 2014 ዓ.ም የአንድ ዓመት የግንባታ ውል የተገባለት ፕሮጀክት ከ90 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል። ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ግንባታ የሲዳማን ባህላዊ ዕሴቶችን ማሳየት የሚችልና በአሁኑ ወቅት ዓለም የደረሰበትን ሙሉ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተገነባ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡
ወደ ሐዋሳ ከተማ መግቢያ በር የሆነው ፕሮጀክት በሀገሪቱ ካሉት መሰል ፕሮጀክቶች የመጀመሪያው ይሆናል።
በተጨማሪም የትምህርት፡ የጤናና ሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለሕብረተሰቡ ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋልም ብለዋል አቶ ታሪኩ፡፡
በጥቁር ዉሃ ዳቶ ሐዋሳ መግብያ በር ሙሉ በሙሉ ዲጂታል ተክኖሎጂ የተገጠመለት በመሆኑ ወጪና ገቢ የትራፊክ ፍሰት ከመቆጣጠሩም በላይ የከተማዉን ብሎም የህብረተሰቡን ደህንነት ለተጠበቀ ያግዛል በለዋል። ከፍትኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።
በከተማው ግንባታቸው በመጠናቀቅ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል 15 ሎት ጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ፤ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ የሚሠሩ ሼዶች፤ 8 የታክሲ ተርሚናሎች፤ የሕዝብ መዝናኛ ሥፍራዎች፣ 3 ቦታ የሚተከሉ የትራፊክ እንዲሁም ሌሎች የመንገድ ዳር መብራቶች፡ ዘመናዊና ውብ የሆኑ የእግረኛ መንገዶች እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡
በአምሳሉ ፈለቀ
************
(ኢ ፕ ድ)
ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ በነገው ዕለት እንደሚመረቅ የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡
በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ታሪኩ ታመነ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በከተማው በ2014 ዓ.ም የተጀመሩትን አብዛኛዎቹን ፕሮጀክቶች በዚህ ዓመት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ ታቅዶ እየተሠራ ነው፡፡
በከተማ በተለይም በUNDP የሚደገፉ 29 ፕሮጀክቶች መኖራቸው ጠቁመው፣ ከአስፋልት መንገድ ግንባታ ውጪ ያሉት ሌሎች ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቁ ገልጸዋል፡፡
ከሁሉም ለየት የሚለውና ጥቁር ውሃ መግቢያ በር ላይ እየተገነባ የሚገኘው ሚሊኒየም ፓርክ ሪስቶሬሽን ፕሮጀክት ለከተማውና ለክልሉ እንዲሁም እንደ ሀገርም ትልቅ ትርጉም ያለው ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡
ሰኔ 2014 ዓ.ም የአንድ ዓመት የግንባታ ውል የተገባለት ፕሮጀክት ከ90 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል። ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ግንባታ የሲዳማን ባህላዊ ዕሴቶችን ማሳየት የሚችልና በአሁኑ ወቅት ዓለም የደረሰበትን ሙሉ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተገነባ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡
ወደ ሐዋሳ ከተማ መግቢያ በር የሆነው ፕሮጀክት በሀገሪቱ ካሉት መሰል ፕሮጀክቶች የመጀመሪያው ይሆናል።
በተጨማሪም የትምህርት፡ የጤናና ሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለሕብረተሰቡ ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋልም ብለዋል አቶ ታሪኩ፡፡
በጥቁር ዉሃ ዳቶ ሐዋሳ መግብያ በር ሙሉ በሙሉ ዲጂታል ተክኖሎጂ የተገጠመለት በመሆኑ ወጪና ገቢ የትራፊክ ፍሰት ከመቆጣጠሩም በላይ የከተማዉን ብሎም የህብረተሰቡን ደህንነት ለተጠበቀ ያግዛል በለዋል። ከፍትኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።
በከተማው ግንባታቸው በመጠናቀቅ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል 15 ሎት ጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ፤ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ የሚሠሩ ሼዶች፤ 8 የታክሲ ተርሚናሎች፤ የሕዝብ መዝናኛ ሥፍራዎች፣ 3 ቦታ የሚተከሉ የትራፊክ እንዲሁም ሌሎች የመንገድ ዳር መብራቶች፡ ዘመናዊና ውብ የሆኑ የእግረኛ መንገዶች እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡
በአምሳሉ ፈለቀ
የቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 93 በመቶ ላይ ደርሷል
********************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን እየተገነባ ያለው የቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 93 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ፡፡
የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ አራት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰድሳ ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ስምንት ብር ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ፡፡
ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሚዩኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (CCCC) ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ሽላዲያ አሶሴት ከኢንሲራድ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ሲስተም እና ሂትከን ኢንጅነሪንግ ጋር በጣምራ እያከናወኑት ይገኛሉ ፡፡
መንገዱ በዋናነት ቢላሎ ከተማን፣ ኤጎ ከተማን፣ ቀርሳ ከተማን እና ጎልጆታ ከተማን የሚያገናኝ ሲሆን ይኸውም የአሰላና ሻሸመኔ ከተማን ለማገናኘት ቀላል ያደርገዋል፡፡
ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚያልፍባቸው ዞን እና ወረዳዎች በስንዴ፣ ገብስ እና ድንች አምራችነት ከሚታወቁ ቦታዎች ውስጥ ስለሆኑ እነዚህን የግብርና ምርቶች ወደ መሃል ሃገር ገበያ ለማምጣት ጉልህ ሚና አለው፡፡
********************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን እየተገነባ ያለው የቢላሎ - ቀርሳ - አርሲ ነገሌ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ አፈጻጸም 93 በመቶ ላይ የደረሰ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ፡፡
የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ አራት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰድሳ ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ስምንት ብር ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ፡፡
ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሚዩኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ (CCCC) ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ሽላዲያ አሶሴት ከኢንሲራድ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ሲስተም እና ሂትከን ኢንጅነሪንግ ጋር በጣምራ እያከናወኑት ይገኛሉ ፡፡
መንገዱ በዋናነት ቢላሎ ከተማን፣ ኤጎ ከተማን፣ ቀርሳ ከተማን እና ጎልጆታ ከተማን የሚያገናኝ ሲሆን ይኸውም የአሰላና ሻሸመኔ ከተማን ለማገናኘት ቀላል ያደርገዋል፡፡
ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚያልፍባቸው ዞን እና ወረዳዎች በስንዴ፣ ገብስ እና ድንች አምራችነት ከሚታወቁ ቦታዎች ውስጥ ስለሆኑ እነዚህን የግብርና ምርቶች ወደ መሃል ሃገር ገበያ ለማምጣት ጉልህ ሚና አለው፡፡
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ ድጋፍ ማድረጓን እንደምትቀጥል ገለጸች
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ (UNMISS) ድጋፍ ማድረጓን አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታወቀች።
በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ ከዩኤንሚስ(UNMISS) ምክትል ኃላፊና ከተመድ የደቡብ ሱዳን ምክትል ልዩ ተወካይ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ተወያይተዋል።
ሁለቱ ባለስልጣናት በቀጣናው ባለው የሰላም እና ደህንነት ሁኔታ ላይ መወያየታቸው ተገልጿል።
ጉዋንግ ኮንግ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን እየተወጣች ያለው ወሳኝ ሚና እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ለዩኤንሚስ እያደረጉት ያለውን ትልቅ አበርክቶ አድንቀዋል።
በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው መረጋጋት እንዲሰፍን አበክራ እየሰራች ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ዩኤንሚስ ለሚያከናውናቸው ስራዎች በቀጣይ ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግስታት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ(ዩኤንሚስ) በተመድ የጸጥታ ምክር ቤት ውሳኔ የተቋቋመው እ.አ.አ በ2011 ነው።
እንደ ኢዜአ ዘገባ የተልዕኮው አላማ በደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት አማካኝነት አገሪቷ ዳግም ወደ እርስ በእርስ ጦርነት እንዳትመለስ መከላከል፣ ጠንካራ ሰላም መገንባት እንዲሁም ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ነጻ ምርጫ እንዲካሄድ ድጋፍ ማድረግ ናቸው።
ኢትዮጵያ ለዩኤንሚስ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰላም አስከባሪ ኃይል ካበረከቱ አገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች።
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ (UNMISS) ድጋፍ ማድረጓን አጠናክራ እንደምትቀጥል አስታወቀች።
በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ ከዩኤንሚስ(UNMISS) ምክትል ኃላፊና ከተመድ የደቡብ ሱዳን ምክትል ልዩ ተወካይ ጉዋንግ ኮንግ ጋር ተወያይተዋል።
ሁለቱ ባለስልጣናት በቀጣናው ባለው የሰላም እና ደህንነት ሁኔታ ላይ መወያየታቸው ተገልጿል።
ጉዋንግ ኮንግ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን እየተወጣች ያለው ወሳኝ ሚና እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ለዩኤንሚስ እያደረጉት ያለውን ትልቅ አበርክቶ አድንቀዋል።
በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው መረጋጋት እንዲሰፍን አበክራ እየሰራች ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ዩኤንሚስ ለሚያከናውናቸው ስራዎች በቀጣይ ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ገልጸዋል።
በተባበሩት መንግስታት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ(ዩኤንሚስ) በተመድ የጸጥታ ምክር ቤት ውሳኔ የተቋቋመው እ.አ.አ በ2011 ነው።
እንደ ኢዜአ ዘገባ የተልዕኮው አላማ በደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት አማካኝነት አገሪቷ ዳግም ወደ እርስ በእርስ ጦርነት እንዳትመለስ መከላከል፣ ጠንካራ ሰላም መገንባት እንዲሁም ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና ነጻ ምርጫ እንዲካሄድ ድጋፍ ማድረግ ናቸው።
ኢትዮጵያ ለዩኤንሚስ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰላም አስከባሪ ኃይል ካበረከቱ አገራት መካከል በዋናነት ትጠቀሳለች።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት‼️
‘ገበታ ለሸገር’ እና ‘ገበታ ለሀገር’ የቱሪዝም ሴክተር ልማት ሥራዎች በአብዛኛው ተጠናቅቀዋል። ይሄን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ 8 የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለማልማት የ‘ገበታ ለትውልድ’ ሐሳባችንን ገፍተንበታል። የዐርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርትን በ120 ሄክታር መሬት ላይ፣ የአባያ ሐይቅን እያየ በሚያማምር ቦታ ላይ እንዲገነባ ዛሬ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠናል።
በዓመት ከመንፈቅ ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቀው ይህ ፕሮጄክት 1.3 ትሪሊዮን ዶላር የሚሸፍነውን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ዘርፍ ገቢን ተቋዳሽ እንድንሆን ያደርገናል። ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ሀብታችንን በመጠቀም ሀብት የማፍራት ጅምሮችን በማስፋፋት፣ የብልጽግና ጉዟችንን ለማሳካት እንተጋለን።
‘ገበታ ለሸገር’ እና ‘ገበታ ለሀገር’ የቱሪዝም ሴክተር ልማት ሥራዎች በአብዛኛው ተጠናቅቀዋል። ይሄን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ 8 የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለማልማት የ‘ገበታ ለትውልድ’ ሐሳባችንን ገፍተንበታል። የዐርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርትን በ120 ሄክታር መሬት ላይ፣ የአባያ ሐይቅን እያየ በሚያማምር ቦታ ላይ እንዲገነባ ዛሬ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠናል።
በዓመት ከመንፈቅ ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቀው ይህ ፕሮጄክት 1.3 ትሪሊዮን ዶላር የሚሸፍነውን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ዘርፍ ገቢን ተቋዳሽ እንድንሆን ያደርገናል። ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ሀብታችንን በመጠቀም ሀብት የማፍራት ጅምሮችን በማስፋፋት፣ የብልጽግና ጉዟችንን ለማሳካት እንተጋለን።
ከንቲባ አዳነች በዛሬው እለት ከ17 ሺህ በላይ የሰላምና ፀጥታ አካላት ጋር ችግኝ ተከሉ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከ17 ሺህ በላይ የሰላምና ፀጥታ አካላት ጋር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ችግኝ ተከሉ።
በዛሬው እለት 100 ሺህ ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን የሰላምና ፀጥታ አካላቱ አንድ ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ እንደያዙም ተገልጿል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በከተማዋ በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ 17 ሚሊዮን ሀገር በቀል ዛፎች፣ ለምግብነት የሚውሉ እና ለውበት የሚሆኑ ችግኞችን በከተማችን የተለያዩ አካባቢዎች የሚተከሉ ይሆናል።
አዲስ አበባን አረንጓዴ በማልበስ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ውብ ከተማ ለማድረግ ሁላችንም ችግኝ መትከል አለብን ያሉ ሲሆን ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክበን እንዲጸድቁ እና ፍሬ እንዲያፈሩ ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ብለዋል።
በሳሙኤል ወንደሰን
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከ17 ሺህ በላይ የሰላምና ፀጥታ አካላት ጋር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ችግኝ ተከሉ።
በዛሬው እለት 100 ሺህ ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን የሰላምና ፀጥታ አካላቱ አንድ ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ እንደያዙም ተገልጿል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በከተማዋ በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ 17 ሚሊዮን ሀገር በቀል ዛፎች፣ ለምግብነት የሚውሉ እና ለውበት የሚሆኑ ችግኞችን በከተማችን የተለያዩ አካባቢዎች የሚተከሉ ይሆናል።
አዲስ አበባን አረንጓዴ በማልበስ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ውብ ከተማ ለማድረግ ሁላችንም ችግኝ መትከል አለብን ያሉ ሲሆን ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክበን እንዲጸድቁ እና ፍሬ እንዲያፈሩ ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ብለዋል።
በሳሙኤል ወንደሰን