የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት‼️
‘ገበታ ለሸገር’ እና ‘ገበታ ለሀገር’ የቱሪዝም ሴክተር ልማት ሥራዎች በአብዛኛው ተጠናቅቀዋል። ይሄን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ 8 የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለማልማት የ‘ገበታ ለትውልድ’ ሐሳባችንን ገፍተንበታል። የዐርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርትን በ120 ሄክታር መሬት ላይ፣ የአባያ ሐይቅን እያየ በሚያማምር ቦታ ላይ እንዲገነባ ዛሬ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠናል።
በዓመት ከመንፈቅ ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቀው ይህ ፕሮጄክት 1.3 ትሪሊዮን ዶላር የሚሸፍነውን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ዘርፍ ገቢን ተቋዳሽ እንድንሆን ያደርገናል። ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ሀብታችንን በመጠቀም ሀብት የማፍራት ጅምሮችን በማስፋፋት፣ የብልጽግና ጉዟችንን ለማሳካት እንተጋለን።
‘ገበታ ለሸገር’ እና ‘ገበታ ለሀገር’ የቱሪዝም ሴክተር ልማት ሥራዎች በአብዛኛው ተጠናቅቀዋል። ይሄን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ 8 የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለማልማት የ‘ገበታ ለትውልድ’ ሐሳባችንን ገፍተንበታል። የዐርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርትን በ120 ሄክታር መሬት ላይ፣ የአባያ ሐይቅን እያየ በሚያማምር ቦታ ላይ እንዲገነባ ዛሬ የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠናል።
በዓመት ከመንፈቅ ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቀው ይህ ፕሮጄክት 1.3 ትሪሊዮን ዶላር የሚሸፍነውን ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ዘርፍ ገቢን ተቋዳሽ እንድንሆን ያደርገናል። ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ሀብታችንን በመጠቀም ሀብት የማፍራት ጅምሮችን በማስፋፋት፣ የብልጽግና ጉዟችንን ለማሳካት እንተጋለን።
ከንቲባ አዳነች በዛሬው እለት ከ17 ሺህ በላይ የሰላምና ፀጥታ አካላት ጋር ችግኝ ተከሉ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከ17 ሺህ በላይ የሰላምና ፀጥታ አካላት ጋር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ችግኝ ተከሉ።
በዛሬው እለት 100 ሺህ ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን የሰላምና ፀጥታ አካላቱ አንድ ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ እንደያዙም ተገልጿል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በከተማዋ በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ 17 ሚሊዮን ሀገር በቀል ዛፎች፣ ለምግብነት የሚውሉ እና ለውበት የሚሆኑ ችግኞችን በከተማችን የተለያዩ አካባቢዎች የሚተከሉ ይሆናል።
አዲስ አበባን አረንጓዴ በማልበስ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ውብ ከተማ ለማድረግ ሁላችንም ችግኝ መትከል አለብን ያሉ ሲሆን ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክበን እንዲጸድቁ እና ፍሬ እንዲያፈሩ ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ብለዋል።
በሳሙኤል ወንደሰን
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከ17 ሺህ በላይ የሰላምና ፀጥታ አካላት ጋር በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ችግኝ ተከሉ።
በዛሬው እለት 100 ሺህ ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን የሰላምና ፀጥታ አካላቱ አንድ ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ እንደያዙም ተገልጿል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በከተማዋ በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ 17 ሚሊዮን ሀገር በቀል ዛፎች፣ ለምግብነት የሚውሉ እና ለውበት የሚሆኑ ችግኞችን በከተማችን የተለያዩ አካባቢዎች የሚተከሉ ይሆናል።
አዲስ አበባን አረንጓዴ በማልበስ ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ውብ ከተማ ለማድረግ ሁላችንም ችግኝ መትከል አለብን ያሉ ሲሆን ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክበን እንዲጸድቁ እና ፍሬ እንዲያፈሩ ማድረግ የሁላችንም ሃላፊነት ነው ብለዋል።
በሳሙኤል ወንደሰን
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሲዲሲ ድጋፍ ማድረጓን ትቀጥላለች
-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
***********************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ በሽታ መቆጣጠር እና መከላከል ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) የምታደርገውን ድጋፍ እንደምታጠናክር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።
አቶ ደመቀ ከአፍሪካ ሲዲሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጂን ካሴያ ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
በውይይቱም በአዲስ አበባ የተገነባው አዲሱ የአፍሪካ ሲዲሲ የዋና መቀመጫ ሕንጻ በአፍሪካ የጤና አጀንዳ ለማራመድ የሚያስችል ዐብይ ፕሮጀክት መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ማዕከሉ እያከናወናቸው ላሉ ስራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቁመው የአፍሪካ ሲዲሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጂን ኬሲያ የኢትዮጵያ መንግሥት ለማዕከሉ እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
አፍሪካ ሲዲሲ ለአባል አገራት አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ መስጠቱን እንደሚቀጥል መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠር እና መከላከል ማዕከል የአፍሪካ ሕብረት ገለልተኛ የጤና ተቋም ሆኖ እ.አ.አ 2016 መቋቋሙ ይታወሳል። ማዕከሉ የሕብረቱ አባል አገራት በሽታን አስቀድሞ ማወቅ፣መከላከል እና መቆጣጠር የሚያስችላቸውን አቅም እንዲገነቡ እና የማህበረሰብ ጤና መርሐ-ግብሮች ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍ ያደርጋል።
-ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
***********************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ ለአፍሪካ በሽታ መቆጣጠር እና መከላከል ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) የምታደርገውን ድጋፍ እንደምታጠናክር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።
አቶ ደመቀ ከአፍሪካ ሲዲሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጂን ካሴያ ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
በውይይቱም በአዲስ አበባ የተገነባው አዲሱ የአፍሪካ ሲዲሲ የዋና መቀመጫ ሕንጻ በአፍሪካ የጤና አጀንዳ ለማራመድ የሚያስችል ዐብይ ፕሮጀክት መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ማዕከሉ እያከናወናቸው ላሉ ስራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቁመው የአፍሪካ ሲዲሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጂን ኬሲያ የኢትዮጵያ መንግሥት ለማዕከሉ እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
አፍሪካ ሲዲሲ ለአባል አገራት አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ መስጠቱን እንደሚቀጥል መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠር እና መከላከል ማዕከል የአፍሪካ ሕብረት ገለልተኛ የጤና ተቋም ሆኖ እ.አ.አ 2016 መቋቋሙ ይታወሳል። ማዕከሉ የሕብረቱ አባል አገራት በሽታን አስቀድሞ ማወቅ፣መከላከል እና መቆጣጠር የሚያስችላቸውን አቅም እንዲገነቡ እና የማህበረሰብ ጤና መርሐ-ግብሮች ውጤታማ እንዲሆኑ ድጋፍ ያደርጋል።
ኢትዮጵያ የናይል ኮሚሽንን ለማቋቋም ዲፕሎማሲያዊ ጥረቷን አጠናክራ ቀጥላለች
********************
(ኢ ፕ ድ)
የተፋሰሱን ሀገራት ትስስር ለማጠናከርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ የናይል ኮሚሽንን ለማቋቋም ዲፕሎማሲያዊ ጥረቷን አጠናክራ እንደቀጠለች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ፍስሐ ሻወል አስታወቁ፡፡
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ፍስሐ ሻወል ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ከግብፅ በስተቀር ሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=104083
********************
(ኢ ፕ ድ)
የተፋሰሱን ሀገራት ትስስር ለማጠናከርና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ የናይል ኮሚሽንን ለማቋቋም ዲፕሎማሲያዊ ጥረቷን አጠናክራ እንደቀጠለች በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ዳይሬክተር ጄነራል አምባሳደር ፍስሐ ሻወል አስታወቁ፡፡
በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ፍስሐ ሻወል ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ከግብፅ በስተቀር ሁሉም የተፋሰሱ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=104083
የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ ግንባታ ተጠናቅቆ በዛሬው ዕለት ተመርቋል
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በሐዋሳ ከተማ ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ ግንባታ ተጠናቅቆ
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተመርቋል።
በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ተገንብተው የተጠናቀቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶችም ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በዛሬው ዕለት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ በተገኙበት የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በይፋ የተመረቀው የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ በግራና ቀኝ የሲዳማን ባህላዊ የቤት አሰራርን፣ አናቱ ላይ ደግሞ የሻፌታን ቅርጽ የያዘ ሲሆን የ "እንኳን ደህና መጣችሁ" ን መልዕክትንም ያዘለ ነው።
የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደወጣበት ለማወቅ ተችሏል።
በተመረቁ ፕሮጀክቶች መሐል ለሀዋሳ ከተማ አዲስ ገፅታ የሆነው የከተማ መግቢያ በር፣ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከተገነቡ ት/ቤቶች ታቦር አንደኛ ደረጃ G+3 የመማሪያ ህንፃና ሌሎች ፕሮጀክቶች ምረቃ እየተካሄደ ይገኛል።
በአስቴር ኤልያስ (ሐዋሳ)
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በሐዋሳ ከተማ ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ ግንባታ ተጠናቅቆ
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተመርቋል።
በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ተገንብተው የተጠናቀቁ የተለያዩ ፕሮጀክቶችም ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በዛሬው ዕለት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ረ/ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ በተገኙበት የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በይፋ የተመረቀው የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ በግራና ቀኝ የሲዳማን ባህላዊ የቤት አሰራርን፣ አናቱ ላይ ደግሞ የሻፌታን ቅርጽ የያዘ ሲሆን የ "እንኳን ደህና መጣችሁ" ን መልዕክትንም ያዘለ ነው።
የሐዋሳ ከተማ መግቢያ ሚሊኒየም ፓርክ ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደወጣበት ለማወቅ ተችሏል።
በተመረቁ ፕሮጀክቶች መሐል ለሀዋሳ ከተማ አዲስ ገፅታ የሆነው የከተማ መግቢያ በር፣ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከተገነቡ ት/ቤቶች ታቦር አንደኛ ደረጃ G+3 የመማሪያ ህንፃና ሌሎች ፕሮጀክቶች ምረቃ እየተካሄደ ይገኛል።
በአስቴር ኤልያስ (ሐዋሳ)
የፖሊስ ዩኒቨርሲቲው ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታ እያከናወነ ነው
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ በመበጀት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያቀፉ ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ፡፡ በሰው ኃይል ልማትም ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ባለሙያዎችን እያሰለጠነ መሆኑን ተነግሯል፡፡
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ የፌዴራል ፖሊስ በጥናት ምርምር ሥራዎች ላይ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=104137
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ በመበጀት ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያቀፉ ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ፡፡ በሰው ኃይል ልማትም ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ባለሙያዎችን እያሰለጠነ መሆኑን ተነግሯል፡፡
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ የፌዴራል ፖሊስ በጥናት ምርምር ሥራዎች ላይ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=104137
ሄራልድ-ለስምንት አስርተ ዓመታት የፀናው የፍትሕ ድምፅ
***************
(ኢ ፕ ድ)
አረጋዊ ነው፤ የሰማንያ ዓመታቱ ጌታ፡፡ ፈር ቀዳጅ ነው፤ ልበሙሉ ነጻነት የተቸረው። የጭቁኖች ልሳን ነው፤ መሰማት ለሻተ ሁሉ ድምፅ ሲሆን የኖረ፡፡ የፍትህ ጋሻ ጃግሬ ነው፤ የባርነት ቀንበር ለተጫናቸው እንደአንበሳ ያገሳ። ድልድይ ነው፤ ሀገሪቱን ከተቀረው የዓለም ክፍል ጋር ያገናኘ፡፡ ባለራዕይ ነው፤ ጥቁሮች ለተነጠቁት የነፃነት ጮራ የብርሃ መስኮትን ያጋራ፡፡
ዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ መጠሪያ ስሙ ነው። የኢትዮጵያን ስም ተሸካሚው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የአብራክ ክፋይ፡፡ እንግሊዘኛ መተየቢያ ቋንቋው ነው። ጥቁሮች ስለ ነፃነት ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=104096
***************
(ኢ ፕ ድ)
አረጋዊ ነው፤ የሰማንያ ዓመታቱ ጌታ፡፡ ፈር ቀዳጅ ነው፤ ልበሙሉ ነጻነት የተቸረው። የጭቁኖች ልሳን ነው፤ መሰማት ለሻተ ሁሉ ድምፅ ሲሆን የኖረ፡፡ የፍትህ ጋሻ ጃግሬ ነው፤ የባርነት ቀንበር ለተጫናቸው እንደአንበሳ ያገሳ። ድልድይ ነው፤ ሀገሪቱን ከተቀረው የዓለም ክፍል ጋር ያገናኘ፡፡ ባለራዕይ ነው፤ ጥቁሮች ለተነጠቁት የነፃነት ጮራ የብርሃ መስኮትን ያጋራ፡፡
ዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ መጠሪያ ስሙ ነው። የኢትዮጵያን ስም ተሸካሚው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የአብራክ ክፋይ፡፡ እንግሊዘኛ መተየቢያ ቋንቋው ነው። ጥቁሮች ስለ ነፃነት ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=104096