በአዲስ አበባ ከተማ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ182 የመፈተ ኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀመረ
***************************
(ኢ ፕ ድ)
አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው የ2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዛሬው እለት በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 182 የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
ዘንድሮ በከተማ አስተዳደር በ182 የፈተና ጣቢያዎች 75 ሺህ 090 ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ከምክትል ቢሮ ኃላፊው ከአቶ አሊ ከማል እና ከየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከአቶ ፈይሳ ወዳጆ ጋር በክፍለከተማው በሚገኙ የመፈተኛ ጣቢያዎች ተዘዋውረው የፈተናውን አጀማመር ተመልክተዋል።
የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዘንድሮ እንደመጀመሩና ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች በእድሜ አነስተኛ እንደመሆናቸው ቢሮው ፈተናው ያለምንም ችግር እንዲጠናቀቅ የጸጥታ አካላትን ጨምሮ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ሲሰራ ቆይቷል።
በከተማ አስተዳደሩ ላለፉት ሁለት ቀናት የተካሄደው የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያለምንም እንከን ተጠናቋል።
የ6ኛ ክፍል ፈተናም በተመሳሳይ ሁኔታ ያልምንም ችግር እንዲጠናቀቅ ሁሉም የፈተና አስፈጻሚ ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
***************************
(ኢ ፕ ድ)
አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠው የ2015 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዛሬው እለት በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 182 የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
ዘንድሮ በከተማ አስተዳደር በ182 የፈተና ጣቢያዎች 75 ሺህ 090 ተማሪዎች የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ከምክትል ቢሮ ኃላፊው ከአቶ አሊ ከማል እና ከየካ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ከአቶ ፈይሳ ወዳጆ ጋር በክፍለከተማው በሚገኙ የመፈተኛ ጣቢያዎች ተዘዋውረው የፈተናውን አጀማመር ተመልክተዋል።
የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዘንድሮ እንደመጀመሩና ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች በእድሜ አነስተኛ እንደመሆናቸው ቢሮው ፈተናው ያለምንም ችግር እንዲጠናቀቅ የጸጥታ አካላትን ጨምሮ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ሲሰራ ቆይቷል።
በከተማ አስተዳደሩ ላለፉት ሁለት ቀናት የተካሄደው የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ያለምንም እንከን ተጠናቋል።
የ6ኛ ክፍል ፈተናም በተመሳሳይ ሁኔታ ያልምንም ችግር እንዲጠናቀቅ ሁሉም የፈተና አስፈጻሚ ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አዲሱ የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስ ዛሬ በይፋ ይመረቃል
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ሸጎሌ አካባቢ የተገነባው አዲሱ የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ይመረቃል። ዘመናዊ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ተቋሙ በአፍሪካ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስችለዋል።
ሰሞኑን የምረቃው አካል የሆኑ የተለያዩ ዝግጅቶች ሲካሄዱ መቆየታቸው ይታወቃል።
በተራራ የተከበበውና በእጽዋት ያጌጠው አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ዓለም በደረሰበት የሚዲያ ቴክኖሎጂ የተደራጀ ነው።
ለሚዲያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን በመፍጠር ተቋማዊ አፈፃፀም እንዲያድግ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ኢቢሲ "ለኢትዮጵያ ልዕልና" በሚል መሪ ቃል በአዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክሱ በሁሉም ሚዲየሞቹ አዳዲስ ይዘቶችን እና አቀራረቦችን አካቶ ወደ አድማጭ ተመልካች ለመድረስ ዝግጅቱን አጠናቋል።
ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ ሸጎሌ አካባቢ የተገነባው አዲሱ የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ይመረቃል። ዘመናዊ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ተቋሙ በአፍሪካ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስችለዋል።
ሰሞኑን የምረቃው አካል የሆኑ የተለያዩ ዝግጅቶች ሲካሄዱ መቆየታቸው ይታወቃል።
በተራራ የተከበበውና በእጽዋት ያጌጠው አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ዓለም በደረሰበት የሚዲያ ቴክኖሎጂ የተደራጀ ነው።
ለሚዲያው ሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢን በመፍጠር ተቋማዊ አፈፃፀም እንዲያድግ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ኢቢሲ "ለኢትዮጵያ ልዕልና" በሚል መሪ ቃል በአዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክሱ በሁሉም ሚዲየሞቹ አዳዲስ ይዘቶችን እና አቀራረቦችን አካቶ ወደ አድማጭ ተመልካች ለመድረስ ዝግጅቱን አጠናቋል።
ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ የመጀመሪያውን የትምህርት ፌስቲቫል ማካሄድ ጀመረ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ የኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ልዩ አዳሪና የኦሮሚያ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያውን የትምህርት ፌስቲቫል ማካሄድ ጀመረ።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም እየተካሄደ ባለው ፌስቲቫል የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ፣ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶ፣ የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በዚህ ፌስቲቫል የኦሮሚያ ኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችና ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ በዛሬው እለት የተጀመረው ይህ ፌስቲቫል ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መሆኑ ተጠቁሟል።
በቃልኪዳን አሳዬ (አዳማ)
ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ የኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ልዩ አዳሪና የኦሮሚያ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያውን የትምህርት ፌስቲቫል ማካሄድ ጀመረ።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስታዲየም እየተካሄደ ባለው ፌስቲቫል የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ፣ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶ፣ የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በዚህ ፌስቲቫል የኦሮሚያ ኢፋ ቦሩ ሁለተኛ ደረጃ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶችና ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ በዛሬው እለት የተጀመረው ይህ ፌስቲቫል ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ መሆኑ ተጠቁሟል።
በቃልኪዳን አሳዬ (አዳማ)
ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም