Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ አዲሱን የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስ መረቁ
******************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ ሸጎሌ አካባቢ የተገነባው አዲሱን የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስን
መርቀው ከፍተዋል።

ዘመናዊ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ተቋሙ በአፍሪካ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያስችለዋል ተብሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ለምክር ቤት የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀርባሉ
****************
(ኢ ፕ ድ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት የመንግስትን የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምክር ቤቱ ዛሬ በሚያካሂደው 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌደራል መንግስት የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለምክር ቤቱ የመንግስትን የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ የሚያቀርቡትን ሪፖርትና ማብራሪያ በሁሉም የማህበራዊ ገጾቻችን ይከታተላሉ።

ለሲዳሙ አፎ https://www.facebook.com/Epasidaamu/

ለአፋን ኦሮሞ https://www.facebook.com/Epabariisaa/

ለትግርኛ https://www.facebook.com/Epatigrigna/ 

ለእንግሊዘኛ https://www.facebook.com/epaEnglish/ 

ለአፋርኛ ቋንቋ https://www.facebook.com/profile.php?id=100092595632078

ለሶማልኛ ቋንቋ https://www.facebook.com/profile.php id=100092677890373

ለአረብኛ https://www.facebook.com/Epaalalam/
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባ‼️
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት እያካሄደ ነው።
የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ነው።
የምክር ቤተ አባላት፤ የሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አሰጣጥን ለማስቀረት የተሠራውን ሥራ፣ ሙስና ለመዋጋት የተቋቋመው ኮሚቴ ያከናወነውን ተግባራት፣ በሱዳን የሚኖሩ ዜጎችን በሚመለከት ምን እየተሰራ እንደሆነ፣ የፕሪቶሪያው ስምምነት አፈፃፀምና የትግራይ ክልል ያለበት ሁኔታን አስመልክተው ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በተለይ ከኤርትራ ጋር ያለን ግንኙነት እንዴት ይታያል ፣ የማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭት፣ የመስኖ ግንባታ ፕሮጀክቶች መጓተት፣ በሀገሪቱ የሚሰተዋሉ የሰላም ችግሮችን በተመለከተ፣ በተለያየ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ክልሎች መልሶ ሟቋቋም፣ የህዝቡን ኑሮ ውድነት ለማሻሻል፣ ህገወጥ ንግድ በሀገሪቱ እየተሰፋፋ ለሀገር ስጋት እየሆነ ስለመምጣቱ፤ መንግስት ህገወጥ ንግድን ለመቆጣጠር ምን እየሰራ እንደሆነ፣ በጀቱ የዋጋ ግሽበትን ከግምት ውስጥ ያስገባ አለመሆን፣ የስራ አጥነትን በዘላቂነት ለመፍታት ምርታማነትን ለማሳደግ ምን ታስቧል፣ የንብረት ግብር ላይ የሚነሱ ችግሮች፣ የተፈናቀሉትን ዜጎችን ወደ ቀያቸው መመላስ ላይ የተሰሩ ስራዎችን የተመለከቱ እና ሌሎች ጉዳዮችን የሚመለከቱ ጥያቄዎችንም አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ.ም
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባው‼️

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት እያካሄደ ነው።

የምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ነው።

እንደ ሀገር የተጀመረው የህግ ማስከበር ስራ ምን ላይ ይገኛል፣ ዜጎች ያለአግባብ መታገትና ገንዘብ መጠየቅ፣ የክልሎች ልዩ ሀይሎች አደረጃጃት በምን ደረጃ ላይ ይገኛል። በተለይም በዚህ ምክንያት በአማራ ክልል የተፈጠረውን ችግር በምን አይነት መንገድ እየተፈታ ነው፤ ከሸኔ ጋር የተጀመረው ውይይት ሂደቱ ቢብራራ፤ በአዲስ አበባና በሸገር ህገወጥ በሚል ቤት የፈረሰባቸውና የፈረሱ የሀይማኖት ተቋማት እጣ ፈንታ ምንድነው የሚሉ ጥያቄዎች ከምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀርበዋል።

በተመሳሳይ ኤክስፖርት በሚደረገው ምርት የአሰራር ችግሮች ዙሪያ የተነሱ የሙስና ችግሮችና የአሰራር ክፍተቶች እየተበራከቱ በመሆናቸው ችግሮቹ እንዲፈቱና የአሰራር ሂደቶቹ እንዲስተካከሉ መመሪያ ቢሰጥ፤ ለግብርና ከተሰጠው ትኩረት አንጻር 2015 መቅረብ የነበረበት የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ አለመቅረብና ገበያውም ለሙስና ተጋልጧል፤ የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋትና ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ለማገዝ ምን እየተሰራ ይገኛል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች‼️

👉 የኢኮኖሚ ዘርፍ ዋና ግብ በአድርጎ የተነሳነው የግሉን ዘርፍ ማነቃቃት ነው፣

👉 ማክሮ ኢኮኖሚ ላይ የተፈጠሩ ስብራቶችን ማሻሻልና ምርታማነትን ማብዛት፣

👉 ሁለተኛው ሀገር በቀል ማሻሻያ እቅድ ዋና ግቡ የኢኮኖሚ ስብራቶችን መጠገን ነው፣

👉 የመጀመሪያው አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ይዞት የተነሳው አላማ የግሉን ዘርፍ ማነቃቃት ዋና ግቡ ነበር፤ ሁለተኛው ግቡ የተሰበሩ ኢኮኖሚዎችን ማነቃቃትና መጠገን፤ ሶስተኛው በሰፊውና በብዝሃ ዘርፍ ምርታማነትን ማሳደግ ነው፣

👉 ይህ እቅድ በርካታ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ተግዳሮቶች ቢገጥሙትም በምክር ቤቱ አባላት እንደተነሳው ብዙ ጥቅሞች አስገኝቷል፣

👉ሁለተኛው አገር በቀል ማሻሻያ ዋና ግቦቹ የኢኮኖሚ ስብራቶችን መጠገን ነው፡፡

👉 የዘንድሮ በጀት የቀረበው የሶስቱን አመት ማሻሻያ የአለምን እድገትን በሚመለከት ብዙ ትንበያ ተሰጥቷል፣

👉 በአለም እድገት እያመጡ ከተባሉ ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ ናት፣ በዚህ አመት 7 ነጥበ 5 እድገት ይመጣል ብለን እንጠብቃለን፣

👉 ግብርና በኢትዮጵያ ውስጥ 33 በመቶ ድርሻ፤ ኢንዱስትሪ 28 በመቶ፣

👉 ግብርና 6.3 በመቶ እድገት ያመጣል፤ በሩዝ በስንዴ በማር በዶሮ እርባታ ከፍተኛ ለውጥ ታይቷል

👉 በኢንዱስትሪ ዘርፍ 160 ፋብሪካዎች ስራ እንዲጀምሩ ተደርጓል፣

👉 የዋጋ ንረት በየትኛውም ሀገር ችግር ነው፤የዋጋ ንረት ያልነካው ሀገር የለም፣

👉 የውጪ ምንዛሪ እጥት ያጋጠማቸው 90 ሀገራት ለክፉ ቀን ብለው ያስቀመጡትን አውጥተው ተጠቅመዋል፣

👉 እነዚህ 90 ሀገራት 80 በመቶ የእነሱ ሀገር ከረንሲ ቀንሷል፣ ለዚህም ነው በዶላር መገባያየት ማቆም አለብን የሚለው የሚሰማው፣

👉 ከ90 ሀገራት መካካል 60 ዎቹ እዳ አለባቸው ከእነሱም ውስጥ 20 ዎቹ እዳ መክፈል አልቻሉም፣ በዚህ ውስጥ የኢትዮጵያን ነገር ማየት ያስፈልጋል፣
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች‼️

👉 ባላፉት 11 ወራት 365 ነጥብ 8 ቢሊዮን ገቢ ተገኝቷል፣ ካለፈው ዓመት 26 ነጥብ 1 በመቶ እድገት አለው፣

👉ባንኮች 31 ደርሰዋል፣ የብድር መጠን ለግሉ ዘርፍ 85 በመቶ፣ ለመንግስት 15 በመቶ ተሰጥቷል፣

👉 በቁጠባ የተሰበሰበው ገንዘብ ከአራት ዓመት በፊት ዝቅተኛ ነበር፤ አሁን 2.1 ትሪሊየን ደርሷል፣

👉 የባንኮች ጠቅላላ ሀብት ከአንድ ነጥብ ሁለት ትሪሊየን ወደ 2.9 ትሪሊየን ደርሷል፣

👉 የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት 10.4 በመቶ አድጓል፣

👉 በቴሌ ብር ከሦስት ሚሊየን ብር በላይ ትናንሽ ብድሮች ተሰጥተዋል፣

👉 ከባንክ ውጪ የሚንቀሳቀሰውን ሀብት መቆጣጠር፣

👉 ማዳበሪያ ላይ 21 ቢሊዮኝ ብር ፤ ነዳጅ 77 ቢሊዮኝ ብር ደጉመናል፣

👉 በበጀት ዓመቱ በርካታ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ቢገጥሙንም፤ ሀገር በቀል ኢኮኖሚውን በማጠናከር ችግሮቹን መሻገር ተችሏል፣

👉 የዋጋ ንረት በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳው ገቢያቸውን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚኖረወን የማህበረሰብ ክፍልና የመንግስት ሠራተኛውን ጭምር ነው፣

👉 የፓርላማ አባላት ጥያቄ ሊሆነ የሚቸለው ሰንት ማዕድ አካፍያለሁ ነው እንጂ ሰለኑሮ ውድነት ስለጠየቅ አይደለም፣

👉 የዋጋ ንረት በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳው ገቢያቸው አነስተኛ የሆኑትን ነው፣

👉 በዚህ ዓመት ቢያንስ ከሁለት ሚሊዮን በላይ መሬትን በመሰኖና በተለያዩ አካባቢዎች አናረሳለን፣
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች‼️

👉 የኢትዮጵያ ዕዳ ለውጡ ሲመጣ 59 በመቶ ነበር፣ ዛሬ ላይ 38 በመቶ ደርሶዋል፤

👉 ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት፤ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከ1000 ዶላር በላይ ሆኗል፣

👉 ባለፉት 11 ወራት ለ3 ነጥብ 3 ሚሊዮኝ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል፣

👉 የስራ ዕድል ፈጠራ ክህሎት በሚኒስቴር ከፍተኛ ለውጥ እያመጡ ካሉ ተቋማት መካከል አንዱ ነው፣

👉 ተቋሙ ሁለት ሚሊዮን ገደማ የሰራተኛ ጥያቄ ቀርቦለታል፣ በአመት 3 ሚሊዮን አዳዲስ ስራ ፈላጊዎች ይኖራሉ፣

👉 የማዳበሪያ ማጓጓዝን በተመለከተ ከአሁን በፊት ከነበረው እጅግ በተሻለ መልኩ እየተሰራ ነው፣

👉 በለውጡ ሰሞን ለማዳበሪያ 450 ሚሊዮን ዶላር ወጭ ተደረጓል፣

👉 በአሁኑ ወቅት 1 ቢሊዮን ዶላር ገንዘብ ወጭ መደረጉ የተሰጠውን ትኩረት ያሳያል ነው ብለዋል፡፡

👉 በበጀት ዓመቱ 12 ነጥብ 9 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ከተገዛ በኋላ ለትግራይ ክልል ታሳቢ አድርገን ተጨማሪ 800 ሺሕ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ተገዝቷል፣

👉 በኢትዮጵያ ያለውን ምርታማነት ለመጨመር ለዘርፉ ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነው፣

👉 178 ሚሊዮኝ ሜትር ኩቢክ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቷል፣

👉 ማዳበሪያ ከራሺያ አከባቢ ስለሚመጣ በዛ አከባቢ ባለ ሁኔታ ችግር ሆኖዋል፣