ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢጋድ የሱዳንን ግጭት ለመፍታት ያቋቋመውን የአራትዮሽ የመሪዎች ጉባኤን ዛሬ ጠዋት በአዲስ አበባ ማስተናገዳቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል ::
በክልሉ ካሉ ትምህርት ቤቶች መስፈርቱን የሚያሟሉት 29ኙ ብቻ ናቸው
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካሉ 643 የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የትምህርት ተቋምነት መስፈርትን የሚያሟሉት 29ኙ ብቻ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ አጠቃላይ ትምህርት ጥራት ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ ሉሌ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በክልሉ ጥናት ከተደረገባቸው 643 የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተቀመጠውን ደረጃ የሚያሟሉት 29ኙ ብቻ ናቸው።
ትምህርት ቤቶቹ ደረጃ የተቀመጠላቸው ባሟሉት ግብአት፣ በመሠረተ ልማታቸውና ተማሪዎች ባስመዘገቡት ውጤት ተመዝነው መሆኑን ገልጸው ፤ በዚህም ከ601 የመጀመሪያ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 572ቱ ደረጃ የወጣላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ደረጃ ከወጣላቸው ትምህርት ቤቶች ውስጥ 143 ቱ ከ50 በመቶ በታች ውጤት ያላቸው በመሆኑ ደረጃ አንድ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። እነዚህ ትምህርት ቤቶችም ከፍተኛ የሚባል የትምህርት መሠረተ ልማት ችግር ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል።
403 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ደግሞ ደረጃ ሁለት ላይ የተቀመጡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ደረጃውን ለማሟላት በሂደት ላይ በመሆናቸው መስፈርቱን ከሃምሳ እስከ 70 በመቶ ድረስ አሟልተዋል ነው ያሉት።
አቶ ዮሐንስ አንድ ትምህርት ቤት መስፈርቱን አሟላ የሚባለው ደረጃ ሦስት ላይ ሲደርስ መሆኑን አመልክተው፤ በክልሉም ካሉ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 26ቱ ብቻ ደረጃ ሦስት ላይ መቀመጣቸውን ገልጸዋል። ሆኖም አንድም ትምህርት ቤት ደረጃ 4 ላይ አለመድረሱን አስታውቀዋል።
በክልሉ ካሉ 92 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 73ቱ ደረጃ የወጣላቸው መሆኑን ጠቁመው፤ ከእነዚህ ውስጥም 15 ትምህርት ቤቶች ደረጃውን ሳያሟሉ ቀርተው ደረጃ አንድ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አቶ ዮሐንስ 55 የሚሆኑት ደግሞ ደረጃ ሁለትን ለማሟላት እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፣ ደረጃቸውን አሟልተው ደረጃ 3 ላይ የተቀመጡት ትምህርት ቤቶች 3 ብቻ ናቸው። በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ደረጃ አራት የገባ ትምህርት ቤት አለመኖሩን ጨምረው ገልጸዋል።
እንደ አቶ ዮሐንስ ገለጻ፤ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶች የግብአት ችግር ያለባቸው ናቸው። ይህም የሆነው በፊት የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከጥራት ይልቅ ተደራሽነት ላይ ያተኮረ በመሆኑ ነው።
አቶ ዮሐንስ የትምህርት ቤቶች ደረጃ እንደ ሀገር ችግር ያለበት ቢሆንም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከፍተኛ ችግር መኖሩን ጠቅሰዋል።
ይህንን ለማስተካከል የክልሉ ትምህርት ቢሮ የራሱን ጥረት እያደረገ ነው። በተጠናው ጥናት መሠረትም በትምህርት ቤቶች የሚፈለገውን መሠረተ ልማት ለማሟላት ማስተካከያ እንዲደረግ ለሚመለከተው አካል ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይ እንደ ሀገር የተጀመረው የትምህርት ቤቶች ደረጃ የማሻሻል ንቅናቄ ለውጥ ያመጣል ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካሉ 643 የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የትምህርት ተቋምነት መስፈርትን የሚያሟሉት 29ኙ ብቻ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ አጠቃላይ ትምህርት ጥራት ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዮሐንስ ሉሌ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በክልሉ ጥናት ከተደረገባቸው 643 የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተቀመጠውን ደረጃ የሚያሟሉት 29ኙ ብቻ ናቸው።
ትምህርት ቤቶቹ ደረጃ የተቀመጠላቸው ባሟሉት ግብአት፣ በመሠረተ ልማታቸውና ተማሪዎች ባስመዘገቡት ውጤት ተመዝነው መሆኑን ገልጸው ፤ በዚህም ከ601 የመጀመሪያ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 572ቱ ደረጃ የወጣላቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ደረጃ ከወጣላቸው ትምህርት ቤቶች ውስጥ 143 ቱ ከ50 በመቶ በታች ውጤት ያላቸው በመሆኑ ደረጃ አንድ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል። እነዚህ ትምህርት ቤቶችም ከፍተኛ የሚባል የትምህርት መሠረተ ልማት ችግር ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል።
403 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ደግሞ ደረጃ ሁለት ላይ የተቀመጡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ደረጃውን ለማሟላት በሂደት ላይ በመሆናቸው መስፈርቱን ከሃምሳ እስከ 70 በመቶ ድረስ አሟልተዋል ነው ያሉት።
አቶ ዮሐንስ አንድ ትምህርት ቤት መስፈርቱን አሟላ የሚባለው ደረጃ ሦስት ላይ ሲደርስ መሆኑን አመልክተው፤ በክልሉም ካሉ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 26ቱ ብቻ ደረጃ ሦስት ላይ መቀመጣቸውን ገልጸዋል። ሆኖም አንድም ትምህርት ቤት ደረጃ 4 ላይ አለመድረሱን አስታውቀዋል።
በክልሉ ካሉ 92 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 73ቱ ደረጃ የወጣላቸው መሆኑን ጠቁመው፤ ከእነዚህ ውስጥም 15 ትምህርት ቤቶች ደረጃውን ሳያሟሉ ቀርተው ደረጃ አንድ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አቶ ዮሐንስ 55 የሚሆኑት ደግሞ ደረጃ ሁለትን ለማሟላት እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን፣ ደረጃቸውን አሟልተው ደረጃ 3 ላይ የተቀመጡት ትምህርት ቤቶች 3 ብቻ ናቸው። በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችም ደረጃ አራት የገባ ትምህርት ቤት አለመኖሩን ጨምረው ገልጸዋል።
እንደ አቶ ዮሐንስ ገለጻ፤ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶች የግብአት ችግር ያለባቸው ናቸው። ይህም የሆነው በፊት የነበረው የትምህርት ሥርዓት ከጥራት ይልቅ ተደራሽነት ላይ ያተኮረ በመሆኑ ነው።
አቶ ዮሐንስ የትምህርት ቤቶች ደረጃ እንደ ሀገር ችግር ያለበት ቢሆንም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከፍተኛ ችግር መኖሩን ጠቅሰዋል።
ይህንን ለማስተካከል የክልሉ ትምህርት ቢሮ የራሱን ጥረት እያደረገ ነው። በተጠናው ጥናት መሠረትም በትምህርት ቤቶች የሚፈለገውን መሠረተ ልማት ለማሟላት ማስተካከያ እንዲደረግ ለሚመለከተው አካል ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይ እንደ ሀገር የተጀመረው የትምህርት ቤቶች ደረጃ የማሻሻል ንቅናቄ ለውጥ ያመጣል ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
በተያዘው የምርት ዘመን የደቡብ ጎንደር ዞን 50 ሺ ሄክታር መሬት በሩዝ ምርት ይሸፈናል
****************
(ኢ ፕ ድ)
በተያዘው የምርት ዘመን በደቡብ ጎንደር ዞን ብቻ በተለያዩ ሰብሎች ዘር የሚሸፈን 526 ሺ ሄክታር መሬት ዝግጁ የተደረገ ሲሆን እስካሁን 65 በመቶው በዘር ተሸፍኗል ተባለ።
በዛሬው ዕለት በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦ ከምከም ወረዳ ቡራ ቀበሌ የሩዝ ክላስተር ዘር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ አመራሮች፣ ባለድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።
ከ 526 ሺ ሄክታር መሬት ውስጥ በተያዘው የምርት ዘመን 50 ሺ ሄክታር መሬት በሩዝ ዘር የመሸፈን እቅድ ተይዞ በመከናወን ላይ ይገኛል።
ካለፈው የምርት ዘመን ጋር ሲነጻጸርም የዘንድሮው የሩዝ ዘር ሽፋን እድገት ያሳየ መሆኑ ተገልጿል። ባለፈው የምርት ዘመን 42 ሺ ሄክታር መሬት በሩዝ ምርት የተሸፈነ መሆኑም የሚታወስ ነው።
የሩዝ ክላስተር ዘር ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ሌየሰ የተገኙት የደቡብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ተፈራ እንደገለጹት በዞኑ የሩዝ ምርት እድገት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን በሄክታር 28 ኩንታል ምርት ይገኝ የነበረው በአሁኑ ጊዜ በሄክታር 35 ኩንታል ድረስ መማረት መቻሉን ገልጸዋል።
ባለፋት ዓመታት መንግሥት ለሩዝ ምርት ልዩ ትኩረት በመስጠት ብሔራዊ የሩዝ ምርምር ማዕከል በአካባቢው በማቋቋም ምርታማነትን የሚያሳድጉና በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸውን ዘር ማሻሻል፣ የአስተራረስና የአዘራር ስልትን ማሳደግ፣ የእሴት መጨመርና የገበያ ትስስርን ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
የሊቦ ከምከም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ፀሐይ ቸኮልም በበኩላቸው የሩዝ ምርታማነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን የሩዝ ምርትን ጥራት በማሳደግና እሴት በመጨመር ለገበያ ለማቅረብ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ያስፈልጋሉ ብለዋል።
ሩዝ ከተመረተ በኋላ አሁን ባለው ገበያ ሳይቀናበር በኪሎ 35 ብር የሚሸጥ ሲሆን ከተቀናበረ በኋላ ደግሞ በኪሎ ከ 75 እስከ 80 ብር ይሸጣል ያሉት ዋና አስተዳዳሪዋ የገበሬውንና የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚነት ለማስፋት የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።
የዘር አቅርቦትን ማሳደግና የጎርፍ መጥለቅለቅን መከላከልም የሩዝ ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አስተዳዳሪዋ ገልጸዋል።
ሩዝ ማምረት በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ አካባቢ በ1976 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን 38 ዓመታትን አሳልፏል። በአሁኑ ጊዜ ደቡብ ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኙት ሩዝ አምራች ወረዳዎች ብቻ የሃገሪቱን 65 በመቶ የሩዝ ምርት በመሸፈን ላይ ይገኛሉ ሲል የክልሉ ኮመንኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
****************
(ኢ ፕ ድ)
በተያዘው የምርት ዘመን በደቡብ ጎንደር ዞን ብቻ በተለያዩ ሰብሎች ዘር የሚሸፈን 526 ሺ ሄክታር መሬት ዝግጁ የተደረገ ሲሆን እስካሁን 65 በመቶው በዘር ተሸፍኗል ተባለ።
በዛሬው ዕለት በደቡብ ጎንደር ዞን ሊቦ ከምከም ወረዳ ቡራ ቀበሌ የሩዝ ክላስተር ዘር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ አመራሮች፣ ባለድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።
ከ 526 ሺ ሄክታር መሬት ውስጥ በተያዘው የምርት ዘመን 50 ሺ ሄክታር መሬት በሩዝ ዘር የመሸፈን እቅድ ተይዞ በመከናወን ላይ ይገኛል።
ካለፈው የምርት ዘመን ጋር ሲነጻጸርም የዘንድሮው የሩዝ ዘር ሽፋን እድገት ያሳየ መሆኑ ተገልጿል። ባለፈው የምርት ዘመን 42 ሺ ሄክታር መሬት በሩዝ ምርት የተሸፈነ መሆኑም የሚታወስ ነው።
የሩዝ ክላስተር ዘር ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ሌየሰ የተገኙት የደቡብ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አዲስ ተፈራ እንደገለጹት በዞኑ የሩዝ ምርት እድገት ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን በሄክታር 28 ኩንታል ምርት ይገኝ የነበረው በአሁኑ ጊዜ በሄክታር 35 ኩንታል ድረስ መማረት መቻሉን ገልጸዋል።
ባለፋት ዓመታት መንግሥት ለሩዝ ምርት ልዩ ትኩረት በመስጠት ብሔራዊ የሩዝ ምርምር ማዕከል በአካባቢው በማቋቋም ምርታማነትን የሚያሳድጉና በሽታን የመቋቋም አቅም ያላቸውን ዘር ማሻሻል፣ የአስተራረስና የአዘራር ስልትን ማሳደግ፣ የእሴት መጨመርና የገበያ ትስስርን ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
የሊቦ ከምከም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ወይዘሮ ፀሐይ ቸኮልም በበኩላቸው የሩዝ ምርታማነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን የሩዝ ምርትን ጥራት በማሳደግና እሴት በመጨመር ለገበያ ለማቅረብ የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ያስፈልጋሉ ብለዋል።
ሩዝ ከተመረተ በኋላ አሁን ባለው ገበያ ሳይቀናበር በኪሎ 35 ብር የሚሸጥ ሲሆን ከተቀናበረ በኋላ ደግሞ በኪሎ ከ 75 እስከ 80 ብር ይሸጣል ያሉት ዋና አስተዳዳሪዋ የገበሬውንና የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚነት ለማስፋት የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል።
የዘር አቅርቦትን ማሳደግና የጎርፍ መጥለቅለቅን መከላከልም የሩዝ ምርታማነትን ለመጨመር ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን አስተዳዳሪዋ ገልጸዋል።
ሩዝ ማምረት በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ አካባቢ በ1976 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን 38 ዓመታትን አሳልፏል። በአሁኑ ጊዜ ደቡብ ጎንደር ዞን ውስጥ የሚገኙት ሩዝ አምራች ወረዳዎች ብቻ የሃገሪቱን 65 በመቶ የሩዝ ምርት በመሸፈን ላይ ይገኛሉ ሲል የክልሉ ኮመንኬሽን ቢሮ ዘግቧል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ለተፈናቀሉ ወገኖች 20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገች
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በትግራይ ክልል በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የ20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስታን ፓትሪያሪክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ድጋፉን ዛሬ ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ አስረክበዋል።
ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ እንዳሉት ድጋፉ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል ነው።
“የሃይማኖት መሪዎች ግጭት ሳይሆን ሰላም፣ ውድመት ሳይሆን ልማት ለማረጋገጥ ሃላፊነት አለብን” ያሉት ብፁእነታቸው ወደፊትም አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርእሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የሃይማኖት መሪዎች ለሰላምና ልማት መረጋገጥ ሚናቸው የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።
የተጀመረው መልካም ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በትግራይ ክልል በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የ20 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስታን ፓትሪያሪክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ድጋፉን ዛሬ ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ አስረክበዋል።
ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ እንዳሉት ድጋፉ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል ነው።
“የሃይማኖት መሪዎች ግጭት ሳይሆን ሰላም፣ ውድመት ሳይሆን ልማት ለማረጋገጥ ሃላፊነት አለብን” ያሉት ብፁእነታቸው ወደፊትም አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርእሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የሃይማኖት መሪዎች ለሰላምና ልማት መረጋገጥ ሚናቸው የላቀ መሆኑን ተናግረዋል።
የተጀመረው መልካም ተግባር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም