«ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር የጤና ሥርዓታችንን ማጠናከር ችለናል»
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኮቪድ ወቅትን መጥፎ ክስተት ወደ ዕድል በመቀየር የጤና ሥርዓቱን ማጠናከር እንደተቻለ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ አስታወቁ። ከኮቪድ በኋላ የጽኑ ሕሙማን ክፍል በእጥፍ አድጓል።
የቢሮ ኃላፊው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኮቪድ 19 ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ዓለምን በከፍተኛ ሁኔታ የፈተነ ወረርሽኝ ነበር። ወረርሽኙ ለኢትዮጵያ የጤና ሥርዓት ዕድልም ሆኖ አልፏል።
የወረርሽኙን መጥፎ ክስተት እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀምና ወደ ዕድል በመቀየር የጤና ሥርዓቱን ማጠናከር ተችሏል።
ዓለም በወረርሽኙ ሳቢያ በሩን ዘግቶ በመቆየቱ የተለያዩ ግብዓቶችን ለማግኘት አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተከስተዋል ያሉት የቢሮ ኃላፊው፤ ኮቪድ 19 የዓለም የጤና ችግር ብቻ ሳይሆን፤ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ማስከተሉን፤ ከቫይረሱ ጫና በርካታ የዓለም ኩባንያዎች እስካሁን ማንሰራራት አለመቻላቸውን ገልጸዋል።
ወረርሽኙ ያስከተለው ዓለም አቀፋዊ ቀውስ እንዳለ ሆኖ እንደ ሀገር ዕድል ማምጣቱንም ተናግረዋል።
የቢሮ ኃላፊው፤ «በወረርሽኙ ወቅት ምን ዓይነት የጤና ሥርዓት እንዳለን አይተንበታል። ብዙ ዕድሎች አምጥቶልን አቅማችንን እንድናደራጅ አድርጎናል።
እንደ ከተማም ሆነ እንደ ሀገር በፊት የነበሩንን የጽኑ ሕሙማን ክፍሎች ከእጥፍ በላይ ማሳደግ ችለናል። በቀጣይ እንደ ኮቪድ ዓይነት ወረርሽኝ ሲመጣ ምን ማድረግ እንደሚገባ ትልቅ ትምህርት ተወስዷል» ብለዋል።
በኮቪድ ወቅት ምን ዓይነት የጤና ሥርዓት እንዳለና መጥፎ ክስተቶችን ወደ ዕድል በመውሰድ የጤና ሥርዓቱን ማጠናከር እንደሚቻል ትልቅ ትምህርት ተወስዷል ነው ያሉት። ከዚህ በኋላ ለሚፈጠሩ የጤና ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት ትልቅ አቅም መፈጠሩንም አመልክተዋል።
በወረርሽኙ በርካታ ባለሙያዎች የሕዝብን ጤና ለማቆየት ሕይወታቸውን እንደሰጡ ጠቅሰው፤ ወቅቱ መሰል ክስተቶች ሲመጡ ምን መደረግ እንዳለበት ትልቅ ትምህርት የተገኘበት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
እንደ ቢሮ ኃላፊው ገለጻ፤ በቋሚነት ማንኛውም ዓይነት በሽታ ከመከሰቱ በፊት የዳሰሳ ጥናት የሚሠራ ቡድን ከፌዴራል ጀምሮ እስከታችኛው የመንግሥት መዋቅር ያለ ሲሆን፤ ይህ ተጠናክሮ ሥራውን ያስቀጥላል።
ዓለም ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ፈታኝ የሆኑ ክስተቶች ሲፈጠሩ ጫናው በሀገር ደረጃ ብቻ ሳይሆን እንደ ዓለምአቀፍ ነው የሚታየው ያሉት ዶክተር ዮሐንስ፤ ኮቪድ 19 በዓለምአቀፍ ደረጃ ያስከተለው ጫና እንደ ኢትዮጵያም ቀላል የማይባል እንደሆነ ጠቅሰዋል። ነገር ግን በሌሎች የዓለም ሀገራት የታየው አስከፊ ሁኔታ በኢትዮጵያ አልነበረም ብለዋል።
ይህም በባለሙያውና በጤና ሴክተሩ ጥንካሬና በመንግሥትም ቁርጠኝነት እንደነበር አስታውቀዋል። በኮቪድ ወቅት ሁሉም ያሳየው ቅንጅታዊ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ነው ዶክተር ዮሐንስ የተናገሩት።
በወቅቱ ከግለሰቦች ጀምሮ የተለያዩ ተቋማት ጭምር የሰጡት በጎ ምላሽ አበረታች እንደነበር ዶክተር ዮሐንስ ጠቅሰው፤ መተባበር በጤናው ሥርዓት ላይ ምን ያህል ለውጥ ማምጣት እንደሚችል ያየንበት ነው ብለዋል።
በአዲሱ ገረመው
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኮቪድ ወቅትን መጥፎ ክስተት ወደ ዕድል በመቀየር የጤና ሥርዓቱን ማጠናከር እንደተቻለ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ አስታወቁ። ከኮቪድ በኋላ የጽኑ ሕሙማን ክፍል በእጥፍ አድጓል።
የቢሮ ኃላፊው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኮቪድ 19 ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ዓለምን በከፍተኛ ሁኔታ የፈተነ ወረርሽኝ ነበር። ወረርሽኙ ለኢትዮጵያ የጤና ሥርዓት ዕድልም ሆኖ አልፏል።
የወረርሽኙን መጥፎ ክስተት እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀምና ወደ ዕድል በመቀየር የጤና ሥርዓቱን ማጠናከር ተችሏል።
ዓለም በወረርሽኙ ሳቢያ በሩን ዘግቶ በመቆየቱ የተለያዩ ግብዓቶችን ለማግኘት አስቸጋሪ ሁኔታዎች ተከስተዋል ያሉት የቢሮ ኃላፊው፤ ኮቪድ 19 የዓለም የጤና ችግር ብቻ ሳይሆን፤ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ማስከተሉን፤ ከቫይረሱ ጫና በርካታ የዓለም ኩባንያዎች እስካሁን ማንሰራራት አለመቻላቸውን ገልጸዋል።
ወረርሽኙ ያስከተለው ዓለም አቀፋዊ ቀውስ እንዳለ ሆኖ እንደ ሀገር ዕድል ማምጣቱንም ተናግረዋል።
የቢሮ ኃላፊው፤ «በወረርሽኙ ወቅት ምን ዓይነት የጤና ሥርዓት እንዳለን አይተንበታል። ብዙ ዕድሎች አምጥቶልን አቅማችንን እንድናደራጅ አድርጎናል።
እንደ ከተማም ሆነ እንደ ሀገር በፊት የነበሩንን የጽኑ ሕሙማን ክፍሎች ከእጥፍ በላይ ማሳደግ ችለናል። በቀጣይ እንደ ኮቪድ ዓይነት ወረርሽኝ ሲመጣ ምን ማድረግ እንደሚገባ ትልቅ ትምህርት ተወስዷል» ብለዋል።
በኮቪድ ወቅት ምን ዓይነት የጤና ሥርዓት እንዳለና መጥፎ ክስተቶችን ወደ ዕድል በመውሰድ የጤና ሥርዓቱን ማጠናከር እንደሚቻል ትልቅ ትምህርት ተወስዷል ነው ያሉት። ከዚህ በኋላ ለሚፈጠሩ የጤና ቀውሶች ምላሽ ለመስጠት ትልቅ አቅም መፈጠሩንም አመልክተዋል።
በወረርሽኙ በርካታ ባለሙያዎች የሕዝብን ጤና ለማቆየት ሕይወታቸውን እንደሰጡ ጠቅሰው፤ ወቅቱ መሰል ክስተቶች ሲመጡ ምን መደረግ እንዳለበት ትልቅ ትምህርት የተገኘበት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
እንደ ቢሮ ኃላፊው ገለጻ፤ በቋሚነት ማንኛውም ዓይነት በሽታ ከመከሰቱ በፊት የዳሰሳ ጥናት የሚሠራ ቡድን ከፌዴራል ጀምሮ እስከታችኛው የመንግሥት መዋቅር ያለ ሲሆን፤ ይህ ተጠናክሮ ሥራውን ያስቀጥላል።
ዓለም ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ፈታኝ የሆኑ ክስተቶች ሲፈጠሩ ጫናው በሀገር ደረጃ ብቻ ሳይሆን እንደ ዓለምአቀፍ ነው የሚታየው ያሉት ዶክተር ዮሐንስ፤ ኮቪድ 19 በዓለምአቀፍ ደረጃ ያስከተለው ጫና እንደ ኢትዮጵያም ቀላል የማይባል እንደሆነ ጠቅሰዋል። ነገር ግን በሌሎች የዓለም ሀገራት የታየው አስከፊ ሁኔታ በኢትዮጵያ አልነበረም ብለዋል።
ይህም በባለሙያውና በጤና ሴክተሩ ጥንካሬና በመንግሥትም ቁርጠኝነት እንደነበር አስታውቀዋል። በኮቪድ ወቅት ሁሉም ያሳየው ቅንጅታዊ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ነው ዶክተር ዮሐንስ የተናገሩት።
በወቅቱ ከግለሰቦች ጀምሮ የተለያዩ ተቋማት ጭምር የሰጡት በጎ ምላሽ አበረታች እንደነበር ዶክተር ዮሐንስ ጠቅሰው፤ መተባበር በጤናው ሥርዓት ላይ ምን ያህል ለውጥ ማምጣት እንደሚችል ያየንበት ነው ብለዋል።
በአዲሱ ገረመው
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
በአቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የልዑካን ቡድን በባህርዳር ከተማ ያለውን የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት የስራ እንቅስቃሴ ተመለከተ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በአቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የልዑካን ቡድን በባህርዳር ከተማ ያለውን የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት የስራ እንቅስቃሴ ተመለከተ።
ልዑኩ በከተማ አስተዳደሩም ሆነ በአለም ባንክ በጀት እየተገነቡ ያሉ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችንና በግለሠቦች እየተሠሩ ያሉ "የሌማት ቱሩፋት"ስራዎች የሆኑትን የበሬ ማድለብ ፣የዶሮ እርባታ እና እንቁላል ምርት ፣የወተት ልማት ፣የማርና መሰል የእንስሳት ሀብት ልማቶችን ተመልክቷል።
ልዑኩ ሌላው በጉብኝቱ በከተማው ኢንዱስትሪ መንደር ካሉ ፋብርካዎች መካከል የጌታሰው አያሌው ቶፕ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ፣የሻምበል መንገሻ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፣ ሙሌ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፋብሪካን፣የቢአይካ የግራናይትና እምነ-በረድ ፋብሪካዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል።
በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶችንና የስራ ዕድል የተፈጠረላቸውን ሰራተኞች የማበረታታት ተግባር ማከናወኑንም ከከተማዋ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በአቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የልዑካን ቡድን በባህርዳር ከተማ ያለውን የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት የስራ እንቅስቃሴ ተመለከተ።
ልዑኩ በከተማ አስተዳደሩም ሆነ በአለም ባንክ በጀት እየተገነቡ ያሉ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችንና በግለሠቦች እየተሠሩ ያሉ "የሌማት ቱሩፋት"ስራዎች የሆኑትን የበሬ ማድለብ ፣የዶሮ እርባታ እና እንቁላል ምርት ፣የወተት ልማት ፣የማርና መሰል የእንስሳት ሀብት ልማቶችን ተመልክቷል።
ልዑኩ ሌላው በጉብኝቱ በከተማው ኢንዱስትሪ መንደር ካሉ ፋብርካዎች መካከል የጌታሰው አያሌው ቶፕ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ፣የሻምበል መንገሻ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፣ ሙሌ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፋብሪካን፣የቢአይካ የግራናይትና እምነ-በረድ ፋብሪካዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል።
በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶችንና የስራ ዕድል የተፈጠረላቸውን ሰራተኞች የማበረታታት ተግባር ማከናወኑንም ከከተማዋ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት !!
የከተማችንን የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ለመመልከት እና ለመደገፍ ከፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች የሱፐርቪዢን ቡድን ጋር ውይይት ጀምረናል፡፡
ቡድኑ ለተከታታይ 10 ቀናት ወደ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ወርዶ የሱፐርቪዢን ስራ ያካሂዳል።
የሰራናቸው ስራዎች ብዙ፣ የሔድንበት ርቀት ረጅም ቢሆንም በከተማችን ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን መፍታት ከፍተኛ ጥረት እና በርካታ ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ፣ የፌደራል መንግስት ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተገቢ እና አስፈላጊ ነው።
እየፈጠርንና እየፈጠንን አዲስ አበባን እንደስሟ ውብ፤ ለኑሮና ለስራ ምቹ ከተማ ለማድረግ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን!
የከተማችንን የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ለመመልከት እና ለመደገፍ ከፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች የሱፐርቪዢን ቡድን ጋር ውይይት ጀምረናል፡፡
ቡድኑ ለተከታታይ 10 ቀናት ወደ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ወርዶ የሱፐርቪዢን ስራ ያካሂዳል።
የሰራናቸው ስራዎች ብዙ፣ የሔድንበት ርቀት ረጅም ቢሆንም በከተማችን ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን መፍታት ከፍተኛ ጥረት እና በርካታ ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ፣ የፌደራል መንግስት ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተገቢ እና አስፈላጊ ነው።
እየፈጠርንና እየፈጠንን አዲስ አበባን እንደስሟ ውብ፤ ለኑሮና ለስራ ምቹ ከተማ ለማድረግ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን!
በአፋር ክልል ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ አገልግሎት ተመለሰ
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞችና በአካባቢያቸው በተነሳ ከባድ ነፋስ ተቋርጦ የነበረው የሃይል አቅርቦት ዛሬ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ ተመልሷል::
አገልግሎቱ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ የተመለሰው የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጎዱትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት በመጠገናቸው መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል።
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞች በተነሳ ከባድ ነፋስ በኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እና ማሰራጫ መስመሮች ላይ ጉዳት መድረሱን መገለጹ ተጠቅሷል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞችና በአካባቢያቸው በተነሳ ከባድ ነፋስ ተቋርጦ የነበረው የሃይል አቅርቦት ዛሬ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ ተመልሷል::
አገልግሎቱ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ የተመለሰው የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጎዱትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት በመጠገናቸው መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል።
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞች በተነሳ ከባድ ነፋስ በኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እና ማሰራጫ መስመሮች ላይ ጉዳት መድረሱን መገለጹ ተጠቅሷል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም