በአቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የልዑካን ቡድን በባህርዳር ከተማ ያለውን የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት የስራ እንቅስቃሴ ተመለከተ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በአቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የልዑካን ቡድን በባህርዳር ከተማ ያለውን የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት የስራ እንቅስቃሴ ተመለከተ።
ልዑኩ በከተማ አስተዳደሩም ሆነ በአለም ባንክ በጀት እየተገነቡ ያሉ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችንና በግለሠቦች እየተሠሩ ያሉ "የሌማት ቱሩፋት"ስራዎች የሆኑትን የበሬ ማድለብ ፣የዶሮ እርባታ እና እንቁላል ምርት ፣የወተት ልማት ፣የማርና መሰል የእንስሳት ሀብት ልማቶችን ተመልክቷል።
ልዑኩ ሌላው በጉብኝቱ በከተማው ኢንዱስትሪ መንደር ካሉ ፋብርካዎች መካከል የጌታሰው አያሌው ቶፕ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ፣የሻምበል መንገሻ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፣ ሙሌ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፋብሪካን፣የቢአይካ የግራናይትና እምነ-በረድ ፋብሪካዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል።
በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶችንና የስራ ዕድል የተፈጠረላቸውን ሰራተኞች የማበረታታት ተግባር ማከናወኑንም ከከተማዋ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በአቶ አህመድ ሽዴ የተመራ የልዑካን ቡድን በባህርዳር ከተማ ያለውን የኢንዱስትሪ እና ኢንቨስትመንት የስራ እንቅስቃሴ ተመለከተ።
ልዑኩ በከተማ አስተዳደሩም ሆነ በአለም ባንክ በጀት እየተገነቡ ያሉ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችንና በግለሠቦች እየተሠሩ ያሉ "የሌማት ቱሩፋት"ስራዎች የሆኑትን የበሬ ማድለብ ፣የዶሮ እርባታ እና እንቁላል ምርት ፣የወተት ልማት ፣የማርና መሰል የእንስሳት ሀብት ልማቶችን ተመልክቷል።
ልዑኩ ሌላው በጉብኝቱ በከተማው ኢንዱስትሪ መንደር ካሉ ፋብርካዎች መካከል የጌታሰው አያሌው ቶፕ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ፣የሻምበል መንገሻ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፣ ሙሌ የእንስሳት መኖ ማቀናበሪያ ፋብሪካን፣የቢአይካ የግራናይትና እምነ-በረድ ፋብሪካዎችን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል።
በዘርፉ የተሰማሩ ባለሀብቶችንና የስራ ዕድል የተፈጠረላቸውን ሰራተኞች የማበረታታት ተግባር ማከናወኑንም ከከተማዋ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓም
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት !!
የከተማችንን የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ለመመልከት እና ለመደገፍ ከፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች የሱፐርቪዢን ቡድን ጋር ውይይት ጀምረናል፡፡
ቡድኑ ለተከታታይ 10 ቀናት ወደ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ወርዶ የሱፐርቪዢን ስራ ያካሂዳል።
የሰራናቸው ስራዎች ብዙ፣ የሔድንበት ርቀት ረጅም ቢሆንም በከተማችን ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን መፍታት ከፍተኛ ጥረት እና በርካታ ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ፣ የፌደራል መንግስት ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተገቢ እና አስፈላጊ ነው።
እየፈጠርንና እየፈጠንን አዲስ አበባን እንደስሟ ውብ፤ ለኑሮና ለስራ ምቹ ከተማ ለማድረግ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን!
የከተማችንን የክረምት ስራዎች አፈፃፀም ለመመልከት እና ለመደገፍ ከፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች የሱፐርቪዢን ቡድን ጋር ውይይት ጀምረናል፡፡
ቡድኑ ለተከታታይ 10 ቀናት ወደ ክፍለ ከተሞች እና ወረዳዎች ወርዶ የሱፐርቪዢን ስራ ያካሂዳል።
የሰራናቸው ስራዎች ብዙ፣ የሔድንበት ርቀት ረጅም ቢሆንም በከተማችን ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን መፍታት ከፍተኛ ጥረት እና በርካታ ትብብርን የሚጠይቅ በመሆኑ፣ የፌደራል መንግስት ክትትልና ድጋፍ ማድረጉ ተገቢ እና አስፈላጊ ነው።
እየፈጠርንና እየፈጠንን አዲስ አበባን እንደስሟ ውብ፤ ለኑሮና ለስራ ምቹ ከተማ ለማድረግ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን!
በአፋር ክልል ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ አገልግሎት ተመለሰ
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞችና በአካባቢያቸው በተነሳ ከባድ ነፋስ ተቋርጦ የነበረው የሃይል አቅርቦት ዛሬ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ ተመልሷል::
አገልግሎቱ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ የተመለሰው የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጎዱትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት በመጠገናቸው መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል።
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞች በተነሳ ከባድ ነፋስ በኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እና ማሰራጫ መስመሮች ላይ ጉዳት መድረሱን መገለጹ ተጠቅሷል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
***************
(ኢ ፕ ድ)
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞችና በአካባቢያቸው በተነሳ ከባድ ነፋስ ተቋርጦ የነበረው የሃይል አቅርቦት ዛሬ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ ተመልሷል::
አገልግሎቱ ወደ መደበኛ አገልግሎቱ የተመለሰው የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተጎዱትን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች በፍጥነት በመጠገናቸው መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል።
በአፋር ክልል ሠመራ፣ ሎጊያ፣ ሚሌ፣ ኤሊውሀ፣ አዳይቱ ከተሞች በተነሳ ከባድ ነፋስ በኤሌክትሪክ ምሰሶዎች እና ማሰራጫ መስመሮች ላይ ጉዳት መድረሱን መገለጹ ተጠቅሷል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግም ተከራይ ማስወጣትም እንደማይቻል አስተዳደሩ አስታወቀ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት እንደማይቻል አስተዳደሩ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የኑሮ ውድነቱ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማችን ነዋሪዎች ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ የቤት ኪራይ ጭማሪ እንዳይደረግ በተለያዩ ተከታታይ ጊዜያት ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል::
አሁንም በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት የማይቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት እንደማይቻል አስተዳደሩ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ የኑሮ ውድነቱ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የከተማችን ነዋሪዎች ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ የቤት ኪራይ ጭማሪ እንዳይደረግ በተለያዩ ተከታታይ ጊዜያት ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል::
አሁንም በግል ከሚደረግ ስምምነት ውጪ ማንኛውም አከራይ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የቤት ኪራይ ጭማሪ ማድረግ እንዲሁም ተከራይ ማስወጣት የማይቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አካሄደ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ከአቃቂ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አምስት ሺህ ችግኞች ተከለ።
"ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ2015 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ጽ/ቤቱ ከ50ሺህ በላይ ችግኞችን ለክፍለከተማው ያበረከተ ሲሆን በዛሬው እለትም አምስት ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
በመርሀግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደቦ ቱንካ እንደገለፁት፤ ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከተማዋ ያላትን 15 በመቶ የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ የሚረዳ ነው።
ጽ/ቤቱ ከሚያከናውነው የአካባቢ ልማት የማሳደግ ተግባር በተጨማሪ ሀገራዊ በሆነው መርሀግብር በመሳተፍና ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በመርሀግብሩ የአዲስ አበባ የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ የአቃቂ ክ/ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በማህሌት ብዙነህ
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ከአቃቂ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ በመሆን ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አምስት ሺህ ችግኞች ተከለ።
"ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ2015 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ጽ/ቤቱ ከ50ሺህ በላይ ችግኞችን ለክፍለከተማው ያበረከተ ሲሆን በዛሬው እለትም አምስት ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
በመርሀግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ደቦ ቱንካ እንደገለፁት፤ ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከተማዋ ያላትን 15 በመቶ የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ለማሳደግ የሚረዳ ነው።
ጽ/ቤቱ ከሚያከናውነው የአካባቢ ልማት የማሳደግ ተግባር በተጨማሪ ሀገራዊ በሆነው መርሀግብር በመሳተፍና ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በመርሀግብሩ የአዲስ አበባ የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ የአቃቂ ክ/ከተማ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በማህሌት ብዙነህ
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም