የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በ2016 በጀት ዓመት ከ140 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
- ቢሮው በ2015 በጀት ዓመት ከ107 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰብስቧል
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ የ2015 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ማጠቃለያ እና የ2016 በጀት ዓመት የግብር ማሳወቂያ የንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አደም ኑሪ በመርሃ ግብሩ እንደተናገሩት፤ ቢሮው በ2015 በጀት ዓመት ከገቢዎች ቢሮ ፣ ከማዕከል ገቢ ሰብሳቢ ሴክተሮች፣ ከክፍለ ከተሞች እና ከሌሎች ገቢዎች ጨምሮ በጥቅሉ ከ107 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል።
የተሰበሰበው ገቢ ከ2014 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ53 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ይህም በገንዘብ 37 ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር መሆኑን የገለፁት ኃላፊው፤ የተሰበሰበው ብር ለከተማዋ ዘላቂ የልማት ዘርፎች ማለትም ለትምህርት ቤት፣ ለተማሪዎች ምገባ እና ለትውልድ መተላለፍ ለሚችሉ ኘሮጀክቶች የሚውል ነው። ስለዚህ ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በሚቀጥለው በጀት ዓመት አጠናክረው ሊከፍሉ ይገባል ብለዋል።
በ2016 በጀት ዓመት ደግሞ ከ140 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል ያሉት አቶ አደም፤ ይህንን ገቢ እውን ለማድረግ አመራሩ በትኩረት የሚሰራ ሲሆን አሰራሩም በቴክኖሎጂ የሚደገፍ ይሆናል ብለዋል።
በ2015 በጀት ዓመት የነበሩ ተግዳሮቶች ማለትም ሀሰተኛ ደረሰኝ የሚጠቀሙ እና ከዋጋ በታች ደረሰኝ በሚቆርጡ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ ትኩረት ይደረጋል። ህብረተሰቡም ግብር መክፈል ለሀገር ክብር መሆኑን ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል።
በመርሃ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፤ በከተማዋ የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ቢመጣም በሚገባው እና መሰብሰብ ባለበት ልክ እየተሰበሰበ አይደለም።
መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት እና የከተማዋን ገቢ በማሳደግ ውብ እና ሁለተናዊ እድገት ለማምጣት መተባበር ያስፈልጋል ብለዋል።
ከንቲባዋ በመርሃ ግብሩ በ2015 በጀት አመት ጠንካራ አፈፃፀም ለነበራቸው ሥራ አስፈፃሚዎች እውቅናና ሽልማት የሰጡ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ለ2016 በጀት አመት ጠንካራ ሥራ እንዲሰሩ የአደራ ሰርተፍኬት ሰጥተዋል።
ሐምሌ 4 ቀን 2015ዓ.ም
በሳሙኤል ወንደሰን
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
- ቢሮው በ2015 በጀት ዓመት ከ107 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰብስቧል
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ የ2015 በጀት ዓመት የገቢ ዕቅድ ማጠቃለያ እና የ2016 በጀት ዓመት የግብር ማሳወቂያ የንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል።
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ አቶ አደም ኑሪ በመርሃ ግብሩ እንደተናገሩት፤ ቢሮው በ2015 በጀት ዓመት ከገቢዎች ቢሮ ፣ ከማዕከል ገቢ ሰብሳቢ ሴክተሮች፣ ከክፍለ ከተሞች እና ከሌሎች ገቢዎች ጨምሮ በጥቅሉ ከ107 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል።
የተሰበሰበው ገቢ ከ2014 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ53 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
ይህም በገንዘብ 37 ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር መሆኑን የገለፁት ኃላፊው፤ የተሰበሰበው ብር ለከተማዋ ዘላቂ የልማት ዘርፎች ማለትም ለትምህርት ቤት፣ ለተማሪዎች ምገባ እና ለትውልድ መተላለፍ ለሚችሉ ኘሮጀክቶች የሚውል ነው። ስለዚህ ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በሚቀጥለው በጀት ዓመት አጠናክረው ሊከፍሉ ይገባል ብለዋል።
በ2016 በጀት ዓመት ደግሞ ከ140 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዷል ያሉት አቶ አደም፤ ይህንን ገቢ እውን ለማድረግ አመራሩ በትኩረት የሚሰራ ሲሆን አሰራሩም በቴክኖሎጂ የሚደገፍ ይሆናል ብለዋል።
በ2015 በጀት ዓመት የነበሩ ተግዳሮቶች ማለትም ሀሰተኛ ደረሰኝ የሚጠቀሙ እና ከዋጋ በታች ደረሰኝ በሚቆርጡ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ ትኩረት ይደረጋል። ህብረተሰቡም ግብር መክፈል ለሀገር ክብር መሆኑን ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል።
በመርሃ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት፤ በከተማዋ የግብር አሰባሰብ ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ቢመጣም በሚገባው እና መሰብሰብ ባለበት ልክ እየተሰበሰበ አይደለም።
መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት እና የከተማዋን ገቢ በማሳደግ ውብ እና ሁለተናዊ እድገት ለማምጣት መተባበር ያስፈልጋል ብለዋል።
ከንቲባዋ በመርሃ ግብሩ በ2015 በጀት አመት ጠንካራ አፈፃፀም ለነበራቸው ሥራ አስፈፃሚዎች እውቅናና ሽልማት የሰጡ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ለ2016 በጀት አመት ጠንካራ ሥራ እንዲሰሩ የአደራ ሰርተፍኬት ሰጥተዋል።
ሐምሌ 4 ቀን 2015ዓ.ም
በሳሙኤል ወንደሰን
በክልሉ በአንድ ጀምበር 20 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት ተጠናቀቀ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ የፊታችን ሰኞ በአንድ ጀምበር 20 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለፁ።
በክልሉ የሚከናወነው የችግኝ ተከላ እንደሀገር ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም 500 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል የተያዘው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ አካል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ባለፉት አራት ዓመታት 646 ሚሊየን 499 ሺህ 415 ችግኞች መተከላቸው ተገልጿል።
የክልሉ ሕዝብ፣የሐይማኖት ተቋማት፣ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሰኞ ለሚከናወነው ታሪካዊ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ስኬት ዐሻራቸውን እንዲያሳርፉ የክልሉ መንግሥት ጥሪ ማቅረቡን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ሐሳብ የፊታችን ሰኞ በአንድ ጀምበር 20 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለፁ።
በክልሉ የሚከናወነው የችግኝ ተከላ እንደሀገር ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም 500 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል የተያዘው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ አካል መሆኑ ተገልጿል፡፡
ባለፉት አራት ዓመታት 646 ሚሊየን 499 ሺህ 415 ችግኞች መተከላቸው ተገልጿል።
የክልሉ ሕዝብ፣የሐይማኖት ተቋማት፣ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሰኞ ለሚከናወነው ታሪካዊ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ስኬት ዐሻራቸውን እንዲያሳርፉ የክልሉ መንግሥት ጥሪ ማቅረቡን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ ለሁለተኛው ምዕራፍ አረንጓዴ አሻራ ታሪካዊ አስተዋጽኦ ያበረክታል
👉 ለ500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር ለሚደረገው ተከላ 9ሺህ 500 ቦታዎች ተዘጋጅተዋል፣
👉 ለዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ እስካሁን 6.4 ቢሊዮን የችግኝ መትከያ ጉድጓድ ተቆፍሯል፣
********
(ኢ ፕ ድ)
በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል የሚደረገው መርሐግብር ምን ያህል ችግኝ እንደተተከለ፣ በተከላው የተሳተፈውን የሰው ኃይልና የተሸፈነውን መሬት የሚያሳይ የካርታ ዝግጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መዘጋጀቱን ፕሮፌሰር ኢያሱ ተናግረዋል፡፡
የመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት በማጠናቀቅ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ የተሸጋገረው የአረንጓዴ አሻራ ልማት የምዕራፉን የመጀመሪያ አመት ስራ በስኬት ለማጠናቀቅ ሰፊ ማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡
በዘንድሮው አመት 6.5 ቢሊዮን ችግኝ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ለመትከል ሰፊ ስራ እየተሰራ ሲሆን ይህን ለማሳካት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ ‹500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር› ለመትከል የሚደረገው መርሐግብር ነው፡፡
በዚህ አመት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ሰፊ የችግኝ ዝግጅት ከመደረጉ ባለፈ እስካሁን 6.4 ቢሊዮን የችግኝ መትከያ ጉድጓድ መቆፈሩን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢያሱ ኤሊያስ/ፕሮፌሰር/ 500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር ለሚደረገው ተከላ 9500 ቦታዎች እንደተዘጋጁና ይህም 361415 ሄክታር መሬት እንደሚሸፍን ተናግረዋል፡፡
በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ለጥራት፣ ለፍራፍሬና ለአገር በቀል ዝርያዎች ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን 60 በመቶ የጥምር ደን እርሻ፣ 35 በመቶ የፍራፍሬ እንዲሁም 5 በመቶ ለከተማ ውበት የሚሆኑ ዘርፈ ብዙ ችግኞች ናቸው፡፡
በመሆኑም 500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር እነዚህን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የሚተገበር ይሆናል፡፡ በመሆኑም ሁሉም የመስራት አቅም ያለው የማህበረሰብ ክፍል በዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ አሻራውን ማስቀመጥ እንዳለበት ፕሮፌሰር ኢያሱ መግለፃቸውን የግብርና ሚኒስትቴር አስታውቋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እየሰጠ ሲሆን በአካባቢ ጥበቃ፣ ኢኮኖሚያዊ ተቀሜታ፣ ስራ እድል ፈጠራና ለአገር ገፅታ ግንባታ የጎላ ድርሻ አበርክቷል፡፡
👉 ለ500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር ለሚደረገው ተከላ 9ሺህ 500 ቦታዎች ተዘጋጅተዋል፣
👉 ለዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ እስካሁን 6.4 ቢሊዮን የችግኝ መትከያ ጉድጓድ ተቆፍሯል፣
********
(ኢ ፕ ድ)
በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል የሚደረገው መርሐግብር ምን ያህል ችግኝ እንደተተከለ፣ በተከላው የተሳተፈውን የሰው ኃይልና የተሸፈነውን መሬት የሚያሳይ የካርታ ዝግጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መዘጋጀቱን ፕሮፌሰር ኢያሱ ተናግረዋል፡፡
የመጀመሪያውን ምዕራፍ በስኬት በማጠናቀቅ ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ የተሸጋገረው የአረንጓዴ አሻራ ልማት የምዕራፉን የመጀመሪያ አመት ስራ በስኬት ለማጠናቀቅ ሰፊ ማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡
በዘንድሮው አመት 6.5 ቢሊዮን ችግኝ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ለመትከል ሰፊ ስራ እየተሰራ ሲሆን ይህን ለማሳካት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ ‹500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር› ለመትከል የሚደረገው መርሐግብር ነው፡፡
በዚህ አመት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ሰፊ የችግኝ ዝግጅት ከመደረጉ ባለፈ እስካሁን 6.4 ቢሊዮን የችግኝ መትከያ ጉድጓድ መቆፈሩን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢያሱ ኤሊያስ/ፕሮፌሰር/ 500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር ለሚደረገው ተከላ 9500 ቦታዎች እንደተዘጋጁና ይህም 361415 ሄክታር መሬት እንደሚሸፍን ተናግረዋል፡፡
በሁለተኛው ምዕራፍ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ለጥራት፣ ለፍራፍሬና ለአገር በቀል ዝርያዎች ልዩ ትኩረት የሚሰጥ ሲሆን 60 በመቶ የጥምር ደን እርሻ፣ 35 በመቶ የፍራፍሬ እንዲሁም 5 በመቶ ለከተማ ውበት የሚሆኑ ዘርፈ ብዙ ችግኞች ናቸው፡፡
በመሆኑም 500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር እነዚህን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የሚተገበር ይሆናል፡፡ በመሆኑም ሁሉም የመስራት አቅም ያለው የማህበረሰብ ክፍል በዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ አሻራውን ማስቀመጥ እንዳለበት ፕሮፌሰር ኢያሱ መግለፃቸውን የግብርና ሚኒስትቴር አስታውቋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እየሰጠ ሲሆን በአካባቢ ጥበቃ፣ ኢኮኖሚያዊ ተቀሜታ፣ ስራ እድል ፈጠራና ለአገር ገፅታ ግንባታ የጎላ ድርሻ አበርክቷል፡፡
የለሚ ናሽል ሲሚንቶ ፋብሪካ ግንባታ 65 ከመቶ ደርሷል
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ዶላር እየተገነባ የሚገኘው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ግንባታ 65 ከመቶ መድረሱ ተገለፀ፡፡
የአማራ ክልል የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የአዲስ አበባ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ አዲስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ የፋብሪካው ግንባታ እየተፋጠነ ነው። አስፈላጊ የሚባሉ ማሽኖችም ከቦታው እየደረሱ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት 3000 ዜጎች የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን፤ አንድ ሺህ 500 ቻይናውያን በፋብሪካው ግንባታ ላይ እየተሳተፉና የዕውቀት ሽግግር እየተፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል።
የፋብሪካው ግንባታ በሚቀጥለው ዓመት ተጠናቆ ምርት እንደሚጀምርም አቶ ያየህ ገልጸዋል።
የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማኅበር የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ በኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ እና በቻይናው ዌስት ቻይና የሲሚንቶ አምራች ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ሽርክና የተመሰረተ ነው፡፡
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
በክፍለዮሐንስ አንበርብር
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሁለት ነጥብ ሁለት ቢሊዮን ዶላር እየተገነባ የሚገኘው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማህበር የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ግንባታ 65 ከመቶ መድረሱ ተገለፀ፡፡
የአማራ ክልል የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የአዲስ አበባ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያየህ አዲስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት፤ የፋብሪካው ግንባታ እየተፋጠነ ነው። አስፈላጊ የሚባሉ ማሽኖችም ከቦታው እየደረሱ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት 3000 ዜጎች የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን፤ አንድ ሺህ 500 ቻይናውያን በፋብሪካው ግንባታ ላይ እየተሳተፉና የዕውቀት ሽግግር እየተፈጠረ መሆኑንም አብራርተዋል።
የፋብሪካው ግንባታ በሚቀጥለው ዓመት ተጠናቆ ምርት እንደሚጀምርም አቶ ያየህ ገልጸዋል።
የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ አክሲዮን ማኅበር የኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ በኢስት አፍሪካን ሆልዲንግ እና በቻይናው ዌስት ቻይና የሲሚንቶ አምራች ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ሽርክና የተመሰረተ ነው፡፡
ሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም
በክፍለዮሐንስ አንበርብር
"የኢትዮጵያና የአሜሪካ የሁለትዮሽና የባለ ብዙ ወገን ትብብር በተፋጠነና በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ ሊሆን ይገባል"
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
******************
(ኢ ፕ ድ)
እየተሻሻለ የመጣው የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ የሁለትዮሽና የባለ ብዙ ወገን ትብብር በተፋጠነና በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ መሆን እንደሚገባው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገረዋል::
ውይይታቸው በሁለትዮሽና በወቅታዊው የአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል።
ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ኢጋድ በአዲስ አበባ ያደረገውን ውይይት ኢትዮጵያ በማስተናገዷ አመስግነው የሱዳን ኃይሎች የተኩስ አቁም በማድረግ ለችግሩ ፖለቲካዊ መፍትሔ እንዲፈልጉ እና ሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በበኩላቸው እየተሻሻለ የመጣውን የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ የሁለትዮሽና የባለ ብዙ ወገን ትብብር በተፋጠነና በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
የሱዳን ሰላም ራሳቸው ሱዳናውያን ባለቤት በሆኑበት በአፍሪካ ሕብረት እና ኢጋድ ማዕቀፍ እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ጥረቶች የተደገፈ ሊሆን እንደሚገባው ማመላከታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ ም
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
******************
(ኢ ፕ ድ)
እየተሻሻለ የመጣው የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ የሁለትዮሽና የባለ ብዙ ወገን ትብብር በተፋጠነና በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ መሆን እንደሚገባው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገረዋል::
ውይይታቸው በሁለትዮሽና በወቅታዊው የአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል።
ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ኢጋድ በአዲስ አበባ ያደረገውን ውይይት ኢትዮጵያ በማስተናገዷ አመስግነው የሱዳን ኃይሎች የተኩስ አቁም በማድረግ ለችግሩ ፖለቲካዊ መፍትሔ እንዲፈልጉ እና ሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በበኩላቸው እየተሻሻለ የመጣውን የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ የሁለትዮሽና የባለ ብዙ ወገን ትብብር በተፋጠነና በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
የሱዳን ሰላም ራሳቸው ሱዳናውያን ባለቤት በሆኑበት በአፍሪካ ሕብረት እና ኢጋድ ማዕቀፍ እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ ጥረቶች የተደገፈ ሊሆን እንደሚገባው ማመላከታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ ም
ሀረር ከተማ የአለም የቅርስ ከተሞች አባል ሆና ተመዘገበች
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ሀረር ከተማ ሀረር ከሰሃራ በታች ካሉ ከተሞች የመጀመሪያዋ የአለም ቅርስ ከተሞች ድርጅት (Organization of World Heritage Cities) አባል ከተማ ሆና ተመዝግባለች።
የሀረሪ ክልል ርዕሰ መተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪም ካናዳ ሀገር ኩቢክ ከተማ በተካሄደው የፊርማ ስነስርዓት ሀረር ከተማ የአለም የቅርስ ከተሞች አባል ሆና የተመዘገበችበት ፊርማ አኑረዋል።
ሀረር ከተማ 115 ሀገራትን በአባልነት በያዘው የቅርስ ከተሞች ድርጅት ከፈረንጆች አቆጣጣር ከሰኔ ወር 2023 ጀምሮ ነው የተመዘገበችው።
ሀረር ከተማ የቅርስ ከተሞች መካከል አንዷ ሆና መመዝገቧ ከተማዋ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ለማልማት እና ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም የቅርስ ከተሞች በጋራ ጉዳዮቻቸው ተመካክረው አቅጣጫ በማስቀመጥ ተግዳሮቶችን ለመሻገርና እድሎችን ለማስፋት እንደሚጠቅም ይታመናል።
ሀረር ከተማ የጁገል አለም አቀፍ ቅርስንን ጨምሮ በዩኔስኮ የተመዘገቡ አለም አቀፍ ቅርሶች መገኛ ከተማ ከመሆኗ በተጨማሪ ከተማዋ ዜጎች በሰላም፣ በመቻቻልና በአብሮነት የሚኖሩባት ከተማ በሚል በተባበሩት መንግስት የሳይንስ፣ የትምህርትና የባህል ተቋም ዩኔስኮ እውቅና እንደተሰጣት ይታወሳል።
በፊርማ ስነ ስርአቱ ላይም የሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ፣ የክልሉ ምክር ቤት ም/አፈ ጉባኤ አቶ አሪፍ መሀመድን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ግንባታ ማእከል ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ካሊድ አልዋን መገኘታቸውን ከክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ሀረር ከተማ ሀረር ከሰሃራ በታች ካሉ ከተሞች የመጀመሪያዋ የአለም ቅርስ ከተሞች ድርጅት (Organization of World Heritage Cities) አባል ከተማ ሆና ተመዝግባለች።
የሀረሪ ክልል ርዕሰ መተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪም ካናዳ ሀገር ኩቢክ ከተማ በተካሄደው የፊርማ ስነስርዓት ሀረር ከተማ የአለም የቅርስ ከተሞች አባል ሆና የተመዘገበችበት ፊርማ አኑረዋል።
ሀረር ከተማ 115 ሀገራትን በአባልነት በያዘው የቅርስ ከተሞች ድርጅት ከፈረንጆች አቆጣጣር ከሰኔ ወር 2023 ጀምሮ ነው የተመዘገበችው።
ሀረር ከተማ የቅርስ ከተሞች መካከል አንዷ ሆና መመዝገቧ ከተማዋ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ለማልማት እና ለቱሪዝም ዘርፉ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም የቅርስ ከተሞች በጋራ ጉዳዮቻቸው ተመካክረው አቅጣጫ በማስቀመጥ ተግዳሮቶችን ለመሻገርና እድሎችን ለማስፋት እንደሚጠቅም ይታመናል።
ሀረር ከተማ የጁገል አለም አቀፍ ቅርስንን ጨምሮ በዩኔስኮ የተመዘገቡ አለም አቀፍ ቅርሶች መገኛ ከተማ ከመሆኗ በተጨማሪ ከተማዋ ዜጎች በሰላም፣ በመቻቻልና በአብሮነት የሚኖሩባት ከተማ በሚል በተባበሩት መንግስት የሳይንስ፣ የትምህርትና የባህል ተቋም ዩኔስኮ እውቅና እንደተሰጣት ይታወሳል።
በፊርማ ስነ ስርአቱ ላይም የሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱጀባር መሀመድ ፣ የክልሉ ምክር ቤት ም/አፈ ጉባኤ አቶ አሪፍ መሀመድን ጨምሮ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ግንባታ ማእከል ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ካሊድ አልዋን መገኘታቸውን ከክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም