በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ የሚቀይር ኩባንያ በኢንቨስትመንት ለመስራት ያለውን ፍላጎት ገለፀ
************************
(ኢ ፕ ድ)
በነዳጅ የሚሰሩ ባለሶስት እግር እና ባለ አራት እግር ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሲስተም የሚቀይር ኩባንያ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለመስራት ያለውን ፍላጎት ገልጿል።
የኢንቨስትመንቱ ባለቤት ኢንጂነር እሸቱ መኮንን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ሰለሞን ጋር መክረዋል።
የኢንቨስትመንት ሀሳቡ ባለቤትም ስለኢንቨስትመንት እቅዱ ማብራሪያ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
ኩባንያው በኡንዱስትሪ ፓርኮች ግዙፍ የመገጣጠሚያ ወርክሾፕ በመክፈት በአንድ አመት አንድ ሺህ ባለሶስት እግር እንዲሁም 200 ባለአራት እግር ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሲስተም ለመቀየር የመጀመሪያ እቅድ እንዳለው ተገልጿል።
በውይይቱም ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ሽፈራው ኢንቨስትመንቱ እንደ ሀገር ያለው ጠቀሜታ ጉልህ በመሆኑ ኮርፖሬሽኑ ለኢንቨስትመንቱ መሳካት አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ ም
************************
(ኢ ፕ ድ)
በነዳጅ የሚሰሩ ባለሶስት እግር እና ባለ አራት እግር ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሲስተም የሚቀይር ኩባንያ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለመስራት ያለውን ፍላጎት ገልጿል።
የኢንቨስትመንቱ ባለቤት ኢንጂነር እሸቱ መኮንን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ሰለሞን ጋር መክረዋል።
የኢንቨስትመንት ሀሳቡ ባለቤትም ስለኢንቨስትመንት እቅዱ ማብራሪያ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
ኩባንያው በኡንዱስትሪ ፓርኮች ግዙፍ የመገጣጠሚያ ወርክሾፕ በመክፈት በአንድ አመት አንድ ሺህ ባለሶስት እግር እንዲሁም 200 ባለአራት እግር ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ሲስተም ለመቀየር የመጀመሪያ እቅድ እንዳለው ተገልጿል።
በውይይቱም ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ሽፈራው ኢንቨስትመንቱ እንደ ሀገር ያለው ጠቀሜታ ጉልህ በመሆኑ ኮርፖሬሽኑ ለኢንቨስትመንቱ መሳካት አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ ም
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከካሜሩን አቻቸው ጋር ውይይት አካሄዱ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ነገ መካሄድ በሚጀምረው 43ኛው የአፍሪካ ኀብረት የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ በፊት ከካሜሮን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሌጄዩን ምቤላ ጋር በሁለትዮሽ፤ በባለብዙ ወገንና በሁለቱ አገሮች የጋራ ተጠቃሚነት ዙሪያ ውይይት አካሄደዋል።
የፖለቲካ ምክክር፤ በባለብዙ ወገን መድረክና በሌሎች ጉዳዩች በጋራ አብሮ መስራት ስለሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ውይይት በቅርቡ እንደሚካሄድ ተገልፆል ።
በሁለትዮሽ ውይይቱ ወቅት አቶ ደመቀ መኮንን ከአፍሪካ አገራት ጋር ለሚኖረን ግንኘነት የበለጠ ትኩረትና ዋጋ እንሰጣለን ብለዋል። በተጨማሪ ስለፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ገለፃ አድርገዋል።
በአገሪቱ የሰሜኑ ክፍል ተፈጥሮ የነበረውን ግጭት ለመፍታት መንግስት በመርህ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ጋና በአለምአቀፍ መድረክ ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ነገ መካሄድ በሚጀምረው 43ኛው የአፍሪካ ኀብረት የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት ስብሰባ በፊት ከካሜሮን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሌጄዩን ምቤላ ጋር በሁለትዮሽ፤ በባለብዙ ወገንና በሁለቱ አገሮች የጋራ ተጠቃሚነት ዙሪያ ውይይት አካሄደዋል።
የፖለቲካ ምክክር፤ በባለብዙ ወገን መድረክና በሌሎች ጉዳዩች በጋራ አብሮ መስራት ስለሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ውይይት በቅርቡ እንደሚካሄድ ተገልፆል ።
በሁለትዮሽ ውይይቱ ወቅት አቶ ደመቀ መኮንን ከአፍሪካ አገራት ጋር ለሚኖረን ግንኘነት የበለጠ ትኩረትና ዋጋ እንሰጣለን ብለዋል። በተጨማሪ ስለፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ገለፃ አድርገዋል።
በአገሪቱ የሰሜኑ ክፍል ተፈጥሮ የነበረውን ግጭት ለመፍታት መንግስት በመርህ ላይ የተመሰረተ ውሳኔዎችን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ጋና በአለምአቀፍ መድረክ ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ.ም
በግብጽ ካይሮ ከፕሬዚዳንት አብዱልፈታሕ ኤልሲሲ ጋር በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ትብብር በሰፈነበት መንፈስ ውይይቶች አካሂደናል"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ከውጭ ጎብኚዎች ከ39 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ከተማዋ ኢኮኖሚ ፈሰስ ሆኗል
********************
(ኢ ፕ ድ )
በ2015 በጀት ዓመት በቱሪዝሙ ዘርፍ ከውጭ ጎብኚዎች የተገኘ ከ39 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ከተማዋ ኢኮኖሚ ፈሰስ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ባሕል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የቱሪዝም መዳረሻ ልማትና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ማስፋፋት ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ዓይናቸው ....
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0kpwW3XdU6ZDer8UVYtdU2kuUhMzDAccr9fsEkx5k7F4fDnqhPjEiSsQKd8BB8tyAl&id=100069403920568&mibextid=Nif5oz
********************
(ኢ ፕ ድ )
በ2015 በጀት ዓመት በቱሪዝሙ ዘርፍ ከውጭ ጎብኚዎች የተገኘ ከ39 ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወደ ከተማዋ ኢኮኖሚ ፈሰስ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ባሕል ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የቱሪዝም መዳረሻ ልማትና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ማስፋፋት ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ዓይናቸው ....
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0kpwW3XdU6ZDer8UVYtdU2kuUhMzDAccr9fsEkx5k7F4fDnqhPjEiSsQKd8BB8tyAl&id=100069403920568&mibextid=Nif5oz
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️
ዛሬ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ የተገነቡትን ከ 70 በላይ የመሸጫ ሱቆች የተካተቱበት የአቃቂ ሰብል ምርት ገበያ ማዕከልን እና በ140,000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሰፈረውን የእንስሳት ልማት ልህቀት ማዕከልን መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።
ህዝባችንን በብርቱ እየፈተነ ያለውን የኑሮ ጫና ለማቃለል ከጀመርናቸው ስራዎች መካከል አንዱ የሆነው የሰብል ምርት ገበያ ማዕከል፣ ህብረተሰቡ በቀጥታ ከአምራቹ እንዲሸምት የሚያስችለው እና ገበያውን በማረጋጋት ትልቅ አስተዋፅዖ ያለው ነው።
የምርት ገበያው ሱቆችን ጨምሮ መጋዘን፣ ወፍጮ ቤት እንዲሁም ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰጡ ማዕከላት የተካተቱበት ሲሆን ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አምራቾች እና አርሶአደሮች የስራ እድል ይፈጥራል። የእንስሳት ልህቀት ማዕከሉ ደግሞ የዶሮና የወተት ላም እርባታ፣ የከብት ማደለብ፣ የመኖ ማቀነባበሪያ እንዲሁም የምርት ማሳያና መሸጫ ቦታዎችን ያካተተ ነው።
ይህ የልህቀት ማዕከል በዘርፉ ለሚሰማሩ 485 የልማት ተነሺ አርሶ አደሮችን የእዉቀት፣ የክህሎት፣ የምርምር፣ የግብዓት፣ እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ምንጭ ሆኖ ያገለግላል። የነዋሪዎቻችንን የኑሮ ጫናዎች ለማቃለል እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በታማኝነትና በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን።
ዛሬ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ የተገነቡትን ከ 70 በላይ የመሸጫ ሱቆች የተካተቱበት የአቃቂ ሰብል ምርት ገበያ ማዕከልን እና በ140,000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሰፈረውን የእንስሳት ልማት ልህቀት ማዕከልን መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።
ህዝባችንን በብርቱ እየፈተነ ያለውን የኑሮ ጫና ለማቃለል ከጀመርናቸው ስራዎች መካከል አንዱ የሆነው የሰብል ምርት ገበያ ማዕከል፣ ህብረተሰቡ በቀጥታ ከአምራቹ እንዲሸምት የሚያስችለው እና ገበያውን በማረጋጋት ትልቅ አስተዋፅዖ ያለው ነው።
የምርት ገበያው ሱቆችን ጨምሮ መጋዘን፣ ወፍጮ ቤት እንዲሁም ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰጡ ማዕከላት የተካተቱበት ሲሆን ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አምራቾች እና አርሶአደሮች የስራ እድል ይፈጥራል። የእንስሳት ልህቀት ማዕከሉ ደግሞ የዶሮና የወተት ላም እርባታ፣ የከብት ማደለብ፣ የመኖ ማቀነባበሪያ እንዲሁም የምርት ማሳያና መሸጫ ቦታዎችን ያካተተ ነው።
ይህ የልህቀት ማዕከል በዘርፉ ለሚሰማሩ 485 የልማት ተነሺ አርሶ አደሮችን የእዉቀት፣ የክህሎት፣ የምርምር፣ የግብዓት፣ እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ምንጭ ሆኖ ያገለግላል። የነዋሪዎቻችንን የኑሮ ጫናዎች ለማቃለል እና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በታማኝነትና በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን።