የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጉብኝት እያደረጉ ነው
********************
(ኢ ፕ ድ)
👉 ፕሬዝዳንቱ በፓርኩ ውስጥ ችግኝ ተክለዋል
የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ከጠቅላይ ሚኒስት ዐቢይ አሕመድ ጋር በመሆኑን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክን እየጎበኙ ነው።
ፕሬዝዳንቱ በፓርኩ ውስጥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር በመሆንም ችግኝ ተክለዋል።
የባንኩ ፕሬዚዳንት ትናንት ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም ፕሬዝዳንቱን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም ፕሬዚዳንቱን በዛሬው እለት በዓለም ባንክ ድጋፍ የተገነባውን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴና እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን እያስጎበኟቸው ነው።
የዓለም ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የትብብር አድማስ በማስፋት ለኢኮኖሚ እድገታችን በኮንሴሽናል ፋይናንስ፣ በአለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በኩል ጠንካራ የኢንቨስትመንት ፋይናንስ አቅርቦት እና የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችንን የሚደግፍ የዘለቀ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ጠቅላይ ሚኒስትረ ዐቢይ አሕመድ በትናንትናው እለት ማስታወቃቸው ይታወሳል።
በሳሙኤል ወንደሰን
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓም
(ፎቶ ፋይል)
********************
(ኢ ፕ ድ)
👉 ፕሬዝዳንቱ በፓርኩ ውስጥ ችግኝ ተክለዋል
የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ከጠቅላይ ሚኒስት ዐቢይ አሕመድ ጋር በመሆኑን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክን እየጎበኙ ነው።
ፕሬዝዳንቱ በፓርኩ ውስጥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር በመሆንም ችግኝ ተክለዋል።
የባንኩ ፕሬዚዳንት ትናንት ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድም ፕሬዝዳንቱን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይም ፕሬዚዳንቱን በዛሬው እለት በዓለም ባንክ ድጋፍ የተገነባውን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴና እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን እያስጎበኟቸው ነው።
የዓለም ባንክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን የትብብር አድማስ በማስፋት ለኢኮኖሚ እድገታችን በኮንሴሽናል ፋይናንስ፣ በአለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በኩል ጠንካራ የኢንቨስትመንት ፋይናንስ አቅርቦት እና የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳችንን የሚደግፍ የዘለቀ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ጠቅላይ ሚኒስትረ ዐቢይ አሕመድ በትናንትናው እለት ማስታወቃቸው ይታወሳል።
በሳሙኤል ወንደሰን
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓም
(ፎቶ ፋይል)
የከተማ አቀፍ የስድስኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
👉 104 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የከተማ አቀፍ የስድስኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤትን በዛሬ ዕለት ይፋ አድርጓል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ በከተማ አስተዳደሩ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ የስድስተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ28 አመት በዋላ ዘንድሮ ለመጀመሪያጊዜ ተሰቷል፡፡
እንደ ዶክተር ዘላለም ገለጻ፡-በከተማ አስተዳደሩ 73 ሺ 667 የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል፡፡ ፈተናው ከወሰዱት ተማሪዎች መካከል 3 ተማሪዎች 99 ከመቶ አምጥተዋል፡፡ 477 ተማሪዎች 95ና ከዛ በላይ ማምጣታቸውን ገልጸው 2 ሺህ 787 ተማሪዎች 90ና ከዛ በላይ ያመጡ ሲሆን 59 ሺህ 105 ተማሪዎች 50ና ከዛ በላይ ማምጣታቸውን ገልጸዋል፡፡
የአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች 80 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆኑት 50ና ከዛ በላይ ማምጣታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በመደበኛ ከተፈተኑት 67 ሺህ 939 ተማሪዎች 56 ሺህ 842 50ና ከዛ በላይ አምጥተዋል፡፡በዚህም 83 ነጥብ 6 በመቶ የሚሆኑት ማለፋቸውን ተናግረዋል፡፡
የማለፊያ ነጥብን በተመለከተ ለመደበኛ ተማሪዎች 50ና ከዛ በላይ ያመጡ ተማሪዎች የሚያልፉ ሲሆን ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች 45ና ከዛ በላይ ያመጡ ወደ ቀጣዩ ክፍል የሚሸጋገሩ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
104 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎችን ማሳለፋቸውን ገልጸው ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ጀምሮ መመልከት የሚችሉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
👉 104 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን አሳልፈዋል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የከተማ አቀፍ የስድስኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤትን በዛሬ ዕለት ይፋ አድርጓል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፣ በከተማ አስተዳደሩ አዲሱን ስርዓተ ትምህርት መሰረት አድርጎ የስድስተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ28 አመት በዋላ ዘንድሮ ለመጀመሪያጊዜ ተሰቷል፡፡
እንደ ዶክተር ዘላለም ገለጻ፡-በከተማ አስተዳደሩ 73 ሺ 667 የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል፡፡ ፈተናው ከወሰዱት ተማሪዎች መካከል 3 ተማሪዎች 99 ከመቶ አምጥተዋል፡፡ 477 ተማሪዎች 95ና ከዛ በላይ ማምጣታቸውን ገልጸው 2 ሺህ 787 ተማሪዎች 90ና ከዛ በላይ ያመጡ ሲሆን 59 ሺህ 105 ተማሪዎች 50ና ከዛ በላይ ማምጣታቸውን ገልጸዋል፡፡
የአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች 80 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆኑት 50ና ከዛ በላይ ማምጣታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በመደበኛ ከተፈተኑት 67 ሺህ 939 ተማሪዎች 56 ሺህ 842 50ና ከዛ በላይ አምጥተዋል፡፡በዚህም 83 ነጥብ 6 በመቶ የሚሆኑት ማለፋቸውን ተናግረዋል፡፡
የማለፊያ ነጥብን በተመለከተ ለመደበኛ ተማሪዎች 50ና ከዛ በላይ ያመጡ ተማሪዎች የሚያልፉ ሲሆን ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች 45ና ከዛ በላይ ያመጡ ወደ ቀጣዩ ክፍል የሚሸጋገሩ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
104 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎችን ማሳለፋቸውን ገልጸው ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ጀምሮ መመልከት የሚችሉ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‼️
ኢትዮጵያ ለብዙ ሺህዎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድል ያስገኙ 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ገንብታ ወደ ስራ አስገብታለች። የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮችንም ገንብተን በስራ ላይ እንገኛለን።
ከአለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር በመሆን ዛሬ ጠዋት በአንደኛው የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በምርት ስራ ላይ ካሉ ኢንዱስትሪዎቻችን ሁለቱን አብረን ጎብኝተናል። ኢትዮጵያ ትልቅ አቅም ያላት ሀገር ብቻ ሳትሆን በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች መዋእለ ነዋይ ለማፍሰስ ለሚሹ ሁሉ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረች ነው።
ኢትዮጵያ ለብዙ ሺህዎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድል ያስገኙ 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ገንብታ ወደ ስራ አስገብታለች። የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮችንም ገንብተን በስራ ላይ እንገኛለን።
ከአለም ባንክ ፕሬዝዳንት አጃይ ባንጋ ጋር በመሆን ዛሬ ጠዋት በአንደኛው የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በምርት ስራ ላይ ካሉ ኢንዱስትሪዎቻችን ሁለቱን አብረን ጎብኝተናል። ኢትዮጵያ ትልቅ አቅም ያላት ሀገር ብቻ ሳትሆን በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች መዋእለ ነዋይ ለማፍሰስ ለሚሹ ሁሉ ምቹ ሁኔታን እየፈጠረች ነው።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና አጀማመርን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተመለከቱ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በመገኘት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ የፈተና አሠጣጥ ሂደቱን ተመልክተዋል።
የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሠር ብርሃኑ ነጋ ከሚንስቴር ደኤታው ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ጋር በመሆን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ሲቪል ሠርቪስ ዩኒቨርሲቲና የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ኢንስቲቲዩት ምልከታ አድርገዋል።
በምልከታቸውም ሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሣይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና በጥሩ ሁኔታ እየተሠጠ መሆኑን ለመገንዘብ መቻሉን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ዛሬ የተጀመረው የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና እስከ ሀምሌ 28/2015 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ቀናት ይሰጣል። መጀመሪያው ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ሚስጥራዊነቱና ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ መጠናቀቁ ይታወሳል።
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
********************
(ኢ ፕ ድ)
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በመገኘት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ የፈተና አሠጣጥ ሂደቱን ተመልክተዋል።
የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሠር ብርሃኑ ነጋ ከሚንስቴር ደኤታው ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ጋር በመሆን አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ሲቪል ሠርቪስ ዩኒቨርሲቲና የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ኢንስቲቲዩት ምልከታ አድርገዋል።
በምልከታቸውም ሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሣይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና በጥሩ ሁኔታ እየተሠጠ መሆኑን ለመገንዘብ መቻሉን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ዛሬ የተጀመረው የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና እስከ ሀምሌ 28/2015 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ቀናት ይሰጣል። መጀመሪያው ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ሚስጥራዊነቱና ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ መጠናቀቁ ይታወሳል።
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️
እንደ ሀገር ከ28 ዓመታት በኋላ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የተሰጠው የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት 73 ሺህ 667 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም 80.2% ያህሉ 50 ፐርሰንትና ከዚያ በላይ በማምጣት ወደ ቀጣይ ክፍል ሲያልፉ ፤ 67 ሺህ 939 ከሚሆኑ የቀን ተማሪዎች መካከል 56 ሺህ 842 የሚሆኑት 83.6% የማለፊያ ውጤቱን በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የትምህርት እርከን ተዘዋውረዋል።
የትምህርት ግብዓት ለማሟላት እያደረግን ያለው ጥረት እና መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ተማሪዎችን ብቁ የማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት የሰሩት ስራ ተማሪዎቹ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በማስቻሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡
ሃገሩን የሚወድ ጠንካራ ትውልድ ለመገንባት እና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የጀመርናቸውን ስራዎች አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል::
እንደ ሀገር ከ28 ዓመታት በኋላ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የተሰጠው የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት 73 ሺህ 667 ተማሪዎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ከነዚህም 80.2% ያህሉ 50 ፐርሰንትና ከዚያ በላይ በማምጣት ወደ ቀጣይ ክፍል ሲያልፉ ፤ 67 ሺህ 939 ከሚሆኑ የቀን ተማሪዎች መካከል 56 ሺህ 842 የሚሆኑት 83.6% የማለፊያ ውጤቱን በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የትምህርት እርከን ተዘዋውረዋል።
የትምህርት ግብዓት ለማሟላት እያደረግን ያለው ጥረት እና መምህራን እና የትምህርት አመራሮች ተማሪዎችን ብቁ የማድረግ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት የሰሩት ስራ ተማሪዎቹ የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በማስቻሉ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ፡፡
ሃገሩን የሚወድ ጠንካራ ትውልድ ለመገንባት እና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የጀመርናቸውን ስራዎች አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል::
“የኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባት ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ፈጥሯል”- የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ
************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባታቸው ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር ማስቻሉን ተመልክቻለሁ ሲሉ የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱን በዛሬው እለት በዓለም ባንክ ድጋፍ የተገነባውን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎብኝተዋል።
ፕሬዚዳንቱ በጉብኝቱ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባታቸው ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ፈጥሯል። ስለዚህ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ማስፋፋት በጣም አስፈላጊና ወሳኝ ነው ብለዋል።
ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ከመፍጠር ባለፈ በርካታ ፋብሪካዎች እንዲገነቡ አድርጓል።
በተለይ በፓርኮቹ ለወጣት ሴቶች የሥራ እድል እየተፈጠረ በመሆኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲኖር ያደርጋል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ በዚህም ወጣቶችና ሴቶች ራሳቸውን ከመቻል አልፈው ለሌሎች መትረፍ እንደቻሉ ተረድቻለሁ ብለዋል።
ስለዚህ ይህንን ማጠናከር ከተቻለ ወደፊት የተሻለ ስኬትና እድገት እንደሀገር ማስመዝገብ ይቻላል ብለዋል።
የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ከጠቅላይ ሚኒስት ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ጋር በመሆኑን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክን መጎብኘታቸው ይታወሳል።
በሳሙኤል ወንደሰን
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባታቸው ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል መፍጠር ማስቻሉን ተመልክቻለሁ ሲሉ የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱን በዛሬው እለት በዓለም ባንክ ድጋፍ የተገነባውን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎብኝተዋል።
ፕሬዚዳንቱ በጉብኝቱ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች መገንባታቸው ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ፈጥሯል። ስለዚህ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ማስፋፋት በጣም አስፈላጊና ወሳኝ ነው ብለዋል።
ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ለበርካታ ዜጎች የሥራ እድል ከመፍጠር ባለፈ በርካታ ፋብሪካዎች እንዲገነቡ አድርጓል።
በተለይ በፓርኮቹ ለወጣት ሴቶች የሥራ እድል እየተፈጠረ በመሆኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲኖር ያደርጋል ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ በዚህም ወጣቶችና ሴቶች ራሳቸውን ከመቻል አልፈው ለሌሎች መትረፍ እንደቻሉ ተረድቻለሁ ብለዋል።
ስለዚህ ይህንን ማጠናከር ከተቻለ ወደፊት የተሻለ ስኬትና እድገት እንደሀገር ማስመዝገብ ይቻላል ብለዋል።
የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት አጃይ ባንጋ ከጠቅላይ ሚኒስት ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር ) ጋር በመሆኑን የቦሌ ለሚ 2 ኢንዱስትሪ ፓርክን መጎብኘታቸው ይታወሳል።
በሳሙኤል ወንደሰን
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም