Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ስሙን በማጠልሸት ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላትን እንደማይታገስ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አስታወቀ
************
(ኢ.ፕ.ድ)

ከውጭና ከውስጥ ያሉ የጥፋት ሀይሎች በመቀናጀት ስሙን በማጥፋት ተግባር የተሰማሩ አካላትን እንደማይታገስ የሀገር መከላከያ ሠራዊት አስታወቀ።

የመከላከያ ሠራዊትብየህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ እነዚህ የጥፋት ሀይሎች የመከላከያ ሰራዊትን ስም የማጥፋት ዘመቻ እያደረጉ ነው።

መከላከያ ሰራዊት አገርን የታደገና አይነተ ብዙ ችግሮችን ተጋፍጦ ድል ያደረገ ሠራዊት ነው ያሉት ኮሎኔል ጌትነት፤
ከዚህ በኋላ የሠራዊቱን ስም የማጥፍት ድርጊት አይታገስም ሲሉ ገልጸዋል።

በጌትነት ምህረቴ
ሐምሌ 25 ቀን 2015 ዓ.ም
የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ ከዓለም ባንክ ፕሬዝደንት አጃይ ባንጋ ጋር ተወያዩ
*******
(ኢ ፕ ድ)

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ ከሚገኙት የዓለም ባንክ ፕሬዝደንት አጃይ ባንጋን ጋር በቢሯቸው ውይይት አድርገዋል፡፡

ውይይቱ በኢትዮጵያና በተቋሙ መካከል ባሉ የጋራ ጉዳዮች፣ በኢትዮጵያና በዓለምን ባንክ መካከል መልካም ግንኙነት ይበልጥ መጠናከር በሚችልበት ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያ ቅድሚያ በምትሰጣቸው የልማት  መስኮች ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል።

በአለም ባንክ የሚደገፉ ፕሮጀክቶች በኢትጵያ ለዋንኞቹ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ጠቅሰው በኢትዮጵያና በአለም ባንክ መካከል ያለው የልማት ትብብር ዘላቂና አካታች እድገት ለማስመዝብ እንደሚያግዝ ሚኒስትሩ አመልተዋል፡፡

በተሻሻለ ምርታማነትና በተወዳዳሪነት መንፈስ ኢኮኖሚያዊ ሽግግርን ለማፋጠን የታቀደውን ሁለተኛውን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ተገባራዊ በማድረግ ሂደት ሊያጋጥሙ ስለሚችሉት  መልካም እድሎችና ፈተናዎች  ክቡር ሚኒስትሩ አብራርተው ከሀገሪቱ የልማት ፍላጎትን  ከማክሮ ኢኮኖሚ ተግዳሮቶች አንጻር ሀገሪቱ ይህን ግዙፍ ማሻሻያ አጀንዳ ውጤታማ በሆነ መልኩ ተግባራዊ እንድታደርግ የአለም ባንክ ድጋፉን እንዲሰጥ የባንኩን ፕሬዚዳንት ጠይቀዋል፡፡

ክቡር አቶ አህመድ ጨምረውም ድህነት እያስከተለ ያለውን ልዩ ተግዳሮት ታሳቢ ያደረገ ምላሽ ከባንኩ የማሻሻያ ሂደት እንደሚጠብቁና በተለይም የባንኩ ድጋፍ ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት አንገብጋቢ ፍላጎት ጋር መጣጣሙን በተመለከተ ለውጥ እንሚጠብቁም ተናግረዋል፡፡

አዲሱ የዓለም ባንክ ፕሬዝዳንት ባንኩ ባካሄደው የለውጥ ሂደት  በአጭር ጊዜ ውስጥ ላበረከቱት አስተዋጽኦ እንዲሁም  የባንኩን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ በቅርቡ የተወሰዱትን ውጤታማ እርምጃዎች  ለፕሬዝደነት አጃይ ባንጋ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️

ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በ100,414 ካሬ ሜትር መሬት ላይ የገነባናቸውን 158 የመስሪያ ሼዶች አስመርቀን በትጋት ለሚሰሩ እጆች ዝግጁ አድርገናል፡፡

በሰኔ ወር የተላለፉ 2,389 ሼዶችን ጨምሮ በጥቅሉ ባዘጋጀናቸው ከ2500 በላይ ሼዶች 17 ሺህ የከተማችን ወጣቶችና ሴቶች እንዲሁም አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው::

ወጣቶችና ሴቶች የለውጡ ዋና ሞተር በመሆናቸው በከተማው ባሉ መጠነ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ እራሳቸውን እና ሃገራቸውን መለወጥ እንዲችሉ የከተማ አስተዳደሩ 24/7 በመስራት ላይ ይገኛል ።በዚህም ዓመት ከወጣቶችና ሴቶች ጋር በነበረን ውይይት ለተጠየቅነው የመስሪያ ቦታ ጥያቄ በተጨባጭ ፈጣን ምላሽ የሰጠንበት ወቅት ነው::

የህዝባችንን የኑሮ ሸክም የሚያቀልሉ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለሁሉም የምትመች "ውብ አዲስ አበባን" ዕውን ለማድረግ በትጋት ማገልገላችንን እንቀጥላለን!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ.ም የስራ ማስታወቂያ‼️
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ -ግብር 6 ነጥብ 25 ቢሊዮን የቡና ችግኞች ተተክለዋል
*****************************
(ኢ ፕ ድ)
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ስድስት ነጥብ 25 ቢሊዮን የቡና ችግኞች መተከላቸውን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡

በባለሥልጣኑ የቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ደፈረስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር አምስት ቢሊዮን በሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ አንድ ነጥብ 25 ቢሊዮን የቡና ችግኞች ተተክለዋል፡፡

የቡና ችግኞችን በማስፋፋት ቀጣይነት ባለው መልኩ ይሠራበታል ያሉት አቶ ፍቃዱ፤ በዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአጠቃላይ ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን በላይ የቡና ችግኞች እንደሚተከሉ ይጠበቃል ብለዋል።

በመስኖ አጠቃቀም ሥርዓት የሚለሙ የቡና ችግኞች በደቡብ፣ በምዕራብና በምሥራቅ እንዲሁም ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106086
መሬት በሊዝ ወስደው ያላለሙ 68 ባለሃብቶች ውል ተቋረጠ
*************************
(ኢ ፕ ድ)

የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ 90 ሄክታር መሬት በሊዝ ወስደው ያላለሙ 68 አልሚዎችን ውል ማቋረጡን እና 1 ሺ 283 አልሚዎች ግንባታ እንዲጀምሩ መወሰኑን አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ ዶክተር ቀነዓ ያደታ የበጀት ዓመቱን አፈጻጸም አስመልክቶ በተካሄደው ግምገማ ላይ እንደተናገሩት፤ አንዳንድ አልሚዎች መሬት ከተቀበሉ በኋለ በወቅቱ ግንባታ ሳይጀምሩ ለረጅም ዓመታት አጥረው ያስቀምጣሉ።

ነገር ግን የሊዝ ሕጉ አንድ መሬት ለልማት ከተወሰደ በኋላ መቼ እንደሚጀመር፤ መቼ ሀምሳ በመቶ መድረስና መቼ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106081
ክረምትን ለበጎ ፈቃድ ያዋሉ ወጣቶች
*************
(ኢ ፕ ድ)

የበጎ ፈቃድ ሥራና ሰብዓዊነት ግለሰቦችን ከራስ ወዳድነት ነፃ በሆነ መንገድ ሌሎች ሰዎችን እንዲረዱ የሚያደርጋቸው ምግባር ነው:: በጎ ፈቃድን ለሚያከናውኑት በጎ ምግባር በምላሹ ምንም ሳይጠይቁ ለሰው ልጅ የሚሰጥ በመሆኑ የተመረጡት ብቻ የሚከውኑት ተግባር ነው።

በጎ አድራጊነት ከማኅበረሰቡ ጎን በመሆን የሚያውቁትን የሚያስተምሩበት የአቅማቸውን ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106085