የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2015 በጀት አመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እያካሄደ ነው
***************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2015 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ በአዳማ ከተማ እያካሄደ ነው።
በግምገማ መድረኩ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት አመቱ በተሟላ ደረጃ ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
አመራሩ ተደራራቢ ሃላፊነትን በመወጣት ረገድ ትልቅ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውቀዋል።
ከንቲባዋ፣ የበጀት አመቱ የሃሳብና የተግባር አንድነት የታየበት፣ መገፋፋቶች የቀነሱበትና ወንድማማችነትና እህትማማችነት ጐልቶ የታየበት አመት እንደነበር ገልጸዋል።
የአመራር ውህደትና አንድነት፣ ደጋፍና ክትትል ለህዝብ ጥቅም በትኩረት መስራት የስኬቱ ምንጭ ነበር ያሉት ከንቲባዋ፣ በበጀት አመቱ በዋናና መሰረታዊ ፍላጐት ላይ ያተኮሩ ከ12ሺ በላይ ፕሮጀክቶችን መፈጸም እንደተቻለ ተናግረዋል።
በአዲሱ ገረመው (አዳማ)
ሐምሌ 29 ቀን 2015 ዓም
***************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2015 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ በአዳማ ከተማ እያካሄደ ነው።
በግምገማ መድረኩ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት አመቱ በተሟላ ደረጃ ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
አመራሩ ተደራራቢ ሃላፊነትን በመወጣት ረገድ ትልቅ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውቀዋል።
ከንቲባዋ፣ የበጀት አመቱ የሃሳብና የተግባር አንድነት የታየበት፣ መገፋፋቶች የቀነሱበትና ወንድማማችነትና እህትማማችነት ጐልቶ የታየበት አመት እንደነበር ገልጸዋል።
የአመራር ውህደትና አንድነት፣ ደጋፍና ክትትል ለህዝብ ጥቅም በትኩረት መስራት የስኬቱ ምንጭ ነበር ያሉት ከንቲባዋ፣ በበጀት አመቱ በዋናና መሰረታዊ ፍላጐት ላይ ያተኮሩ ከ12ሺ በላይ ፕሮጀክቶችን መፈጸም እንደተቻለ ተናግረዋል።
በአዲሱ ገረመው (አዳማ)
ሐምሌ 29 ቀን 2015 ዓም
በአማራ ክልል የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር በመፍታት ሰላም ለማስፈን ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልገሎት ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ (ዶክተር) በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ በመግለጫቸው በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር በመፍታት ሰላምን ለማስፈን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የክልሉን አንዳንድ አካባቢዎች በመደበኛው የህግ ስርዓት መምራት ባለመቻሉ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ከትናንት ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን አስታውሰዋል።
በአዋጁ መሰረትም የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ተቋቁሞ ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።
እዙ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።
በዘላለም ግዛው
ሐምሌ 29 ቀን 2015 ዓም
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልገሎት ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ (ዶክተር) በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ በመግለጫቸው በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር በመፍታት ሰላምን ለማስፈን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የክልሉን አንዳንድ አካባቢዎች በመደበኛው የህግ ስርዓት መምራት ባለመቻሉ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ከትናንት ጀምሮ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን አስታውሰዋል።
በአዋጁ መሰረትም የአስቸኳይ ጊዜ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ተቋቁሞ ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።
እዙ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።
በዘላለም ግዛው
ሐምሌ 29 ቀን 2015 ዓም
የርዕደ መሬት አደጋን ለመቋቋም እንደሀገር ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይገባል
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በስምጥ ሸለቆ የሚከሰቱ የርዕደ መሬት አደጋዎችን ለመቋቋም እንደሀገር የቅድመ ጥንቃቄ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ስፔስሳይንስና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ገለጹ።
ፕሮፌሰር አታላይ አየለ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያና በአካባቢዋ በሚገኙ ሀገራት ከስምጥ ሸለቆ ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የርዕደ መሬት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=106405
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በስምጥ ሸለቆ የሚከሰቱ የርዕደ መሬት አደጋዎችን ለመቋቋም እንደሀገር የቅድመ ጥንቃቄ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ስፔስሳይንስና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር አታላይ አየለ ገለጹ።
ፕሮፌሰር አታላይ አየለ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በኢትዮጵያና በአካባቢዋ በሚገኙ ሀገራት ከስምጥ ሸለቆ ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የርዕደ መሬት ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=106405
በእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ከ500 ሺህ በላይ የሥራ ዕድል ተፈጥሯል
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በ2015 በጀት ዓመት በእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ከ500 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስቴር የበጀት አመቱን ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ እቅድ ግምገማ ባካሄደበት ወቅት የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ እንደገለጹት፤ የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ለበርካቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=106400
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በ2015 በጀት ዓመት በእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ከ500 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስቴር የበጀት አመቱን ዕቅድ አፈጻጸምና የቀጣይ እቅድ ግምገማ ባካሄደበት ወቅት የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ፍቅሩ ረጋሳ እንደገለጹት፤ የእንስሳትና ዓሣ ሀብት ዘርፍ ለበርካቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=106400
የሰው ሀብት ልማት ለአየር መንገዱ የዕድገት ፍኖተ ካርታ ቁልፍ ምሰሶ ነው
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
የሰው ሀብት ልማት ለአየር መንገዱ የዕድገት ስትራቴጂክ ፍኖተ ካርታ አንዱ ቁልፍ ምሰሶ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናገሩ።
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን አንድ ሺህ 551 ተማሪዎችን ትናንትና አስመርቋል።
በምርቃቱ የተገኙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ የሰው ሀብት ልማት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የእድገት ስትራቴጂክ ፍኖተ ካርታ ቁልፍ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=106412
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
የሰው ሀብት ልማት ለአየር መንገዱ የዕድገት ስትራቴጂክ ፍኖተ ካርታ አንዱ ቁልፍ ምሰሶ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ተናገሩ።
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን አንድ ሺህ 551 ተማሪዎችን ትናንትና አስመርቋል።
በምርቃቱ የተገኙት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፤ የሰው ሀብት ልማት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የእድገት ስትራቴጂክ ፍኖተ ካርታ ቁልፍ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=106412
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ 583 ዶክተሮችን አስመረቀ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ በቅድም ምረቃናና ድህረ ምረቃ 583 ዶክተሮችን ዛሬ አስመረቀ።
በምረቃ ስነስርአቱ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አስፋ፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ድጉማና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
በ"ሰብስፔሻሊቲ፣ በነርሲንግ ስፔሻሊቲ፣ በፐብሊክ ሄልዝ፣ በሌሎች ዘርፎች አስመርቋል።
የኮሌጁ ፕሮቮስት ዶክተር ሲሳይ ሰርጉ እንዳሉት፤ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለመስጠት፣ ብቁ የጤና ባለሙያዎችን ለማፍራት ከመማር ማስተማሩ ጐን ለጐን ችግር ፈቺ ምርምሮችን በመስራት የህክምና አሰጣጡ የዘመነ እንዲሆንና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን እየሰራ ነው።
ኮሌጁ በ35 የስልጠና መርሃግብሮች የህክምና ባለሙያዎችን በማሰልጠን የህክምናው ዘርፍ እንዲዘምን ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ሲሳይ፣ ለአገሪቱ የጤና ስርአት መሻሻል የበኩሉን ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል።
ከሚሰጣቸው የስልጠና መርሃግብሮች ሰባቱ በዚህ አመት የተጀመሩ መሆናቸውን ጠቅሰው በቀጣይነትም ምርምሮችን በመስራት የጤና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።
ምሩቃን በቀጣይ በኮሌጁ የቀሰሙትን እውቀት በተግባር በመግለጽ ሙያዊ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ዶክተር ሲሳይ ጥሪ አቅርበዋል።
ኮሌጁ ያስመረቃቸው በህክምና 395፣ በህብረተሰብ ጤና፣ 78፣ በነርስ 110 በድምሩ 583 ሲሆኑ 185ቱ ሴቶች ናቸው።
ከምሩቃኑ መካክል በተሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና 151ዱ በሙሉ ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ ማለፋቸው ተገልጿል።
በሞገስ ተስፋ
ሐምሌ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ በቅድም ምረቃናና ድህረ ምረቃ 583 ዶክተሮችን ዛሬ አስመረቀ።
በምረቃ ስነስርአቱ ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አስፋ፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ድጉማና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።
በ"ሰብስፔሻሊቲ፣ በነርሲንግ ስፔሻሊቲ፣ በፐብሊክ ሄልዝ፣ በሌሎች ዘርፎች አስመርቋል።
የኮሌጁ ፕሮቮስት ዶክተር ሲሳይ ሰርጉ እንዳሉት፤ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለመስጠት፣ ብቁ የጤና ባለሙያዎችን ለማፍራት ከመማር ማስተማሩ ጐን ለጐን ችግር ፈቺ ምርምሮችን በመስራት የህክምና አሰጣጡ የዘመነ እንዲሆንና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆን እየሰራ ነው።
ኮሌጁ በ35 የስልጠና መርሃግብሮች የህክምና ባለሙያዎችን በማሰልጠን የህክምናው ዘርፍ እንዲዘምን ለማስቻል እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ሲሳይ፣ ለአገሪቱ የጤና ስርአት መሻሻል የበኩሉን ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል።
ከሚሰጣቸው የስልጠና መርሃግብሮች ሰባቱ በዚህ አመት የተጀመሩ መሆናቸውን ጠቅሰው በቀጣይነትም ምርምሮችን በመስራት የጤና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።
ምሩቃን በቀጣይ በኮሌጁ የቀሰሙትን እውቀት በተግባር በመግለጽ ሙያዊ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ዶክተር ሲሳይ ጥሪ አቅርበዋል።
ኮሌጁ ያስመረቃቸው በህክምና 395፣ በህብረተሰብ ጤና፣ 78፣ በነርስ 110 በድምሩ 583 ሲሆኑ 185ቱ ሴቶች ናቸው።
ከምሩቃኑ መካክል በተሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና 151ዱ በሙሉ ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ ማለፋቸው ተገልጿል።
በሞገስ ተስፋ
ሐምሌ 30 ቀን 2015 ዓ.ም
ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ የተሳታፊ ልየታ ሥራ በአስር ቀናት ውስጥ ይጀምራል
*************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ የሚደረገው የተሳታፊ ልየታ ሥራ በአስር ቀናት ውስጥ እንደሚጀምር አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሲዳማ፣ በሐረሪ እና በደቡብ ምዕራብ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ የተሳታፊዎች ልየታ ሥራ በአብዛኛው ተጠናቋል።
በቤኒሻንጉልና በጋምቤላ ክልሎች ወደ ተሳታፊዎች ልየታ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106452
*************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ የሚደረገው የተሳታፊ ልየታ ሥራ በአስር ቀናት ውስጥ እንደሚጀምር አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሲዳማ፣ በሐረሪ እና በደቡብ ምዕራብ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ ከተማ የተሳታፊዎች ልየታ ሥራ በአብዛኛው ተጠናቋል።
በቤኒሻንጉልና በጋምቤላ ክልሎች ወደ ተሳታፊዎች ልየታ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106452
ኢትዮጵያ የገዛችው አንድ ሚሊዮን ኩንታል ስኳር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ጅቡቲ ወደብ ይደርሳል
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢትዮጵያ የገዛችው አንድ ሚሊዮን ኩንታል ስኳር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ጅቡቲ ወደብ የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አስታወቀ።
ተጨማሪ አንድ ሚሊዮን ስኳር ግዢ ለመፈፀም እየተሠራ ነው ተብሏል።
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኮርፖሬት ጉዳዮች ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዘመድኩን ተክሌ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በ2014 ዓመተ ምህረት የኮቪድ ወረርሽኝ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106524
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢትዮጵያ የገዛችው አንድ ሚሊዮን ኩንታል ስኳር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ጅቡቲ ወደብ የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አስታወቀ።
ተጨማሪ አንድ ሚሊዮን ስኳር ግዢ ለመፈፀም እየተሠራ ነው ተብሏል።
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኮርፖሬት ጉዳዮች ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዘመድኩን ተክሌ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በ2014 ዓመተ ምህረት የኮቪድ ወረርሽኝ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106524
ሁለት ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች የኮሌራ ክትባት አግኝተዋል
- በሦስት ክልሎች በሚገኙ 35 ወረዳዎች ላይ የአተት በሽታን መቆጣጠር ተችሏል
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ለአንድ ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ዜጎች የኮሌራ ክትባት መስጠቱን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳወቀ።
ኢንስቲትዩቱ 85 የሕክምና መስጫ ጣቢያዎችን በማቋቋም ሕክምና የመስጠት ተግባር እያከናወነ መሆኑ ተመላክቷል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ሀይሉ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ የክረምት ወራትን …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106503
- በሦስት ክልሎች በሚገኙ 35 ወረዳዎች ላይ የአተት በሽታን መቆጣጠር ተችሏል
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ለአንድ ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ዜጎች የኮሌራ ክትባት መስጠቱን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳወቀ።
ኢንስቲትዩቱ 85 የሕክምና መስጫ ጣቢያዎችን በማቋቋም ሕክምና የመስጠት ተግባር እያከናወነ መሆኑ ተመላክቷል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ሀይሉ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ የክረምት ወራትን …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106503
ሦስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ዜጎች ከፍሎራይድ የጸዳ ውሃ አያገኙም
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በስምጥ ሸለቆ አካባቢ የሚኖሩ ሦስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ዜጎች ከፍሎራይድ የጸዳ ውሃ እንደማያገኙ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ።
በሚኒስቴሩ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ሐይማኖት በለጠ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ከ12 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በስምጥ ሸለቆና በፍሎራይድ በተጠቃ አካባቢ ይኖራሉ። ከዚህ ውስጥ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106501
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በስምጥ ሸለቆ አካባቢ የሚኖሩ ሦስት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ዜጎች ከፍሎራይድ የጸዳ ውሃ እንደማያገኙ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለጸ።
በሚኒስቴሩ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ ሐይማኖት በለጠ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ከ12 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በስምጥ ሸለቆና በፍሎራይድ በተጠቃ አካባቢ ይኖራሉ። ከዚህ ውስጥ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106501
የኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀል ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያስችላል
*************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የብሪክስ የአባልነት ጥያቄ ተቀባይነት ካገኘ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ እንደሚሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ እና እስያ ጥናትና ምርምር ማዕከል መምህር ዶክተር ሳሙኤል ተፈራ ተናገሩ።
ዶክተር ሳሙኤል ተፈራ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ብሪክስ ውስጥ ያሉ ሀገራት ከዓለም ኢኮኖሚ 31 ነጥብ ሰባት በመቶ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106485
*************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የብሪክስ የአባልነት ጥያቄ ተቀባይነት ካገኘ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ እንደሚሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ እና እስያ ጥናትና ምርምር ማዕከል መምህር ዶክተር ሳሙኤል ተፈራ ተናገሩ።
ዶክተር ሳሙኤል ተፈራ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ብሪክስ ውስጥ ያሉ ሀገራት ከዓለም ኢኮኖሚ 31 ነጥብ ሰባት በመቶ …
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=106485
ግብርና ሚኒስቴር 33 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው የወተት ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን ለክልሎች በድጋፍ አበረከተ
****************
(ኢ ፕ ድ)
ግብርና ሚኒስቴር 33 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው ሰባት የወተት ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን ለክልሎች በድጋፍ አበረከተ።
ተሽከርካሪዎቹ ከዓለም ባንክ በድጋፍ የተገኙ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን የወተት ግብይትን በማሳለጥ የሌማት ትሩፋትን ከግብ እንዲደርስ የሚያግዙ መሆናቸውም ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ ያበረከታቸውን ተሽከርካሪዎች ድጋፍ የተደረገላቸው የክልል ግብርና እና እንስሳት ሃብት ቢሮ ሃላፊዎች ተረክበዋል።
ተሽከርካሪዎቹ በድጋፍ የተበረከቱትም ለኦሮሚያ፣ ለአማራ፣ ለደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች እንዲሁም ለሲዳማ ክልሎች መሆኑ ተገልጿል።
ተሽከርካሪዎቹ በአንድ ጊዜ 10 ሺህ ሊትር የወተት ምርቶችን ማሰባሰብ እና በተፈለገበት ቦታ ማድረስ የሚችሉ መሆናቸው ተጠቅሷል።
ተሽከርካሪዎቹ ወተት በስፋት የሚያመርቱ አካባቢዎች ላይ አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚደረጉም ተመላክቷል።
በርክክቡ ወቅት ባለፈው በጀት ዓመት በአገር አቀፍ ደረጃ 8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ሊትር ወተት መመረቱ ገልጸዋል።
ይህ የሆነው የእንስሳት ማሻሻያ፣ ዝርያ ማሻሻል እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን መጠቀም በመቻሉ እንደሆነ ተመላክቷል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ በመጪዎቹ ዓመታትም በአገር አቀፍ ደረጃ 11 ቢሊዮን ሊትር ወተት በዓመት ለማምረት ዕቅድ ስለመያዙም ተጠቁሟል።
ነሀሴ 1 ቀን 2015 ዓም
****************
(ኢ ፕ ድ)
ግብርና ሚኒስቴር 33 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸው ሰባት የወተት ማጓጓዣ ተሽከርካሪዎችን ለክልሎች በድጋፍ አበረከተ።
ተሽከርካሪዎቹ ከዓለም ባንክ በድጋፍ የተገኙ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን የወተት ግብይትን በማሳለጥ የሌማት ትሩፋትን ከግብ እንዲደርስ የሚያግዙ መሆናቸውም ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ ያበረከታቸውን ተሽከርካሪዎች ድጋፍ የተደረገላቸው የክልል ግብርና እና እንስሳት ሃብት ቢሮ ሃላፊዎች ተረክበዋል።
ተሽከርካሪዎቹ በድጋፍ የተበረከቱትም ለኦሮሚያ፣ ለአማራ፣ ለደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች እንዲሁም ለሲዳማ ክልሎች መሆኑ ተገልጿል።
ተሽከርካሪዎቹ በአንድ ጊዜ 10 ሺህ ሊትር የወተት ምርቶችን ማሰባሰብ እና በተፈለገበት ቦታ ማድረስ የሚችሉ መሆናቸው ተጠቅሷል።
ተሽከርካሪዎቹ ወተት በስፋት የሚያመርቱ አካባቢዎች ላይ አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚደረጉም ተመላክቷል።
በርክክቡ ወቅት ባለፈው በጀት ዓመት በአገር አቀፍ ደረጃ 8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ሊትር ወተት መመረቱ ገልጸዋል።
ይህ የሆነው የእንስሳት ማሻሻያ፣ ዝርያ ማሻሻል እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን መጠቀም በመቻሉ እንደሆነ ተመላክቷል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ በመጪዎቹ ዓመታትም በአገር አቀፍ ደረጃ 11 ቢሊዮን ሊትር ወተት በዓመት ለማምረት ዕቅድ ስለመያዙም ተጠቁሟል።
ነሀሴ 1 ቀን 2015 ዓም