አሕጉራትን እያስተሳሰረ ያለው “የቻይና ቀበቶ"
******
(ኢ ፕ ድ)
ቻይና እ.አ.አ. በ 2013 ይፋ ያደረገችው “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” እስያን፣ አውሮፓንና አፍሪካን በየብስ፣ በአየርና በውቅያኖስ በመሠረተ ልማት ለማስተሳሰር ያለመ ነው። ይህም የዓለም ሀገራትን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎች ለማቀራረብ የተቀረጸ ፕሮጀክት መሆኑ ነው የሚገለጸው።
ከ151 ሀገራት የተውጣጡ ከ10 ሺህ በላይ ተወካዮችና 41 ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የተሳተፉበት ሦስተኛው የ “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” ጉባዔ በቅርቡ በቻይና ተካሂዷል። መድረኩ የፕሮጀክቱ 10ኛ ዓመት የተከበረበትም ጭምር ነው።
ለመሆኑ ይህ የቻይና ግዙፍ የትብብር ማዕቀፍ ባለፉት 10 ዓመታት በተለይም ለአፍሪካውያን ምን አስገኝቷል? ከምዕራባውያን የትብብር ማዕቀፎችስ በምን ይለያል ?
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህሩ ረዳት ፕሮፌሰር ዳዊት ሃዬሶ (ዶ/ር) “የዓለምን ኢኮኖሚ ለመምራት ወደፊት እየተጠጋች ያለች ሀገር ናት” የሚሏት ቻይና፣ ዘላቂ የሆነ የጋራ ዕድገት ማስመዝገብ የሚቻለው ከአጋር ሀገራት ጋር በጋራ ማደግ ሲቻል ነው በሚል መርህ አህጉራትን የሚያስተሳስረውን “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” ቀርጻ ላለፉት 10 ዓመታት ስትተገብረው መቆየቷን ይናገራሉ።
ኢኒሼቲቩ ብዙ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞች አሉት የሚሉት ረዳት ፕሮፌሰሩ፣ ባለፉት 10 ዓመታት የአፍሪካ ሀገራትን ተጠቃሚ አድርጓል ባይ ናቸው። ከኢትዮጵያ ብንነሳ ከአዲስ አበባ – ጅቡቲ ያለው የባቡር መንገድ የተገነባው በዚህ ኢኒሼቲቭ ድጋፍ ነው። ግንባታው ከዚህ በፊት ተሳቢ መኪኖች በአነስተኛ መጠን እየተመላለሱ.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=113182
******
(ኢ ፕ ድ)
ቻይና እ.አ.አ. በ 2013 ይፋ ያደረገችው “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” እስያን፣ አውሮፓንና አፍሪካን በየብስ፣ በአየርና በውቅያኖስ በመሠረተ ልማት ለማስተሳሰር ያለመ ነው። ይህም የዓለም ሀገራትን በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ በቱሪዝምና በሌሎች ዘርፎች ለማቀራረብ የተቀረጸ ፕሮጀክት መሆኑ ነው የሚገለጸው።
ከ151 ሀገራት የተውጣጡ ከ10 ሺህ በላይ ተወካዮችና 41 ዓለም አቀፍ ድርጅቶች የተሳተፉበት ሦስተኛው የ “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” ጉባዔ በቅርቡ በቻይና ተካሂዷል። መድረኩ የፕሮጀክቱ 10ኛ ዓመት የተከበረበትም ጭምር ነው።
ለመሆኑ ይህ የቻይና ግዙፍ የትብብር ማዕቀፍ ባለፉት 10 ዓመታት በተለይም ለአፍሪካውያን ምን አስገኝቷል? ከምዕራባውያን የትብብር ማዕቀፎችስ በምን ይለያል ?
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት መምህሩ ረዳት ፕሮፌሰር ዳዊት ሃዬሶ (ዶ/ር) “የዓለምን ኢኮኖሚ ለመምራት ወደፊት እየተጠጋች ያለች ሀገር ናት” የሚሏት ቻይና፣ ዘላቂ የሆነ የጋራ ዕድገት ማስመዝገብ የሚቻለው ከአጋር ሀገራት ጋር በጋራ ማደግ ሲቻል ነው በሚል መርህ አህጉራትን የሚያስተሳስረውን “ቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ” ቀርጻ ላለፉት 10 ዓመታት ስትተገብረው መቆየቷን ይናገራሉ።
ኢኒሼቲቩ ብዙ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞች አሉት የሚሉት ረዳት ፕሮፌሰሩ፣ ባለፉት 10 ዓመታት የአፍሪካ ሀገራትን ተጠቃሚ አድርጓል ባይ ናቸው። ከኢትዮጵያ ብንነሳ ከአዲስ አበባ – ጅቡቲ ያለው የባቡር መንገድ የተገነባው በዚህ ኢኒሼቲቭ ድጋፍ ነው። ግንባታው ከዚህ በፊት ተሳቢ መኪኖች በአነስተኛ መጠን እየተመላለሱ.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=113182
የአፍሪካ ሀገራት በማዕድን ውጤቶች ላይ ዕሴት በመጨመር ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ አለባቸው
*****
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ሀገራት ከድህነት ለመውጣት ያስቀመጡትን አጀንዳ 2063ን ለማሳካት በማዕድን ዘርፉ ጥሬ እቃዎችን ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ በመላክ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ እንደሚገባቸው ተገለጸ።
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በማእድን ዘርፉ ላይ በማተኮር በጋራ ያዘጋጁት የውይይት መድረክ ትናንት ተካሂዷል።
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚደንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር)፤ ኮሚሽኑ በእውቀት ግንባታ፣ በፈጠራና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባዋል። አዳዲስ ምርምሮችን በማፍለቅ ምርት ከውጭ ማስገባት .....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=113183
*****
(ኢ ፕ ድ)
የአፍሪካ ሀገራት ከድህነት ለመውጣት ያስቀመጡትን አጀንዳ 2063ን ለማሳካት በማዕድን ዘርፉ ጥሬ እቃዎችን ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ በመላክ ተጠቃሚነታቸውን ማሳደግ እንደሚገባቸው ተገለጸ።
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲና የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን በማእድን ዘርፉ ላይ በማተኮር በጋራ ያዘጋጁት የውይይት መድረክ ትናንት ተካሂዷል።
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚደንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር)፤ ኮሚሽኑ በእውቀት ግንባታ፣ በፈጠራና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባዋል። አዳዲስ ምርምሮችን በማፍለቅ ምርት ከውጭ ማስገባት .....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=113183
በገበታ ለትውልድ በመገንባት ላይ ያሉና የሚገነቡ ፕሮጀክቶች ለቱሪዝም ዘርፉ ሰፊ ዕድል ይፈጥራሉ‼️
በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ የተገነቡ፣ በመገንባት ላይ ያሉና የሚገነቡ ፕሮጀክቶች ለቱሪዝም ዘርፉ ሰፊ ዕድሎች እየፈጠሩለት ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ በያዝነው የፈረንጆች አመት በመጀመሪያዎቹ 7 ወራት የዓለም ቱሪዝምን በመሳብ 7ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የዓለም አቀፉ ቱሪዝም ተቋም አስታወቀ፡፡ ተቋሙ 2023 ከጥር እስከ ሐምሌ ያለውን የሀገራትን የቱሪዝም ፍሰት ከ2019 ጋር በማነጻጸር ይፋ አድርጓል፡፡
ኢትዩጵያ በያዝነው 2016 ዓ.ም መጀመሪያ ሁለት ቅርሶቿን በዩኔስኮ መዝገብ አካትታለች።
በተያዘው 2016 በጀት ዓመት አንድ ሚሊዮን የውጭ ሀገራት ዜጎች ኢትዮጵያን ይጎበኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ከሚመጡ የውጭ ሀገራት ዜጎች ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት ማቀዱን ኢፕድ መዘገቡ ይታወሳል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ የተገነቡ፣ በመገንባት ላይ ያሉና የሚገነቡ ፕሮጀክቶች ለቱሪዝም ዘርፉ ሰፊ ዕድሎች እየፈጠሩለት ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ በያዝነው የፈረንጆች አመት በመጀመሪያዎቹ 7 ወራት የዓለም ቱሪዝምን በመሳብ 7ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የዓለም አቀፉ ቱሪዝም ተቋም አስታወቀ፡፡ ተቋሙ 2023 ከጥር እስከ ሐምሌ ያለውን የሀገራትን የቱሪዝም ፍሰት ከ2019 ጋር በማነጻጸር ይፋ አድርጓል፡፡
ኢትዩጵያ በያዝነው 2016 ዓ.ም መጀመሪያ ሁለት ቅርሶቿን በዩኔስኮ መዝገብ አካትታለች።
በተያዘው 2016 በጀት ዓመት አንድ ሚሊዮን የውጭ ሀገራት ዜጎች ኢትዮጵያን ይጎበኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ። ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ ከሚመጡ የውጭ ሀገራት ዜጎች ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት ማቀዱን ኢፕድ መዘገቡ ይታወሳል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
161 የፌዴራል ተቋማት በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት ግዢ ለመፈጸም ዕቅድ አቅርበዋል
****
(ኢ ፕ ድ)
ከ169 የፌዴራል ተቋማት 161 ተቋማት በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት ግዢ ለመፈጸም ዕቅድ አቅርበዋል።
የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ኤሌክትሮኒክስ ግዢ ላይ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ዉይይት እያደረገ ይገኛል።
በዉይይቱ ላይ የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ እንደገለጹት በተያዘዉ በጀት ዓመት 161 ተቋማት ዕቅድ ያቀረቡ ሲሆን ቀሪዎቹም በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ያቀርባሉ።
በ2016 ዓ.ም የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ግዢ ሙሉ ለሙሉ በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ብቻ እንደሚፈጸም ጠቁመዋል።
በግዢ ስርዓቱ ሲያጋጥም የነበረዉን ሌብነት ከማስቀረቱም በተጨማሪ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ ነዉ ብለዋል።
በመጀመሪያወዉ ሩብ ዓመትም 2802 ጨረታዎች በኤሌክትሮኒክስ መንገድ መዉጣታቸዉ ተጠቁሟል። 3,800 የሚጠጉ የንግዱ ማህበረሰብም በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ግዢ እየፈጸመ እንደሆነም ተገልጿል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
****
(ኢ ፕ ድ)
ከ169 የፌዴራል ተቋማት 161 ተቋማት በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት ግዢ ለመፈጸም ዕቅድ አቅርበዋል።
የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ኤሌክትሮኒክስ ግዢ ላይ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ዉይይት እያደረገ ይገኛል።
በዉይይቱ ላይ የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀጂ ኢብሳ እንደገለጹት በተያዘዉ በጀት ዓመት 161 ተቋማት ዕቅድ ያቀረቡ ሲሆን ቀሪዎቹም በአንድ ወር ጊዜ ዉስጥ ያቀርባሉ።
በ2016 ዓ.ም የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ግዢ ሙሉ ለሙሉ በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ብቻ እንደሚፈጸም ጠቁመዋል።
በግዢ ስርዓቱ ሲያጋጥም የነበረዉን ሌብነት ከማስቀረቱም በተጨማሪ ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ ነዉ ብለዋል።
በመጀመሪያወዉ ሩብ ዓመትም 2802 ጨረታዎች በኤሌክትሮኒክስ መንገድ መዉጣታቸዉ ተጠቁሟል። 3,800 የሚጠጉ የንግዱ ማህበረሰብም በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ግዢ እየፈጸመ እንደሆነም ተገልጿል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
ኢትዮጵያ እና ቻይና አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ
****
(ኢ ፕ ድ)
ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ኢትዮጵያ እና ቻይና በአስተዳደር ዘርፍ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
ከቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ የልዑካን ጋር የሁለቱን ሀገራት አጋርነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ መስኮች አብሮ በመስራት የቆየ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቁመው፤ በአሁኑ ጊዜ የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ በአስተዳደር ስልጠና እንዲሁም በጥናትና ምርምር ያለውን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ያለውን ዝግጅት አድንቀዋል፡፡
አካዳሚው በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አቅም ያለውና የበርካታ ምሁራን ስብስብ በመሆኑ፤ ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ተዛማጅ የሆነ ልምድ በማጋራት የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር እንደሚገባ አፈጉባኤው ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ፕሮፌሰር ጎንግ ዌቢን ቻይና ከኢትዮጵያም ሆነ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸው፤ አካዳሚው በስልጠናም ሆነ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ እና የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ በቅርቡ የሚፈራረሙት የትብብር ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት እንደሚያጠናክርም የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
****
(ኢ ፕ ድ)
ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ኢትዮጵያ እና ቻይና በአስተዳደር ዘርፍ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
ከቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ የልዑካን ጋር የሁለቱን ሀገራት አጋርነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ መስኮች አብሮ በመስራት የቆየ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቁመው፤ በአሁኑ ጊዜ የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ በአስተዳደር ስልጠና እንዲሁም በጥናትና ምርምር ያለውን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ያለውን ዝግጅት አድንቀዋል፡፡
አካዳሚው በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አቅም ያለውና የበርካታ ምሁራን ስብስብ በመሆኑ፤ ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ተዛማጅ የሆነ ልምድ በማጋራት የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር እንደሚገባ አፈጉባኤው ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ፕሮፌሰር ጎንግ ዌቢን ቻይና ከኢትዮጵያም ሆነ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸው፤ አካዳሚው በስልጠናም ሆነ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ እና የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ በቅርቡ የሚፈራረሙት የትብብር ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት እንደሚያጠናክርም የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም