ኢትዮጵያ እና ቻይና አጋርነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ ገለጹ
****
(ኢ ፕ ድ)
ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ኢትዮጵያ እና ቻይና በአስተዳደር ዘርፍ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
ከቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ የልዑካን ጋር የሁለቱን ሀገራት አጋርነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ መስኮች አብሮ በመስራት የቆየ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቁመው፤ በአሁኑ ጊዜ የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ በአስተዳደር ስልጠና እንዲሁም በጥናትና ምርምር ያለውን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ያለውን ዝግጅት አድንቀዋል፡፡
አካዳሚው በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አቅም ያለውና የበርካታ ምሁራን ስብስብ በመሆኑ፤ ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ተዛማጅ የሆነ ልምድ በማጋራት የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር እንደሚገባ አፈጉባኤው ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ፕሮፌሰር ጎንግ ዌቢን ቻይና ከኢትዮጵያም ሆነ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸው፤ አካዳሚው በስልጠናም ሆነ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ እና የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ በቅርቡ የሚፈራረሙት የትብብር ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት እንደሚያጠናክርም የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
****
(ኢ ፕ ድ)
ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ኢትዮጵያ እና ቻይና በአስተዳደር ዘርፍ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ ያላቸውን አጋርነት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
ከቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ የልዑካን ጋር የሁለቱን ሀገራት አጋርነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።
ኢትዮጵያ እና ቻይና በተለያዩ መስኮች አብሮ በመስራት የቆየ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቁመው፤ በአሁኑ ጊዜ የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ በአስተዳደር ስልጠና እንዲሁም በጥናትና ምርምር ያለውን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ያለውን ዝግጅት አድንቀዋል፡፡
አካዳሚው በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አቅም ያለውና የበርካታ ምሁራን ስብስብ በመሆኑ፤ ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር ተዛማጅ የሆነ ልምድ በማጋራት የሁለቱን ሀገራት ስትራቴጂካዊ አጋርነት ማጠናከር እንደሚገባ አፈጉባኤው ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ፕሮፌሰር ጎንግ ዌቢን ቻይና ከኢትዮጵያም ሆነ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸው፤ አካዳሚው በስልጠናም ሆነ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ለኢትዮጵያ የሚያደርገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
የቻይና ብሄራዊ የአስተዳደር አካዳሚ እና የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ በቅርቡ የሚፈራረሙት የትብብር ስምምነት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት እንደሚያጠናክርም የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
በ16 ሚሊየን ዶላር በጀት የአፍሪካ ሚኒ ግሪድ ፕሮግራም ተጀምሯል
*****
(ኢ ፕ ድ)
በ16 ሚሊየን ዶላር በጀት 624 ኪሎዋት ሀይል በማመንጨት 32ሺ ግለሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የአፍሪካ ሚኒ ግሪድ ፕሮግራም ተጀምሯል።
ግሎባል ኢንቫሮመንት ፋሲሊቲ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የአፍሪካ ሚኒ ግሪድ ፕሮግራም አስጀመረ
የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ እንደገለጹት ብሔራዊ ኤሌክትርፍኬሽን ፕሮግራም ተቀርፆ በመንቀሳቀስ በ2030 ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
ብሄራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም 35 በመቶ ከመስመር ውጭ (off grid) ለመሸፈን የታለመ በመሆኑ፤ መሰል ፕሮጀክቶች ፕሮግራሙን ለማሳካት ጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የአፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮጀክት 16 ሚሊየን ዶላር የተመደበለት፤ ሲሆን 624 ኪሎዋት ሀይል በማመንጨትና 32ሺ ግለሰቦችን ተጠቃሚ በማድረግ፤ 120 ሰዎች የስራ እድልን ይፈጥራል ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የአየር ንብረትን ለመከላከል ሚና እንዳለው ጠቅሰው፤ በዚህ ስራ ከ16ሺ ቶን በላይ የካርበን ልቀትን ለመቀነስ እንደሚረዳና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
*****
(ኢ ፕ ድ)
በ16 ሚሊየን ዶላር በጀት 624 ኪሎዋት ሀይል በማመንጨት 32ሺ ግለሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የአፍሪካ ሚኒ ግሪድ ፕሮግራም ተጀምሯል።
ግሎባል ኢንቫሮመንት ፋሲሊቲ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የአፍሪካ ሚኒ ግሪድ ፕሮግራም አስጀመረ
የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ እንደገለጹት ብሔራዊ ኤሌክትርፍኬሽን ፕሮግራም ተቀርፆ በመንቀሳቀስ በ2030 ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
ብሄራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም 35 በመቶ ከመስመር ውጭ (off grid) ለመሸፈን የታለመ በመሆኑ፤ መሰል ፕሮጀክቶች ፕሮግራሙን ለማሳካት ጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
የአፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮጀክት 16 ሚሊየን ዶላር የተመደበለት፤ ሲሆን 624 ኪሎዋት ሀይል በማመንጨትና 32ሺ ግለሰቦችን ተጠቃሚ በማድረግ፤ 120 ሰዎች የስራ እድልን ይፈጥራል ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የአየር ንብረትን ለመከላከል ሚና እንዳለው ጠቅሰው፤ በዚህ ስራ ከ16ሺ ቶን በላይ የካርበን ልቀትን ለመቀነስ እንደሚረዳና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
"ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ ለመሥራት ቁርጠኛ ናት"
-ሚስተር ሺን ኪንሚን በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ
******
(ኢ ፕ ድ)
ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ ለመሥራት ቁርጠኛ ናት ሲሉ በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ ሚስተር ሺን ኪንሚን ገለጹ፡፡ ሚስተር ሺን ኪንሚን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ ቻይና በቱሪዝም ዘርፍ እስካሁን ካከናወነቻቸው የትብብር ሥራዎች በላቀ ሁኔታ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ናት።
ቻይናና ኢትዮጵያ በዘርፉ ውጤታማ ሥራዎች ለማከናወን እርስ በእርሳቸው የሚማሩበት ዕድል አላቸው ያሉት ሚስተር ሺን፤ የቻይና የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ኢትዮጵያን ከ30 ሀገራት መካከል አዲስ መዳረሻ አድርጎ መሰየሙ በዘርፉ በጋራ ለመሥራት ያለውን ፍላጎት ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
በቱሪዝም ዘርፉ ቻይና ኢትዮጵያን ተመራጭ ማድረጓ በርካታ ቻይናውያን ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ያበረታታል ሲሉ አስረድተዋል። አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የአፍሪካ መዲናና የቻይና መግቢያ በር ናት ያሉት ሚስተር ሺን በከተማዋ ያለውን የኢኮ-ቱሪዝም ሥፍራዎች ማስፋፋት ለዘርፉ ዕድገት.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=113229
-ሚስተር ሺን ኪንሚን በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ
******
(ኢ ፕ ድ)
ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ ለመሥራት ቁርጠኛ ናት ሲሉ በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ ሚስተር ሺን ኪንሚን ገለጹ፡፡ ሚስተር ሺን ኪንሚን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ ቻይና በቱሪዝም ዘርፍ እስካሁን ካከናወነቻቸው የትብብር ሥራዎች በላቀ ሁኔታ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ናት።
ቻይናና ኢትዮጵያ በዘርፉ ውጤታማ ሥራዎች ለማከናወን እርስ በእርሳቸው የሚማሩበት ዕድል አላቸው ያሉት ሚስተር ሺን፤ የቻይና የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ኢትዮጵያን ከ30 ሀገራት መካከል አዲስ መዳረሻ አድርጎ መሰየሙ በዘርፉ በጋራ ለመሥራት ያለውን ፍላጎት ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
በቱሪዝም ዘርፉ ቻይና ኢትዮጵያን ተመራጭ ማድረጓ በርካታ ቻይናውያን ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ ያበረታታል ሲሉ አስረድተዋል። አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የአፍሪካ መዲናና የቻይና መግቢያ በር ናት ያሉት ሚስተር ሺን በከተማዋ ያለውን የኢኮ-ቱሪዝም ሥፍራዎች ማስፋፋት ለዘርፉ ዕድገት.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=113229