የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ከአፋሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ጋር ተወያዩ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃመት ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ፣ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት በማውሳት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረትን በአባልነት እና በአስተናጋጅነት ለመደገፍ ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ሙሳ ፋኪ አምባሳደር ታዬ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በመሾማቸው የተሰማቸው ደስታ ገልፀው ፤ ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ በተለይ፣በአፍሪካ ፀጥታ እና መረጋጋትን በማስፈን ረገድ ያላትን ሚና ክቡር ሙሳ ፋቂ ያደነቁ ሲሆን ተጠናክሮ እንዲቀጥል መጠየቃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃመት ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ፣ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን መካከል ያለውን የቆየ ግንኙነት በማውሳት ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረትን በአባልነት እና በአስተናጋጅነት ለመደገፍ ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ሙሳ ፋኪ አምባሳደር ታዬ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በመሾማቸው የተሰማቸው ደስታ ገልፀው ፤ ትብብራቸውን እንደሚያጠናክሩም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ በተለይ፣በአፍሪካ ፀጥታ እና መረጋጋትን በማስፈን ረገድ ያላትን ሚና ክቡር ሙሳ ፋቂ ያደነቁ ሲሆን ተጠናክሮ እንዲቀጥል መጠየቃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢጋድ ዋና ፀሃፊ አዲስ አበባ ገቡ
************
(ኢ.ፕ.ድ )
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በአፍሪካ ህብረት 44ኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ እና በ37ኛው የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
ዋና ፀሃፊው ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል ።
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
************
(ኢ.ፕ.ድ )
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥት (ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በአፍሪካ ህብረት 44ኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ እና በ37ኛው የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።
ዋና ፀሃፊው ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል ።
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
በመዲናዋ ለኮንስትራክሽን እና ለጭነት ተሽከርካሪዎች የተከለከሉ መንገዶች ይፋ ሆኑ
*****
(ኢ ፕ ድ)
ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ የትራፊክ ፍሠቱን የተሳለጠ ለማድረግ እንዲቻል ለኮንስትራክሽንና ለጭነት ተሽከርካሪዎች የተከለከሉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ቀደም ሲል በከተማው ላይ በደንብ ተላላፊ አሽከርካሪዎች የተከሰተውን ተመሣሣይ ጥፋት መነሻ አድርጎ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክት ማስተላለፋ ይታወሳል።
በመሆኑም የትራፊክ ህግና ደንብን በማስከበር የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋን ከመከላከል ባሻገር ጤናማ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር እንዲሁም በመዲናዋ በቀጣይ ቀናት ለሚካሔደው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔ የፀጥታ አካላት ለሚያከናውኑት የፀጥታ ስራ አመቺ ሁኔታን ለመፍጠር እንዲቻል ከዚህ በታች በተገለፁት መንገዶች፤
👉 ቦሌ ድልድይ አካባቢ
👉 ከቦሌ ድልድይ እሰከ ሩዋንዳ ድልድይ
👉 ከቦሌ ድልድይ በወሎ ሰፈር ደንበል አደባባይ እስከ መስቀል አደባባይ
👉 ከመስቀል አደባባይ እስከ አራት ኪሎ
👉 ከኡራኤል አደባባይ እስከ አትላስ ሆቴል
👉 ከኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል እስከ ልማት ባንከ
👉 ከአራት ኪሎ እስከ አምባሳደር መናፈሻ
👉 ከብሄራዊ ቴአትር እስከ ሜክሲኮ አደባባይ
👉 ከሜክሲኮ አደባባይ እስከ አፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት እና
👉 ከአፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት እስከ ቡልጋሪያ ማዞሪያ ባሉት መንገዶች ላይ ተለዋጭ መረጃ እስኪተላለፍ ድረስ የኮንስትራክሽን ከባድ እና የጭነት ተሽከርካሪንዎችን ማሽከርከርም ሆነ ማቆም የተከለከለ መሆኑን በመገንዘብ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ አሳስቧል።
ይህንን ተላልፈው በተገኙት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ የትራፊክ ፍሠቱን የተሳለጠ ለማድረግ እንዲቻል ለኮንስትራክሽንና ለጭነት ተሽከርካሪዎች የተከለከሉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ቀደም ሲል በከተማው ላይ በደንብ ተላላፊ አሽከርካሪዎች የተከሰተውን ተመሣሣይ ጥፋት መነሻ አድርጎ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክት ማስተላለፋ ይታወሳል።
በመሆኑም የትራፊክ ህግና ደንብን በማስከበር የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋን ከመከላከል ባሻገር ጤናማ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር እንዲሁም በመዲናዋ በቀጣይ ቀናት ለሚካሔደው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔ የፀጥታ አካላት ለሚያከናውኑት የፀጥታ ስራ አመቺ ሁኔታን ለመፍጠር እንዲቻል ከዚህ በታች በተገለፁት መንገዶች፤
👉 ቦሌ ድልድይ አካባቢ
👉 ከቦሌ ድልድይ እሰከ ሩዋንዳ ድልድይ
👉 ከቦሌ ድልድይ በወሎ ሰፈር ደንበል አደባባይ እስከ መስቀል አደባባይ
👉 ከመስቀል አደባባይ እስከ አራት ኪሎ
👉 ከኡራኤል አደባባይ እስከ አትላስ ሆቴል
👉 ከኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል እስከ ልማት ባንከ
👉 ከአራት ኪሎ እስከ አምባሳደር መናፈሻ
👉 ከብሄራዊ ቴአትር እስከ ሜክሲኮ አደባባይ
👉 ከሜክሲኮ አደባባይ እስከ አፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት እና
👉 ከአፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት እስከ ቡልጋሪያ ማዞሪያ ባሉት መንገዶች ላይ ተለዋጭ መረጃ እስኪተላለፍ ድረስ የኮንስትራክሽን ከባድ እና የጭነት ተሽከርካሪንዎችን ማሽከርከርም ሆነ ማቆም የተከለከለ መሆኑን በመገንዘብ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ አሳስቧል።
ይህንን ተላልፈው በተገኙት ላይ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓም
ሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ከነገ የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ይሰጣል
*****
(ኢ ፕ ድ)
ሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ከነገ የካቲት 6 ጀምሮ እሰከ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በ84 የፈተና ማዕከላት
እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሰታወቀ።
የፈተና አሰጣጡን ፍትሃዊነትና ተአማኒነት ለማስጠበቅ ከዩኒቨርስቲዎች ታዛቢዎች መመደባቸው ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጅና(ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና በ2015 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ በሁሉም የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ተግባራዊ መደረጉን ጠቅሰው በመውጫ ፈተና ማስፈጸሚያ መመሪያ ቁጥር 919/2014 ድንጋጌ መሠረት ፈተናው በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡
የሁለተኛ ዙር ፈተናው በ47 የመንግስት ተቋማት በ84 የፈተና ማዕከላት ይሰጣል።
በመንግስትና ግል ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑትን ጨምሮ 149 ሺህ 145 ተፈታኞች በ204 የፈተና ፕሮግራሞች እንደሚፈተኑ ተናግረዋል።
የመውጫ ፈተና አሰጣጡ ፍትሃዊነትና ተአማኒነት ለማስጠበቅና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እንዲቻል በሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ታዛቢዎችን መመደባቸውን ገልጸዋል።
ታዛቢዎቹ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የተመለመሉ መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴርን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ከነገ የካቲት 6 ጀምሮ እሰከ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በ84 የፈተና ማዕከላት
እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሰታወቀ።
የፈተና አሰጣጡን ፍትሃዊነትና ተአማኒነት ለማስጠበቅ ከዩኒቨርስቲዎች ታዛቢዎች መመደባቸው ተገልጿል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት አካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጅና(ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና በ2015 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ በሁሉም የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ተግባራዊ መደረጉን ጠቅሰው በመውጫ ፈተና ማስፈጸሚያ መመሪያ ቁጥር 919/2014 ድንጋጌ መሠረት ፈተናው በዓመት ሁለት ጊዜ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡
የሁለተኛ ዙር ፈተናው በ47 የመንግስት ተቋማት በ84 የፈተና ማዕከላት ይሰጣል።
በመንግስትና ግል ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑትን ጨምሮ 149 ሺህ 145 ተፈታኞች በ204 የፈተና ፕሮግራሞች እንደሚፈተኑ ተናግረዋል።
የመውጫ ፈተና አሰጣጡ ፍትሃዊነትና ተአማኒነት ለማስጠበቅና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ እንዲቻል በሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ታዛቢዎችን መመደባቸውን ገልጸዋል።
ታዛቢዎቹ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የተመለመሉ መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴርን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም
በጅግጅጋ ከተማ ግንባታውን ያስጀመሩት የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከጥቂት ወራት በፊት በእህት ከተማችንና በምስራቋ ጮራ በጅግጅጋ ከተማ ግንባታውን ያስጀመሩት የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ተጠናቅቆ ለከተማዋ አቅመደካማ ነዋሪዎች አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስጠፋ መሃመድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ የሚገኘው ስራቸውን በማስፋፋት በጅግጅጋ ከተማ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል እንዲገነባ ስላደረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል::
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከጥቂት ወራት በፊት በእህት ከተማችንና በምስራቋ ጮራ በጅግጅጋ ከተማ ግንባታውን ያስጀመሩት የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ተጠናቅቆ ለከተማዋ አቅመደካማ ነዋሪዎች አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስጠፋ መሃመድ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እያደረገ የሚገኘው ስራቸውን በማስፋፋት በጅግጅጋ ከተማ የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል እንዲገነባ ስላደረጉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል::
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
ለአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ተሳታፊ እንግዶች የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
ለ37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 44ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ ያለ ምንም የኃይል መቆራረጥ እንዲጠናቀቅ ለማድረግ የኃይል መስመር የቅድመ ጥገኛ እና ማሻሻያ ስራዎች መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የተሰራው የኃይል መስመር የቅድመ ጥገኛ ስራ ለህብረቱ የስብሰባ አዳራሽ የኃይል አቅርቦት የሚሰጡ አዲስ ሴንተር 5፣ 11፣ 4፣ 15 እና 6 የሚባሉ የኃይል መስመሮች ላይ ያረፉ የዛፍ ቅርንጫፎችን የማስተካከል፣ ያረጁ ፖሎችን የመቀየር እና በጉዳት ምከንያት አገልግሎት አቁሞ የነበረ የመሬት ዉስጥ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርን የመጠገን እና ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ እንዲገባ የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡
ለአፍሪካ ህብረት እና አካባቢዉ የኃይል አቅርቦት ይሰጥ የነበረ ትራንስፎርመር በባለ 315 ኬቪኤ ትራንስፎርመር የመቀየር እና ተሸከርካሪ በቀላሉ በማያገኘዉ እና ለይታ አመቺ በሆነ መልኩ የማስቀመጥ ስራ ተከናዉኗል፡፡
በአፍሪካ ህብረት ዙሪያ እንዲሁም አካባቢው ላሉ ድርጅቶች እና ለመንገድ መብራት ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሰጠዉ ”አዲስ ሴንተር አስራ አንድ” የተባለ መስመር በተመሳሳይ የቅድመ ጥገና ስራዎች የተሰሩለት ሲሆን በመንገድ አካፋይ ዉስጥ ባሉ ዛፎች መካከል የሚሄደዉ መስመር ነፃ ወደሆነ ቦታ የማዛወር ስራ ተከናውኗል፡፡
በከተማዋ የህብረቱ ተሰብሳቢ እንግዶች መዳረሻ ለሆኑ ቦታዎች የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ሲሆን ከልማት ባንክ እስከ ካዛንቺስ መብራት እንዲሁም ሜክሲኮ አካባቢ በአዲስ መልክ ለሚሰራዉ የእግረኞች መንገድ ኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ ፖሎችን የማንሳት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
በተጨማሪም ለስብሰባዉ አገልግሎት የሚሰጡ አራት ግዙፍ ስክሪኖች ከኢትዮ ቴሌኮም በቀረበ ጥያቄ መሰረት ባለ 200 ኬቪኤ ትራንስፎርመሮችን የመትከል ስራ ተከናውኗል፡፡
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
ለ37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 44ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔ ያለ ምንም የኃይል መቆራረጥ እንዲጠናቀቅ ለማድረግ የኃይል መስመር የቅድመ ጥገኛ እና ማሻሻያ ስራዎች መከናወናቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡
የተሰራው የኃይል መስመር የቅድመ ጥገኛ ስራ ለህብረቱ የስብሰባ አዳራሽ የኃይል አቅርቦት የሚሰጡ አዲስ ሴንተር 5፣ 11፣ 4፣ 15 እና 6 የሚባሉ የኃይል መስመሮች ላይ ያረፉ የዛፍ ቅርንጫፎችን የማስተካከል፣ ያረጁ ፖሎችን የመቀየር እና በጉዳት ምከንያት አገልግሎት አቁሞ የነበረ የመሬት ዉስጥ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርን የመጠገን እና ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ እንዲገባ የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡
ለአፍሪካ ህብረት እና አካባቢዉ የኃይል አቅርቦት ይሰጥ የነበረ ትራንስፎርመር በባለ 315 ኬቪኤ ትራንስፎርመር የመቀየር እና ተሸከርካሪ በቀላሉ በማያገኘዉ እና ለይታ አመቺ በሆነ መልኩ የማስቀመጥ ስራ ተከናዉኗል፡፡
በአፍሪካ ህብረት ዙሪያ እንዲሁም አካባቢው ላሉ ድርጅቶች እና ለመንገድ መብራት ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚሰጠዉ ”አዲስ ሴንተር አስራ አንድ” የተባለ መስመር በተመሳሳይ የቅድመ ጥገና ስራዎች የተሰሩለት ሲሆን በመንገድ አካፋይ ዉስጥ ባሉ ዛፎች መካከል የሚሄደዉ መስመር ነፃ ወደሆነ ቦታ የማዛወር ስራ ተከናውኗል፡፡
በከተማዋ የህብረቱ ተሰብሳቢ እንግዶች መዳረሻ ለሆኑ ቦታዎች የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ሲሆን ከልማት ባንክ እስከ ካዛንቺስ መብራት እንዲሁም ሜክሲኮ አካባቢ በአዲስ መልክ ለሚሰራዉ የእግረኞች መንገድ ኤሌክትሪክ መስመር ተሸካሚ ፖሎችን የማንሳት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
በተጨማሪም ለስብሰባዉ አገልግሎት የሚሰጡ አራት ግዙፍ ስክሪኖች ከኢትዮ ቴሌኮም በቀረበ ጥያቄ መሰረት ባለ 200 ኬቪኤ ትራንስፎርመሮችን የመትከል ስራ ተከናውኗል፡፡
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
ከየካቲት 8 እስከ 11 ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ተከለከለ
********
(ኢ.ፕ.ድ)
በመዲናዋ ከየካቲት 8 ቀን ጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት 2 ሰዓት ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር መከልከሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።
ሞተር ብስክሌት የማሽከርከር ክልከላው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን የማያካትት መሆኑን የጠቆመው ቢሮውና የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ቢሮው አሳስቧል፡፡
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
********
(ኢ.ፕ.ድ)
በመዲናዋ ከየካቲት 8 ቀን ጠዋት 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም ጠዋት 2 ሰዓት ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር መከልከሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።
ሞተር ብስክሌት የማሽከርከር ክልከላው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን የማያካትት መሆኑን የጠቆመው ቢሮውና የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ቢሮው አሳስቧል፡፡
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት‼️
ዛሬ ጠዋት ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ፀሃፊ ሞሊ ፊ፣ እና የአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክል ሀመር ጋር በአህጉራዊ እና በባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት ለማድረግ ተገናኝተናል።
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
ዛሬ ጠዋት ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ፀሃፊ ሞሊ ፊ፣ እና የአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክል ሀመር ጋር በአህጉራዊ እና በባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት ለማድረግ ተገናኝተናል።
የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም
የባህር በር ስምምነቱ የቀጣናውን ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስር ማጠናከር የሚያስችል ነው
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የባህር በር ስምምነቱ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስርን በማጠናከር ዕድገታቸውን በፈጣን ሁኔታ ማሳደግ የሚያስችል ነው ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ሽመልስ ኃይሉ ገለጹ፡፡
መምህር ሽመልስ ኃይሉ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት በወደብ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ኢኮኖሚያዊ ትስስራቸውን ካጠናከሩ የተሻለ ዕድገት ማስመዝግብ ይችላሉ።
በቀጣናው ያለውን ሀብት ይበልጥ ለመጠቀም ሀገራቱ የተሻለ ትስስር መፍጠር ይገባቸዋል ያሉት መምህሩ፤ ከጦርነት ይልቅ በጋራ የመልማት ልምድን በማዳበት የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራትን የተሻለ መጥቀም የሚቻልበት ሰፊ አማራጭ መኖሩን ጠቁመዋል።
የባህር በር ለኢትዮጵያ ቅንጦት ሳይሆን የሀገርን ሉዓላዊነት፣ ኢኮኖሚ፣ ደህንነትና ወታደራዊ እንቅስቃሴን የሚወስን በመሆኑ ለነገ የሚተው ጉዳይ እንዳልሆነ አንስተዋል። ቀይ ባህርና የኤደን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120828
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
የባህር በር ስምምነቱ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስርን በማጠናከር ዕድገታቸውን በፈጣን ሁኔታ ማሳደግ የሚያስችል ነው ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ሽመልስ ኃይሉ ገለጹ፡፡
መምህር ሽመልስ ኃይሉ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት በወደብ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ኢኮኖሚያዊ ትስስራቸውን ካጠናከሩ የተሻለ ዕድገት ማስመዝግብ ይችላሉ።
በቀጣናው ያለውን ሀብት ይበልጥ ለመጠቀም ሀገራቱ የተሻለ ትስስር መፍጠር ይገባቸዋል ያሉት መምህሩ፤ ከጦርነት ይልቅ በጋራ የመልማት ልምድን በማዳበት የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራትን የተሻለ መጥቀም የሚቻልበት ሰፊ አማራጭ መኖሩን ጠቁመዋል።
የባህር በር ለኢትዮጵያ ቅንጦት ሳይሆን የሀገርን ሉዓላዊነት፣ ኢኮኖሚ፣ ደህንነትና ወታደራዊ እንቅስቃሴን የሚወስን በመሆኑ ለነገ የሚተው ጉዳይ እንዳልሆነ አንስተዋል። ቀይ ባህርና የኤደን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=120828
የአፍሪካ አባቶችን ይተዋወቁ‼️
ኢትዮጵያ “የሞኖሮቪያ” እና “የካዛብላንካ” ቡድን በሚል ተከፍለው የነበሩትን የአፍሪካ አገሮች አዲስ አበባ ላይ በማገናኘትና ልዩነቶችን በማለዘብ ወደ አንድ የጋራ አቋም እንዲመጡ አድርጋለች።
በዚሁ መሰረት ግንቦት 1955 ዓ.ም. 32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆንም ኢትዮጵያ በመሪዋ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የመሪነት ሚና ተጫውታለች።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱ አማረኛ ነበር።
ኢትዮጵያ “የሞኖሮቪያ” እና “የካዛብላንካ” ቡድን በሚል ተከፍለው የነበሩትን የአፍሪካ አገሮች አዲስ አበባ ላይ በማገናኘትና ልዩነቶችን በማለዘብ ወደ አንድ የጋራ አቋም እንዲመጡ አድርጋለች።
በዚሁ መሰረት ግንቦት 1955 ዓ.ም. 32 መስራች አገሮች የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን በይፋ አቋቁመዋል።
ለዚህ ድርጅት እውን መሆንም ኢትዮጵያ በመሪዋ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የመሪነት ሚና ተጫውታለች።
በወቅቱ ድርጅቱ ሲመሰረት የመመስረቻ ሰነዱ በአራት ቋንቋዎች ተጽፎ በ32 አገራት መሪዎች የተፈረመ ሲሆን፤ ከአራቱ ቋንቋ አንዱ አማረኛ ነበር።
44ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ተጀመረ
📌 አማርኛ የህብረቱ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ጥያቄ ቀርቧል
****
(ኢ.ፕ.ድ)
44ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
በስብስባው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳፋኪ መሃመት፣ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀ ስላሴ፣ የሕብረቱ አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ዲፕሎማቶች፣ የሕብረቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ ቀጣናዊ የአፍሪካ ተቋማት ኃላፊዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀ ስላሴ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለአፍሪካውያን ችግሮች አፍሪካዊ መፈትሔ በሚለው እሳቤ እየሰራበት ነው። በዚህም በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተውን ችግር ተከትሎ የተደረሰውን የፕሪቶሪያ
የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እያደረገ ነው ብለዋል።
እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ኮምሽን ተቋቋሞ የሚከሰቱ ችገሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ አማርኛ ቋንቋ የህብረቱ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ጥያቄ አቅርበዋል።
ምክር ቤቱ በስብሰባው በአፍሪካ የልማት አጀንዳዎች ላይ ስትራቴጂካዊ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ኢንዲሁም በንግድ፣ በትምህርት፣ በወጣቶችና ሴቶች፣ በግብርና፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በሰላምና ፀጥታ እንዲሁም በሌሎች የአህፍሪካን የ2063 አጀንዳ ዕውን ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች በጥልቀት ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
ስብሰባው ዛሬና ነገ የሚካሄድ ሲሆን 37ኛው የህብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ደግሞ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል።
በቃልኪዳን አሳዬ
📌 አማርኛ የህብረቱ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ጥያቄ ቀርቧል
****
(ኢ.ፕ.ድ)
44ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ ዛሬ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል።
በስብስባው ላይ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳፋኪ መሃመት፣ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀ ስላሴ፣ የሕብረቱ አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ዲፕሎማቶች፣ የሕብረቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ ቀጣናዊ የአፍሪካ ተቋማት ኃላፊዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀ ስላሴ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለአፍሪካውያን ችግሮች አፍሪካዊ መፈትሔ በሚለው እሳቤ እየሰራበት ነው። በዚህም በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተከሰተውን ችግር ተከትሎ የተደረሰውን የፕሪቶሪያ
የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እያደረገ ነው ብለዋል።
እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ኮምሽን ተቋቋሞ የሚከሰቱ ችገሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ አማርኛ ቋንቋ የህብረቱ የስራ ቋንቋ እንዲሆን ጥያቄ አቅርበዋል።
ምክር ቤቱ በስብሰባው በአፍሪካ የልማት አጀንዳዎች ላይ ስትራቴጂካዊ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ኢንዲሁም በንግድ፣ በትምህርት፣ በወጣቶችና ሴቶች፣ በግብርና፣ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በሰላምና ፀጥታ እንዲሁም በሌሎች የአህፍሪካን የ2063 አጀንዳ ዕውን ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች በጥልቀት ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
ስብሰባው ዛሬና ነገ የሚካሄድ ሲሆን 37ኛው የህብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ደግሞ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል።
በቃልኪዳን አሳዬ