በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሰላሳ ዓመታት የተከናወኑ አበይት ሥራዎችን የሚያሳይ አውደ ርዕይ ተከፈተ
**************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሰላሳ ዓመታት የተከናወኑ ሥራዎችን የሚያስቃኝ ዓውደ ርዕይ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኦሮሞ ባህል ማዕከል ተከፍቷል።
አውደርዕዩ "የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጉዞ" በሚል እስከ መጪው ዓርብ ድረስ እንደሚቆይ ተገልጿል።
በአውደ ርዕዩ በክልል ደረጃ የሚገኙ ሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የሽገር ከተማ አስተዳደር ተሳትፈዋል። አውደ ርዕዩ በክልሉ የኮሙኒኬሽን ቢሮ የተዘጋጀ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዓርብ ይቆያል።
በሳሙኤል ወንደሰን
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
**************
(ኢ ፕ ድ)
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሰላሳ ዓመታት የተከናወኑ ሥራዎችን የሚያስቃኝ ዓውደ ርዕይ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የኦሮሞ ባህል ማዕከል ተከፍቷል።
አውደርዕዩ "የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጉዞ" በሚል እስከ መጪው ዓርብ ድረስ እንደሚቆይ ተገልጿል።
በአውደ ርዕዩ በክልል ደረጃ የሚገኙ ሁሉም ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የሽገር ከተማ አስተዳደር ተሳትፈዋል። አውደ ርዕዩ በክልሉ የኮሙኒኬሽን ቢሮ የተዘጋጀ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዓርብ ይቆያል።
በሳሙኤል ወንደሰን
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጂንካ ኤርፖርት ያስገነባውን ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ አሰመረቀ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጂንካ ኤርፖርት ያስገነባውን ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል እያስመረቀ ይገኛል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው መንግስቴ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባውዲና የአሪ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አብርሃም አታን ጨምሮ ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
እንዲሁም የአሪ ዞን የአገር ሽማግሌዎች፣ የማህበረሰብ ተወካዮች እና የሀይማኖት አባቶችም በስነ-ስርዓቱ ላይ ታድመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በጂንካ ኤርፖርት ያስገነባውን ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል እያስመረቀ ይገኛል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌታቸው መንግስቴ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ ባውዲና የአሪ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አብርሃም አታን ጨምሮ ሌሎችም የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
እንዲሁም የአሪ ዞን የአገር ሽማግሌዎች፣ የማህበረሰብ ተወካዮች እና የሀይማኖት አባቶችም በስነ-ስርዓቱ ላይ ታድመዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
ምክር ቤቱ እንደ ዓባይ ሁሉ ለሀገራዊ አጀንዳዎች ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ
***************
(ኢ ፕ ድ)
እንደ ዓባይ ፕሮጀክት ሁሉ ለትላልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።
የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ደስታ ዲንቃ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዓባይ ግድብ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የተሳተፉበት የጋራ ፕሮጀክት ነው። ግድቡ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ ብዙ ችግሮችን ሊቀርፍ የሚችል በመሆኑ እስከዛሬ ድረስ ሁሉም ዜጎች በመረባረብ አሻራቸውን እያሳረፉበት ይገኛሉ ብለዋል።
የጋራ ምክር ቤቱም ከግድቡ ግንባታ ጀምሮ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ እንደ ዓባይ ያሉ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ሥራዎች ላይ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።
ግድቡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚታይ የልማት ጉዳይ በመሆኑ፤ ከፖለቲካ ውጪ በሆነ እይታ ውስጥ ያለና የሀገር ሀብት ነው ብለዋል።
የጋራ ምክር ቤቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የግድቡን ግንባታ እየደገፈ ያለውም የጋራ ሀብታችን መሆኑን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=124946
***************
(ኢ ፕ ድ)
እንደ ዓባይ ፕሮጀክት ሁሉ ለትላልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።
የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ደስታ ዲንቃ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዓባይ ግድብ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የተሳተፉበት የጋራ ፕሮጀክት ነው። ግድቡ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ ብዙ ችግሮችን ሊቀርፍ የሚችል በመሆኑ እስከዛሬ ድረስ ሁሉም ዜጎች በመረባረብ አሻራቸውን እያሳረፉበት ይገኛሉ ብለዋል።
የጋራ ምክር ቤቱም ከግድቡ ግንባታ ጀምሮ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው፤ እንደ ዓባይ ያሉ ዘመን ተሻጋሪ የልማት ሥራዎች ላይ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።
ግድቡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚታይ የልማት ጉዳይ በመሆኑ፤ ከፖለቲካ ውጪ በሆነ እይታ ውስጥ ያለና የሀገር ሀብት ነው ብለዋል።
የጋራ ምክር ቤቱ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ የግድቡን ግንባታ እየደገፈ ያለውም የጋራ ሀብታችን መሆኑን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=124946
#የሚኒስትሮች_ምክር_ቤት ውሳኔዎች ‼️
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 28ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
👉 በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የመካከለኛ ዘመን 2017-2021 የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊሲካል ማዕቀፍ ላይ ነው፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚና ፊሲካል ማዕቀፉ የመንግስት በጀት ከማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታው እና የፊሲካል አቅም ጋር ተጣጥሞ እንዲዘጋጅ ለማድረግ፤ ከመንግስት ገቢ አሰባሰብ እና ሀብት አመዳደብ አኳያ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በማመላከት ለቀጣይ በጀት አመት የበጀት ዝግጅት ለማድረግ፤ የመካከለኛ ዘመን የመንግስት ገቢና ወጪ እንዲሁም የፊሲካል ሚዛን የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመለየት እና ለማመላከት የሚያገለግል ማዕቀፍ በመሆኑ ምክር ቤቱ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
👉በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የተጨማሪ እሴት ታክስ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የተጨማሪ እሴት ታክስ ስራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ በሀገሪቱ የእኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የተደረጉ ለውጦችን በህግ ማእቀፉ ውስጥ ማስገባት በማስፈለጉ፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የተጨማሪ እሴት ታክስ ጫና እንዳያርፍባቸው ለማድረግ የሚያስችል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብዓቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 28ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
👉 በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የመካከለኛ ዘመን 2017-2021 የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊሲካል ማዕቀፍ ላይ ነው፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚና ፊሲካል ማዕቀፉ የመንግስት በጀት ከማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታው እና የፊሲካል አቅም ጋር ተጣጥሞ እንዲዘጋጅ ለማድረግ፤ ከመንግስት ገቢ አሰባሰብ እና ሀብት አመዳደብ አኳያ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በማመላከት ለቀጣይ በጀት አመት የበጀት ዝግጅት ለማድረግ፤ የመካከለኛ ዘመን የመንግስት ገቢና ወጪ እንዲሁም የፊሲካል ሚዛን የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመለየት እና ለማመላከት የሚያገለግል ማዕቀፍ በመሆኑ ምክር ቤቱ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
👉በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የተጨማሪ እሴት ታክስ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የተጨማሪ እሴት ታክስ ስራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ በሀገሪቱ የእኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የተደረጉ ለውጦችን በህግ ማእቀፉ ውስጥ ማስገባት በማስፈለጉ፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የተጨማሪ እሴት ታክስ ጫና እንዳያርፍባቸው ለማድረግ የሚያስችል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብዓቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️
ዛሬ የረመዳን ወር ጾምን ምክንያት በማድረግ ከ127 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ የከተማችን ነዋሪዎች ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር አስጀምረናል።
በለውጡ መንግስት በጀመርነው የሰው ተኮር ስራችን የህዝባችንን የኑሮ ጫና የማቅለልና አለኝታነታችንን በተግባር የማረጋገጥ በርካታ ስራ በመስራት፣ ማዕድ ብቻ ሳይሆን ለወገኖቻችን ክብር እና ፍቅርን እያጋራን የቆየን ሲሆን በዛሬው ዕለትም ለሁሉም የአዲስ አበባ መስጅዶች የሚከፋፈል ቴምር እና ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወገኖቻችን ደግሞ ማዕድ አጋርተናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
ዛሬ የረመዳን ወር ጾምን ምክንያት በማድረግ ከ127 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ የከተማችን ነዋሪዎች ማዕድ የማጋራት መርሃ ግብር አስጀምረናል።
በለውጡ መንግስት በጀመርነው የሰው ተኮር ስራችን የህዝባችንን የኑሮ ጫና የማቅለልና አለኝታነታችንን በተግባር የማረጋገጥ በርካታ ስራ በመስራት፣ ማዕድ ብቻ ሳይሆን ለወገኖቻችን ክብር እና ፍቅርን እያጋራን የቆየን ሲሆን በዛሬው ዕለትም ለሁሉም የአዲስ አበባ መስጅዶች የሚከፋፈል ቴምር እና ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወገኖቻችን ደግሞ ማዕድ አጋርተናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአፈፃፀም ተጠያቂነት ስርዓት ሊተገበር ነው- ትምህርት ሚኒስቴር
*****
(ኢ ፕ ድ)
ከቀጣይ አመት ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራትን ለማምጣት የሚያግዝ የአፈፃፀም ተጠያቂነት ስርዓት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ሰለሞን አብርሃ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥርን ለማሳደግ ሲሰራ ቢቆይም የትምህርት ጥራት ላይ ብዙ ይቀር እንደነበር አስታውሰዋል።
የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ባሰፈረው ምክረሃሳብ፤ የትምህርት ጥራትና አግባብነት ላይ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ሲከናወን መቆየቱን ተናግረዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውጤታማ አለመሆን ከዚህ ቀደም ከሚታዩ ችግሮች መካከል መሆናቸውን አንስተው፤ ተቋማቱን ብቁና ውጤታማ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ የማድረግ ሂደት መጀመሩን ጠቅሰዋል።
የስርዓተ ትምህርት፣ የትምህርት ምዘና ማሻሻያ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎችን በትኩረትና በተልዕኮ መስክ የመለየት ስራ ከማሻሻያው መካከል የሚገኙ እንደሆኑም ገልፀዋል።
ከዚህ ቀደም ተቋማት በፋይናንስ አጠቃቀማቸው እንጂ በአፈፃፀም ተጠያቂ የሚሆኑበት ስርዓት እንዳልነበር አንስተው ከሚቀጥለው አመት ጀምሮ ተቋማት በአፈፃፀማቸው ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር መተግበር ይጀመራል ብለዋል።
በተጠያቂነት የአሰራር ስርዓት መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቁልፍ ውጤት አመላካቾች ላይ ውል በማድረግ ስራቸውን እንደሚያከናውኑ ገልፀዋል።
ይህም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ያለውን ስራ የሚያግዝ መሆኑን ነው የተናገሩት።
የአፈፃፀም ተጠያቂነት ስርዓቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ተመዝነው የተሻለ አፈጻጻም ያስመዘገቡት እውቅና እንዲያገኙ እንዲሁም ዝቅተኛ አፈፃፀም ያላቸው ደግሞ የማስተካከያ እርምጃዎች የሚወስዱበት አግባብ የሚፈጠርበት መሆኑንም ነው ያስረዱት።
ሚኒስቴሩ በቀጣይም የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ለማረጋገጥ በዘርፉ ያለውን ስብራት ማከም የሚችሉ የተለያዩ አሰራሮችን በጥናት እየለየ እንደሚተገብርም ተናግረዋል።
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ከቀጣይ አመት ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራትን ለማምጣት የሚያግዝ የአፈፃፀም ተጠያቂነት ስርዓት ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ሰለሞን አብርሃ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከዚህ ቀደም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥርን ለማሳደግ ሲሰራ ቢቆይም የትምህርት ጥራት ላይ ብዙ ይቀር እንደነበር አስታውሰዋል።
የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ባሰፈረው ምክረሃሳብ፤ የትምህርት ጥራትና አግባብነት ላይ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ሲከናወን መቆየቱን ተናግረዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውጤታማ አለመሆን ከዚህ ቀደም ከሚታዩ ችግሮች መካከል መሆናቸውን አንስተው፤ ተቋማቱን ብቁና ውጤታማ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ የማድረግ ሂደት መጀመሩን ጠቅሰዋል።
የስርዓተ ትምህርት፣ የትምህርት ምዘና ማሻሻያ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎችን በትኩረትና በተልዕኮ መስክ የመለየት ስራ ከማሻሻያው መካከል የሚገኙ እንደሆኑም ገልፀዋል።
ከዚህ ቀደም ተቋማት በፋይናንስ አጠቃቀማቸው እንጂ በአፈፃፀም ተጠያቂ የሚሆኑበት ስርዓት እንዳልነበር አንስተው ከሚቀጥለው አመት ጀምሮ ተቋማት በአፈፃፀማቸው ተጠያቂ የሚሆኑበትን አሰራር መተግበር ይጀመራል ብለዋል።
በተጠያቂነት የአሰራር ስርዓት መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቁልፍ ውጤት አመላካቾች ላይ ውል በማድረግ ስራቸውን እንደሚያከናውኑ ገልፀዋል።
ይህም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትና አግባብነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ያለውን ስራ የሚያግዝ መሆኑን ነው የተናገሩት።
የአፈፃፀም ተጠያቂነት ስርዓቱ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ተመዝነው የተሻለ አፈጻጻም ያስመዘገቡት እውቅና እንዲያገኙ እንዲሁም ዝቅተኛ አፈፃፀም ያላቸው ደግሞ የማስተካከያ እርምጃዎች የሚወስዱበት አግባብ የሚፈጠርበት መሆኑንም ነው ያስረዱት።
ሚኒስቴሩ በቀጣይም የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ለማረጋገጥ በዘርፉ ያለውን ስብራት ማከም የሚችሉ የተለያዩ አሰራሮችን በጥናት እየለየ እንደሚተገብርም ተናግረዋል።
መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም
👍1
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በሶስት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል
*****
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው በሶስት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።
ለከተማዋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅም ጉልህ ሚና ባላቸው ጉዳዮች ላይ በዛሬው ዕለት ተወያይቶ አጽድቋል።
በዚህም መሰረት፤
1ኛ. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን የተሽከርካሪ አስተዳደር ህግ እና ሥርዓት ለማስከበር የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው የተሽከርካሪ ማቆሚያ አገልግሎት አሰጣጥ ረቂቅ ደንብን ለአሰራር በሚያመች መልኩ ሀሳብ ተሰጥቶበት ፀድቋል።
2ኛ. የከተማዋን ስታንዳርድና መዋቅራዊ ፕላን ለማስጠበቅ እንዲሁም መልሶ ማፍረስ እንዳይገጥም፤ ግንባታዎች ከመንገድ ያላቸው ርቀት ከዚህ በኋላ ወጥነት ያለው የከተማ አሰራር አንዲኖር በማሰብ ከመንገድ መራቅ ያለባቸውን 3 ደረጃዎች ለማውጣት በቀረበው መተዳደሪያ ደንብ ላይ በመወያየት ከአሁን በኋላ የሚገነቡ ማንኛውም ግንባታዎች ከዋና ከመንገድ በ10 ሜትር ርቀት መሆን እንደሚገባው ፤ ከንዑስ ዋና መንገድ 5 ሜትር ርቀት፤ ሰብሳቢ መንገድ ደግሞ 3 ሜትር ርቀት በተጨማሪም የውስጥ ለውስጥ መንገድ 2 ሜትር ርቀት መጠበቅ እንዳለባቸው ካቢኔው ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።
3ኛ. የነገዋ የሴቶች ተሀድሶ እና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ማቋቋሚያ ደንብ ማዕከሉን በተለይም ለጎዳና ህይወት ፤ ለፆታዊ ጥቃት ለተጋለጡ እና ለወሲብ ንግድ ተጋላጭ ለሆኑ ሴቶች ፣ መጠለያ፣ ማገገሚያና የተመሰቃቀለ ህይወታቸውን እንደገና ለማደስ የሚያስችል የሙያ እና ክህሎት ሥልጠናዎች የሚያገኙበትንና በዘላቂነት እንዲቋቋሙ የሚያግዝ አቅም ያለዉ ማዕከል እንዲሆን ለማስቻል በሚያግዘው ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ካቢኔው ተወያይቶ አጽድቋል።
*****
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው በሶስት ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።
ለከተማዋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅም ጉልህ ሚና ባላቸው ጉዳዮች ላይ በዛሬው ዕለት ተወያይቶ አጽድቋል።
በዚህም መሰረት፤
1ኛ. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን የተሽከርካሪ አስተዳደር ህግ እና ሥርዓት ለማስከበር የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው የተሽከርካሪ ማቆሚያ አገልግሎት አሰጣጥ ረቂቅ ደንብን ለአሰራር በሚያመች መልኩ ሀሳብ ተሰጥቶበት ፀድቋል።
2ኛ. የከተማዋን ስታንዳርድና መዋቅራዊ ፕላን ለማስጠበቅ እንዲሁም መልሶ ማፍረስ እንዳይገጥም፤ ግንባታዎች ከመንገድ ያላቸው ርቀት ከዚህ በኋላ ወጥነት ያለው የከተማ አሰራር አንዲኖር በማሰብ ከመንገድ መራቅ ያለባቸውን 3 ደረጃዎች ለማውጣት በቀረበው መተዳደሪያ ደንብ ላይ በመወያየት ከአሁን በኋላ የሚገነቡ ማንኛውም ግንባታዎች ከዋና ከመንገድ በ10 ሜትር ርቀት መሆን እንደሚገባው ፤ ከንዑስ ዋና መንገድ 5 ሜትር ርቀት፤ ሰብሳቢ መንገድ ደግሞ 3 ሜትር ርቀት በተጨማሪም የውስጥ ለውስጥ መንገድ 2 ሜትር ርቀት መጠበቅ እንዳለባቸው ካቢኔው ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።
3ኛ. የነገዋ የሴቶች ተሀድሶ እና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ማቋቋሚያ ደንብ ማዕከሉን በተለይም ለጎዳና ህይወት ፤ ለፆታዊ ጥቃት ለተጋለጡ እና ለወሲብ ንግድ ተጋላጭ ለሆኑ ሴቶች ፣ መጠለያ፣ ማገገሚያና የተመሰቃቀለ ህይወታቸውን እንደገና ለማደስ የሚያስችል የሙያ እና ክህሎት ሥልጠናዎች የሚያገኙበትንና በዘላቂነት እንዲቋቋሙ የሚያግዝ አቅም ያለዉ ማዕከል እንዲሆን ለማስቻል በሚያግዘው ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ካቢኔው ተወያይቶ አጽድቋል።