Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.75K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ሥራ ፈላጊ ነዎት⁉️
መልካም ዕድል 🙏
በነገው ዕለት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ለሚካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ለአሽከርካሪዎች ዝግ የሚሆኑ መንገዶች

👉 ከቴዎድሮስ አደባባይ በብሄራዊ ቴአትር ወደ ወደ መስቀል አደባባይ ሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ

👉 ከኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ ላይ

👉 ከቦሌ አቅጣጫ  ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ኦሎምፒያ አደባባይ

👉 ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

👉 ከጎተራ ማሳለጫ ወደ መስቀል አደባባይ አጎና  ሲኒማ

👉 ከቅ/ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን በአዲሱ መንገድ  ወደ መስቀል አደባባይ ለሚሄዱ ለገሀር መብራት

👉 ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ቴሌ ለሚጓዙ ለገሀር መብራት

👉 ከጌጃ ሰፈር አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ሰንጋተራ ትራፊክ መብራት

👉 ከሃራምቤ  መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ  መብራት ላይ

👉 ከብሔራዊ ቤተ መንግስት  ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ  ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ

👉 ከካዛንቺስ ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ

👉 ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡

ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በ011-1-26-43-59 ፣ 011-5-52-63-02፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81፤ በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ ጥሪ ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ግብረ ኃይሉ ጥሪውን አስተላልፏል።

መጋቢት 27 ቀን 2016 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ባለፉት 6 ዓመታት የከተማዋን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸው ተገለጸ
*****
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ባለፉት 6 ዓመታት የከተማዋን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ሥራዎች መከናወናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ዣንጥራር አባይ ገለጹ።

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ዓመታት የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል ያለመ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

በወቅቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ዣንጥራር አባይ እንደተናገሩ፤ ለውጡ ለአዲስ አበባ አዲስነት ብዙ ገጸ በረከቶችን አምጥቷል።

በተለይም በከተማዋ የተከናወነው የቤት ልማት የሀገር ባለውለታዎችና አቅመ ደካሞችን፣ የልማት ተነሺዎችን እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል አቶ ዣንጥራር ።

ከተማዋ ለረጅም ዓመታት የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ማዕከልነቷን የማይመጥኑ መሰረተ ልማቶች የነበሩባት ከተማ ነበረች ብለዋል።

የለውጡ መንግስት ለሰው ልጅ ከምግብ ባለፈ ራሱን የሚያዳምጥበት አረንጓዴ ቦታዎችና ፓርኮች ገንብቷል ያሉት አቶ ዣንጥራር፤ የኑሮ ውድነትን በማሻሻል በኩል የእሁድ ገበያን ጨምሮ ትላልቅ የገበያ ማዕከላት ተገንብተዋል። እነዚህም ዝቅተኛ ገቢ ያለቸውን የከተማዋን ነዋሪዎች መሰረት ያደረጉ ማቸው ብለዋል።

የትምህርት ቤት ምገባ፣ የሌማት ትሩፋት ሥራዎች እና የዳቦ ምርት መጠንን ከመጨመር አኳያ በርካታ ሥራዎች መሰራታቸውን የገለጹት አቶ ዣንጥራር፤ በቀጣይ በከተማዋ የሚስተዋሉ የልማትና መሰል ችግሮችን ለመፍታት የለውጡ መንግስት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በሳሙኤል ወንደሰን

መጋቢት 28 ቀን 2016 ዓ.ም
ሥራ ፈላጊ ነዎት⁉️
መልካም ዕድል 🙏
እንደሀገር ለስታርት አፕ’ ዘርፉ ዕድገት መሠረት የሚጥሉ ማሻሻያዎች ተደርገዋል” – ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር
*****
(ኢ ፕ ድ)

እንደሀገር ለ‘ስታርት አፕ’ ዘርፉ ዕድገት መሠረት የሚጥሉ የተለያዩ የሕግና የፋይናንስ አሠራር ማሻሻያዎች መደረጋቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል አስታወቁ።

የ’ስታርት አፕ’ ኢትዮጵያ ዓውደ ጥናት ትናንትና በሳይንስ ሙዚየም በተዘጋጀበት ወቅት ሚኒስትሯ ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት፤ ቴክኖሎጂን ማዕከል አድርገው በሚከናወኑ ችግር ፈቺ የፈጠራ ሥራዎችን ለማበረታታት የሚረዱ የተለያዩ ማዕቀፎች ላይ ማሻሻያ ተደርጓል።

ከተደረጉ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች ሃሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት ያለምንም የንግድ ቤት ኪራይ ውል ሥራ መጀመር የሚችሉበትን አዲስ አሠራር መዘርጋቱ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ ሀገር ፈንድ ያገኘ ስታርት አፕ ሙሉ በሙሉ የውጭ ምንዛሪውን ለሚፈልገው ሥራ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=125133
ሰሞኑን ያጋጠመው የነዳጅ እጥረት ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል
👉 በቀን ሦስት ሚሊዮን ሊትር የሚጠጋ ነዳጅ ወደ ሀገር እየገባ ነው
**
(ኢ ፕ ድ)
በቅርቡ አጋጥሞ የነበረው የነዳጅ እጥረት በአሁኑ ጊዜ ሙሉ በሙሉ መቅረፍ ተችሏል ሲል የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት አስታወቀ፡፡ በቀን ሦስት ሚሊዮን ሊትር የሚጠጋ ነዳጅ ወደ ሀገር እየገባ መሆኑም ተገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከፍተኛ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ዓለማየሁ ፀጋዬ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የነዳጅ እጥረቱ አጋጥሞ የነበረው በጅቡቲ ጥሎ በነበረው ከባድ ዝናብ ምክንያት መንገዶች በመዘጋጋታቸው ነው፡፡ በዚህ ሳቢያም ነዳጅ የሚጭኑ ከባድ ቦቴዎች ወደ ሀገር መግባትም ሆነ መውጣት አልቻሉም ፡፡

መንገዱ ከዚህ ቀደምም ችግር የነበረበት ነው ያሉት ባለሙያው፤ ከሹፌሮችም በተደጋጋሚ ስሞታ የሚቀርብበት ነው ሲሉ ተናግረዋል ፡፡

አቶ ዓለማየሁ፤ ድርጅቱ ያጋጠመውን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ ነዳጅ የጫኑ ተሽከርካሪዎች በድሬዳዋ በኩል እንዲገቡ መደረጉን ገልጸው፤ በዚህም አጋጥሞ የነበረውን ችግር ሙሉ በሙሉ መቅረፍ መቻሉን አንስተዋል፡፡

ችግሩ ከማጋጠሙ በፊት በቀን በአማካኝ ከ250 እስከ 300 የሚሆኑ ነዳጅ የሚጭኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=125144
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሩዋንዳ ኪጋሊ ገብተዋል።

መጋቢት 28 ቀን 2016 ዓም