ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሲንጋፖር በብሔራዊው የእፅዋት ማዕከል ባህላዊውን እፅዋት የመሰየም ሥነሥርዓት ተካፍለዋል፤ 'አራንዳ ዐቢይ አሕመድ ዝናሽ ታያቸው' የተሰኘ የኦርኪድ አበባ በስማቸው ተሰይሞላቸዋል። ይህንን ስነስርዓት በፎት‼️
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ-ጉባኤ ተጠናቀቀ
**
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ-ጉባኤ ተጠናቀቀ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የምልዓተ - ጉባኤውን መጠናቀቅ በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልዕክቶች ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉና ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸው እንዲሁም በጥብቅ የሚያወግዛቸው መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተክርስቲያንና ለሀገራችን ህዝቦች ጠቃሚ ውሳኔ አሳልፏል ብለዋል በመግለጫቸው፡፡
በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተመሥርቶ አባታዊ ምክርና ተግሣጽ ማስተላለፍ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑን አንስተው ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልዕክቶች ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉና ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸው እንዲሁም በጥብቅ የሚያወግዛቸው ናቸው ብለዋል፡፡
ወደ ፊት እንዲህ ዓይነት ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም ወጥ የሆነ የመግለጫ አሰጣጥና የትምህርተ ወንጌል ተልእኮ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምልዐተ ጉበኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑንም ጠቁመዋል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ ላይ በሰፊው ተወያይቶ ሊሻሻሉ የሚገባቸው ሀሳቦችን ለሚመለከተው የመንግስት ተቋም መላኩን ገልጸዋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊትም የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦች በአዋጁ ስለመካተታቸው ክትትል የሚያደርግ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟልም ነው ያሉት በመግለጫቸው፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡
ለአፈጻጸም እንዲያመችም የተዘጋጀው መዋቅራዊ አደረጃጀት በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዓዋዲው ተካቶ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑን ጠቁመዋል፡፡
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት ተዘጋጅቶ የቀረበው የ2017 ዓ.ም ዓመታዊ በጀት ጸድቆ ሥራ ላይ እንዲውልም ቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑን አስታውቀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
**
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ-ጉባኤ ተጠናቀቀ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የምልዓተ - ጉባኤውን መጠናቀቅ በማስመልከት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልዕክቶች ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉና ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸው እንዲሁም በጥብቅ የሚያወግዛቸው መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተክርስቲያንና ለሀገራችን ህዝቦች ጠቃሚ ውሳኔ አሳልፏል ብለዋል በመግለጫቸው፡፡
በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ ተመሥርቶ አባታዊ ምክርና ተግሣጽ ማስተላለፍ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያለው መሆኑን አንስተው ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልዕክቶች ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉና ቅዱስ ሲኖዶስ የማይቀበላቸው እንዲሁም በጥብቅ የሚያወግዛቸው ናቸው ብለዋል፡፡
ወደ ፊት እንዲህ ዓይነት ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጸም ወጥ የሆነ የመግለጫ አሰጣጥና የትምህርተ ወንጌል ተልእኮ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ ለምልዐተ ጉበኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑንም ጠቁመዋል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ ላይ በሰፊው ተወያይቶ ሊሻሻሉ የሚገባቸው ሀሳቦችን ለሚመለከተው የመንግስት ተቋም መላኩን ገልጸዋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ከመጽደቁ በፊትም የተሰጡ የማሻሻያ ሐሳቦች በአዋጁ ስለመካተታቸው ክትትል የሚያደርግ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟልም ነው ያሉት በመግለጫቸው፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ዘመኑን የዋጀ እንዲሆን የዐሥር ዓመት መሪ ዕቅድ በማጽደቅ ወደ ትግበራ እንዲገባ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡
ለአፈጻጸም እንዲያመችም የተዘጋጀው መዋቅራዊ አደረጃጀት በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዓዋዲው ተካቶ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑን ጠቁመዋል፡፡
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት ተዘጋጅቶ የቀረበው የ2017 ዓ.ም ዓመታዊ በጀት ጸድቆ ሥራ ላይ እንዲውልም ቅዱስ ሲኖዶስ መወሰኑን አስታውቀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከእስያ ጉብኝታቸው ማምሻውን በመመለስ የሶስት ቀናት የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን ካጠናቀቁት የሳዑዲ አረቢያ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ተወካዮች ልዑክ ጋር ውይይት አድርገዋል።
ውይይቱ በቤቶች ልማት፣ በቱሪዝምና በግብርና በተለይም በሀገር ውስጥ የማዳበሪያ ምርት ላይ ያተኮረ ነበር።
ሰባ ዘጠኝ ኢንቨስተሮችን ያካተተው ከፍተኛ ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሳዑዲ አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሰልማን በህዳር ወር በሳዑዲ - አፍሪካ ጉባኤ ወቅት ያደረጉትን የሁለትዮሽ ውይይት ተከትሎ መከናወኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
ውይይቱ በቤቶች ልማት፣ በቱሪዝምና በግብርና በተለይም በሀገር ውስጥ የማዳበሪያ ምርት ላይ ያተኮረ ነበር።
ሰባ ዘጠኝ ኢንቨስተሮችን ያካተተው ከፍተኛ ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሳዑዲ አልጋ ወራሽ መሃመድ ቢን ሰልማን በህዳር ወር በሳዑዲ - አፍሪካ ጉባኤ ወቅት ያደረጉትን የሁለትዮሽ ውይይት ተከትሎ መከናወኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
ለደቡብ ሱዳን ዲፕሎማቶች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ
***
(ኢ ፕ ድ)
የደቡብ ሱዳን ዲፕሎማቶች በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትብብር የተዘጋጀላቸውን የሶስት ቀናት ስልጠና መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ አጠናቀዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በስልጠናው ማጠናቀቂያ ስነ-ስርዓት ላይ ስልጠናው ዲፕሎማቶቹ በቀጣይ በስራቸው የሚያጋጥሟቸውን ውስብስብ ፈተናዎች ለመገንዘብና ለመፍታት ጠቃሚ ክህሎት እንዲኖራቸው ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀ እንደሆነም ገልጸዋል።
መሰል ስልጠናዎች በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መካከል ያለውን የቆየ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል።
በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ አምባሳደር ናታሊና ኤድዋርድ ሙዩ በበኩላቸዉ ስልጠናውን ላዘጋጁት የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን አመስግነዋል።
ዲፕሎማቶቹ ስልጠናውን በተሳካ ሁኔታ በማጠናቀቃቸው የምስክር ወረቀት እንደተበረከተላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
***
(ኢ ፕ ድ)
የደቡብ ሱዳን ዲፕሎማቶች በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትብብር የተዘጋጀላቸውን የሶስት ቀናት ስልጠና መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ አጠናቀዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በስልጠናው ማጠናቀቂያ ስነ-ስርዓት ላይ ስልጠናው ዲፕሎማቶቹ በቀጣይ በስራቸው የሚያጋጥሟቸውን ውስብስብ ፈተናዎች ለመገንዘብና ለመፍታት ጠቃሚ ክህሎት እንዲኖራቸው ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀ እንደሆነም ገልጸዋል።
መሰል ስልጠናዎች በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መካከል ያለውን የቆየ የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል።
በኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ አምባሳደር ናታሊና ኤድዋርድ ሙዩ በበኩላቸዉ ስልጠናውን ላዘጋጁት የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን አመስግነዋል።
ዲፕሎማቶቹ ስልጠናውን በተሳካ ሁኔታ በማጠናቀቃቸው የምስክር ወረቀት እንደተበረከተላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓም
"ሕንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት የሁለትዮሽና ግንኙነት ያድጋል" - ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ
******
(ኢ ፕ ድ)
በአዲሱ የስልጣን ዘመኔ ሕንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት የሁለትዮሽና ግንኙነትና አጋርነት ያድጋል ሲሉ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ገለጹ፡፡
በሕንድ በተካሄደው ምርጫ ናሬንድራ ሞዲ ለሦስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ይታወሳል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወቃል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ላስተላለፉላቸው መልዕክት ምሰጋና አቅርበዋል።
ሕንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ግንኙነት ከፍተኛ ትኩረት ትሰጣለችም ብለዋል።
ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
በአዲሱ የስልጣን ዘመኔ ሕንድ ከኢትዮጵያ ጋር ያላት የሁለትዮሽና ግንኙነትና አጋርነት ያድጋል ሲሉ የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ገለጹ፡፡
በሕንድ በተካሄደው ምርጫ ናሬንድራ ሞዲ ለሦስተኛ ጊዜ ማሸነፋቸውን ይታወሳል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወቃል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ላስተላለፉላቸው መልዕክት ምሰጋና አቅርበዋል።
ሕንድ ከኢትዮጵያ ጋር ላላት የሁለትዮሽ ግንኙነት ከፍተኛ ትኩረት ትሰጣለችም ብለዋል።
ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓም
#ጽዱኢትዮጵያ #CleanEthiopia
በሰሜን አሜሪካ የአትሌቶች ማህበር አባላት 8 ሺህ300 የአሜሪካን ዶላር ለ“ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” ድጋፍ አደረጉ
👉 እስከ አሁን 29 ሺህ 445 የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም 74 ሺህ የኢትዮጵያ ብር ተሰብስቧል፣
****
(ኢ ፕ ድ)
ለ“ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” በሰሜን አሜሪካ የአትሌቶች ማህበር አባላት 8 ሺህ300 የአሜሪካን ዶላር የገንዘብና አንድ መጸዳጃ ቤት ለመስራት የአይነት ድጋፍ አደረጉ።
ድጋፋቸውን በአሜሪካ የኢትየጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ስለሺ በቀለ አስረክበዋል።
የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አትሌት ሀይሉ መኮንን ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው ወቅት ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የማህበሩ አባላት በተለያዩ አገራዊ ጥሪዎች ላይ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አምባሳደር ስለሺ በቀለ
ጠቅሰው አሁንም ማህበሩ ለ”ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” ኢንሼቲቭ ላደረገው ድጋፍ ያላቸውን ምስጋና አቅርበዋል።
በአሜሪካ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን ለ”ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” እስከ አሁን በአጠቃላይ በጥሬ ገንዘብ 29 ሺህ 445 የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም 74 ሺህ የኢትዮጵያ ብር ተሰብስቧል።
በዓይነት 21 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ 14 መጸዳጃ ቤቶችን ለመስራት ቃል መግባታቸውን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓም
በሰሜን አሜሪካ የአትሌቶች ማህበር አባላት 8 ሺህ300 የአሜሪካን ዶላር ለ“ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” ድጋፍ አደረጉ
👉 እስከ አሁን 29 ሺህ 445 የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም 74 ሺህ የኢትዮጵያ ብር ተሰብስቧል፣
****
(ኢ ፕ ድ)
ለ“ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” በሰሜን አሜሪካ የአትሌቶች ማህበር አባላት 8 ሺህ300 የአሜሪካን ዶላር የገንዘብና አንድ መጸዳጃ ቤት ለመስራት የአይነት ድጋፍ አደረጉ።
ድጋፋቸውን በአሜሪካ የኢትየጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ስለሺ በቀለ አስረክበዋል።
የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አትሌት ሀይሉ መኮንን ኢትዮጵያ በምትፈልጋቸው ወቅት ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የማህበሩ አባላት በተለያዩ አገራዊ ጥሪዎች ላይ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን አምባሳደር ስለሺ በቀለ
ጠቅሰው አሁንም ማህበሩ ለ”ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” ኢንሼቲቭ ላደረገው ድጋፍ ያላቸውን ምስጋና አቅርበዋል።
በአሜሪካ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን ለ”ጽዱ ጎዳና ኑሮ በጤና” እስከ አሁን በአጠቃላይ በጥሬ ገንዘብ 29 ሺህ 445 የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም 74 ሺህ የኢትዮጵያ ብር ተሰብስቧል።
በዓይነት 21 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ 14 መጸዳጃ ቤቶችን ለመስራት ቃል መግባታቸውን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓም