Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️

የቀደሙትን የኮሪደር ልማት ስራዎች ግምገማ ስናጠናቅቅ ቀጣዩን ግምገማችንን በስራው ስፍራ ተገኝተን እንደምናካሂድ ቃል ገብተን ነበር። የፒያሳ እና የአራት ኪሎ መስመር ስራ በተያዘው የሶስት ወር መርሃግብር ማጠናቀቃችንን ስገልፅ ደስታ ይሰማኛል።

በቀጣይ ስራ ሀብት ቁጠባ ቀዳሚ ትኩረት ሆኖ በቀሪ ኮሪደሮች ስራዎቻችን ፈጣን እና ፈጠራ መር ልንሆን ይገባል። ጥራትን ማስጠበቅ እና ለዜጎቻችን ሁሉ የተመቸ ከባቢን መፍጠር ቅድሚያ የምንሰጣቸው ተግባራት ናቸው።

ይህ ፕሮጀክት የሚራመደው በብዙሃን ትብብር ነው። ከጅማሮው በስራችን ባገኘነው በጎፈቃድ ምስጋና አቀርባለሁ። ይህም በእቅድ እና አፈፃፀም ላይ የታየውን ጥረታችንን እና መልካም ፈቃዳችንን የመጠነ ሆኖ ታይቷል።

በዚህ ከተማችንን ለተሻለ ለውጥ ለማብቃት በተደከመበት ታላቅ ስራ ሂደት ውስጥ በዜጎቻችን ላይ ፈጥረነው ሊሆን ለሚችል አለመመቸት ይቅርታ እንጠይቃለን። ኢትዮጵያችን እንድትለወጥ በፅናት እንደምንሰራ በዚህ የኮሪደር ልማት ስራ ሂደትም ያሉ የዲዛይን እና የጥራት ክፍተቶችም ካሉ ማስተካከል እንደምንቀጥል እንድትተማመኑ ለመግለፅ እፈልጋለሁ።

በግሉ ዘርፍ ያሉ አጋሮቻችንን ጨምሮ ትናንት ምሽት በጎዳናዎች ፍቅራችሁን ለገለፃችሁልን፤ በአጠቃላይም በዚህ ስራ ለተሳተፋችሁ ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።

ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓም
የኢትዮጵያ ባሕር በር ተጠቃሚነት ለቀጣናው ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ ሚና ይኖረዋል
***
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ባሕር በር ተጠቃሚነት በቀጣናው ዘላቂ ሠላምን በማረጋገጥ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣት ጉልህ ሚና እንደሚኖረው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰፕላይ ቸን ማኔጅመንት ምሁር ማትዮስ ህንሰርሙ ( አሶሸት ፕሮፌሰር ) ገለጹ።

ማትዮስ (አሶሸት ፕሮፌሰር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ባሕር በር ተጠቃሚነት በቀጣናው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከማስቻሉም በላይ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት በማስመዝገብም ተባብሮ ማደግ ያስችላል፡፡

ኢትዮጵያ ባሕር በር ሳይኖራት የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች ቢሆንም ከዚህ የበለጠ ለማደግ ባሕር በር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ የባህር በር ለኢትዮጵያ የህልውናና አብሮ የማደግ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በዓለም አቀፍ ባህር በር አጠቃቀም ሕጎች መሠረት ማንኛውም ሀገር ባሕር በር የመጠቀም መብት የሚከለክል ሕግ አለመኖሩን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ ባሕር በር ተጠቃሚነት.....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129625
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️

ቃል በተግባር !

ከሁሉም በፊት የረዳንን ፈጣሪ እናመሰግናለን !

በተያዘላቸው የሶስት ወር ጊዜ ውስጥ የተጠናቀቁትን ፒያሳ የአድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያና የአራት ኪሎ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትርችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ፣ ከክብርት ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸውና ከሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር ገምግመናል።

አዲስ አበባን ከከተማው ነዋሪ ስንረከባት ልናስውባት፣ ልናለማት ቃል ገብተን ነው የጀመርነው። ለትውልድ የምትተርፍ፣ ቆሻሻ እና ስንፍና የሌለባት ከተማ ልናድርጋት ቃል ገብተን ነበር። እነሆ ቃላችንን ጠብቀናል!!

እንካችሁ የፀዳች አራዳን፤ እንካችሁ 24/7 የምትተጋ አራት ኪሎን፤ አሁን ለናንተ ምቹ አድርገናታል። ከውበቷና ከፅዳቷ ሳትጎድል ለትውልድ አኑሯት።

የኮሪደር ልማት ስራዎች ስንጀምር አብራችሁን ለተነሳችሁ፣ ለተባበራችሁ፣ ላሳመራችሁ ባለቤቶች፣ ለተባበራችሁ ባለሀብቶች፣ ተቋራጮች፣ በሙያችሁ ለተጋችሁ ሰራተኞች፣ አመራሮችና የፌደራል ተቋማት ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።

ከሁሉ በላይ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለነበራቸው ድጋፍና ክትትል ምስጋናዬ ትልቅ ነው። በአጠቃላይ ትናንት ምሽት ስንጎበኝ በጎዳናዎች ላይ ስራዎቹን እያደነቃችሁ ፍቅራችሁን ለገለፃችሁልን ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችን ይድረሳችሁ።

ያስቀመጥንላችሁ ፎቶዎች ከፊል ገፅታዎች ናቸው። ሙሉውን ገፅታ መጥታችሁ ትመለከቱ ዘንድ እጋብዛችኋለሁ። ቀሪ የኮሪደር ስራዎቻችንን ፍጥነትንና የፈጠራ መርህን ተከትለን አጠናቅቀን ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን።

ጥራትን ማስጠበቅ እና ለዜጎቻችን ሁሉ የተመቸ ከባቢን መፍጠር ቅድሚያ የምንሰጣቸው ተግባራት ናቸው።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
በክልሉ ከበጋ መስኖ ልማት 31 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኘ
******
(ኢ ፕ ድ)

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በበጋ መስኖ ልማት 31 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። በበጋ መስኖ ልማት ሥራው ከ33 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ እድል እንደተፈጠረላቸው ተመላክቷል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ገበያው የሚፈልገውን እና ክልሉ ባለው የመሬትና የውሃ አቅም ልክ የበጋ መስኖ ልማት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሠራ ቆይቷል።

በበጋ መስኖ ልማት 147 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት 33 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ፤ 147 ሺህ 500 ሄክታር መሬትን በማልማት 31 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን አስታውቀዋል።

በበጋ መስኖ ልማት ከለማው 147 ሺህ 500 ሄክታር መሬት ውስጥ ሁለት ሺህ 600 ሄክታር መሬትን በበጋ ስንዴ በማልማት ከ100 ሺህ ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129651
76 አዳዲስ የገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሆነዋል
******
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት 10 ወራት በኢትዮጵያ 76 አዳዲስ የገጠር ከተሞችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ እንደተቻለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ።

የተቋሙ የአገልግሎት ታሪፍ ወጪን መሠረት ያደረገ አለመሆኑ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት እንቅፋት መፍጠሩ ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መላኩ ታዬ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ባለፉት አስር ወራት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽነትን ለማስፋት የተለያዩ ሥራዎች ተሠርተዋል።

በዚህም 76 አዳዲስ የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

አቶ መላኩ ባለፉት አስር ወራት ከ328 ሺህ በላይ አዲስ ደንበኞች ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን ጠቁመው፤ ከነዚህም ውስጥ 31 ሺዎቹ በሚያዚያ ወር አገልግሎቱን........

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129645
አስተዳደሩ ለአረንጓዴ ዐሻራ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ችግኞች አዘጋጀ
******
(ኢ ፕ ድ)

ለዘንድሮው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ከ5 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ለመትከል መዘጋጅቱን በኦሮሚያ ክልል የማያ ከተማ አስተዳደር ገለጸ።

የማያ ከተማ ከንቲባ ዶክተር ኢፍረሃ ወዘር ለኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ እንደገለጹት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ለምስራቁ የሀገራችን ክፍል በተለይም ለከተማዋ ያለውን ከፍተኛ ጥቅም በመረዳት በየዓመቱ በሚሊዮች የሚቆጠር ችግኞችን እየተተከሉ፣ ክትትልና እና እንክብካቤ እየተደረገባቸው ይገኛል።

ለአብነትም በባለፈው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ወቅት የከተማው አስተዳደር እና ማህበረሰብ መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ከ4 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ችግኝ መተከሉን አውስተው፤ ከተከላ በኋላ በተሠራው የመንከባከብ እና የመጠበቅ ሥራ ከ82 በመቶ በላይ ችግኞች መጸደቃቸውን.......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129647