የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕዝብ በዓላት እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ አጸደቀ
*******
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 31ኛ መደበኛ ስብሰባው የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አጽድቋል።
በተመሳሳይ ሶስት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።
ረቂቅ አዋጁን በዝርዝር ሲመለከቱ የነበሩት የጤና፣ ማህበራዊ ልማትና ስፖርት ጉዳዮች እና የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች በጋራ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
የውሳኔ ሀሳቡን ያቀረቡት የጤና፣ ማህበራዊ ልማትና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ወርቀስሙ ማሞ፤ አዋጁ ላይ የተካተቱ ዋና ዋና ሀሳቦችን በዝርዝር አቅርበዋል።
የሕዝብ በዓላት ለዜጎች ሥነ-ምግባርና ስነ-ልቦና ግንባታ እንዲሁም ለሀገርና ለህዝብ ያላቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ ስለመሆኑ በውሳኔ ሀሳቡ ተብራርቷል።
የሕዝብ በዓላት ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ታሪካዊ እሴታቸውን ጠብቀው በሰላም በድምቀት እና የዜጎችን የእርስ በእርስ መልካም ግንኙነትና መተሳሰብ በሚያጎለብት ሁኔታ እንዲከበሩ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።
የህዝብ በዓላት አከባበርና ሥርዓት ኃይማኖታዊና ባህላዊ ይዘታቸውን ጠብቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ያለው አስተዋፅዎና ለሀገራዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና ያላቸው በመሆኑ ከመንግስት የሚጠበቀውን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ እንዲሁም በቂ የሚዲያ ሽፋን የሚሰጥ እንደሆነም በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ተብራርቷል።
ነባሩ የሕዝብ በዓላትና የዕረፍት ቀን መወሰኛ አዋጅ የሕዝብ በዓላት ሲከበሩ ጥቅም ሊያስገኙ በሚችሉ መልኩ በድምቀት የሚከበሩበትን ዝርዝር የአከባበር ሥነ-ሥርዓት አለማስቀመጡም ተመላክቷል፡፡
ይህ አዋጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሕዝብ በዓላትና የበዓላትን አከባበር የሚመለከት ሲሆን፤ ክልሎች በራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ ህግ አውጥተው በክልል ደረጃ የሚከበሩት መወሰን እንደሚችሉ ገልፀዋል።
በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመስልና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለዝርዝር እይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መምራቱን ከምክር ቤቱ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 31ኛ መደበኛ ስብሰባው የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አጽድቋል።
በተመሳሳይ ሶስት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።
ረቂቅ አዋጁን በዝርዝር ሲመለከቱ የነበሩት የጤና፣ ማህበራዊ ልማትና ስፖርት ጉዳዮች እና የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች በጋራ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
የውሳኔ ሀሳቡን ያቀረቡት የጤና፣ ማህበራዊ ልማትና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ወርቀስሙ ማሞ፤ አዋጁ ላይ የተካተቱ ዋና ዋና ሀሳቦችን በዝርዝር አቅርበዋል።
የሕዝብ በዓላት ለዜጎች ሥነ-ምግባርና ስነ-ልቦና ግንባታ እንዲሁም ለሀገርና ለህዝብ ያላቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍተኛ ስለመሆኑ በውሳኔ ሀሳቡ ተብራርቷል።
የሕዝብ በዓላት ኃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ታሪካዊ እሴታቸውን ጠብቀው በሰላም በድምቀት እና የዜጎችን የእርስ በእርስ መልካም ግንኙነትና መተሳሰብ በሚያጎለብት ሁኔታ እንዲከበሩ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።
የህዝብ በዓላት አከባበርና ሥርዓት ኃይማኖታዊና ባህላዊ ይዘታቸውን ጠብቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ያለው አስተዋፅዎና ለሀገራዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና ያላቸው በመሆኑ ከመንግስት የሚጠበቀውን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ እንዲሁም በቂ የሚዲያ ሽፋን የሚሰጥ እንደሆነም በቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ተብራርቷል።
ነባሩ የሕዝብ በዓላትና የዕረፍት ቀን መወሰኛ አዋጅ የሕዝብ በዓላት ሲከበሩ ጥቅም ሊያስገኙ በሚችሉ መልኩ በድምቀት የሚከበሩበትን ዝርዝር የአከባበር ሥነ-ሥርዓት አለማስቀመጡም ተመላክቷል፡፡
ይህ አዋጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሕዝብ በዓላትና የበዓላትን አከባበር የሚመለከት ሲሆን፤ ክልሎች በራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ ህግ አውጥተው በክልል ደረጃ የሚከበሩት መወሰን እንደሚችሉ ገልፀዋል።
በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመስልና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለዝርዝር እይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መምራቱን ከምክር ቤቱ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሰኔ 4 ቀን 2016 ዓም
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሦስተኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ሆናለች
****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ማሻሻል በመቻሉ በ2016 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሦስተኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆን መቻሏን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ሐና አርዓያሥላሴ እንደገለጹት፤የኢትዮጵያ መንግሥት የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ለማሻሻል ብዙ የአሠራር ማሻሻያዎችና ለውጦች አድርጓል፡፡
የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ማሻሻል በመቻሉ እየተገባደደ ባለው የ2016 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሦስተኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለመሆን በቅታለች፡፡
ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በምሥራቅ አፍሪካ ቁጥር አንድ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆን መቻሏን አውስተው፤ በቀጣይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንቶችን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ጠንካራ ሥራ እየተሠራ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነር ሐና ገለጻ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ለማሻሻል ብዙ የአሠራር ማሻሻያዎችና ለውጦች ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዋናነት መሠረተ ልማት ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን https://press.et/?p=129735
****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ማሻሻል በመቻሉ በ2016 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሦስተኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆን መቻሏን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ሐና አርዓያሥላሴ እንደገለጹት፤የኢትዮጵያ መንግሥት የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ለማሻሻል ብዙ የአሠራር ማሻሻያዎችና ለውጦች አድርጓል፡፡
የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ማሻሻል በመቻሉ እየተገባደደ ባለው የ2016 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሦስተኛ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ለመሆን በቅታለች፡፡
ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት በምሥራቅ አፍሪካ ቁጥር አንድ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆን መቻሏን አውስተው፤ በቀጣይ ተጨማሪ ኢንቨስትመንቶችን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ጠንካራ ሥራ እየተሠራ ስለመሆኑም ገልጸዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነር ሐና ገለጻ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ለማሻሻል ብዙ የአሠራር ማሻሻያዎችና ለውጦች ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዋናነት መሠረተ ልማት ላይ የተደረጉ ኢንቨስትመንቶች.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን https://press.et/?p=129735
ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት በጋራ ለማደግ የሚያስችል ነው
***************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ከቀጣናው ሀገሮች ጋር በጋራ ለማደግ የሚያስችል መሆኑን የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል የሱፍ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል የሱፍ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት በቀጣናው ሀገራት ብዙ ዕድሎችን ይፈጥራል፡፡
በተለይ ሀገሮቹ በጋራ ችግር ፈቺ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ምርምሮችን በመስራት በጋራ ለማደግ ያስችላቸዋል።
በምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በተለይ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ያለውን የረዥም ጊዜ ልምድ በመጠቀም የአካባቢውን አርሶ አደርና የማህበረሰቡን ፍላጎት መሠረት በማድረግ ችግር ፈቺ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኘ ጀማል (ዶ/ር) ገልጸው፤ይሁንና ዩኒቨርሲቲው የሚሠራውን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129736
***************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ከቀጣናው ሀገሮች ጋር በጋራ ለማደግ የሚያስችል መሆኑን የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል የሱፍ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል የሱፍ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት በቀጣናው ሀገራት ብዙ ዕድሎችን ይፈጥራል፡፡
በተለይ ሀገሮቹ በጋራ ችግር ፈቺ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ምርምሮችን በመስራት በጋራ ለማደግ ያስችላቸዋል።
በምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በተለይ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ያለውን የረዥም ጊዜ ልምድ በመጠቀም የአካባቢውን አርሶ አደርና የማህበረሰቡን ፍላጎት መሠረት በማድረግ ችግር ፈቺ የምርምር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኘ ጀማል (ዶ/ር) ገልጸው፤ይሁንና ዩኒቨርሲቲው የሚሠራውን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129736
በመዲናዋ 35 በመቶ ሕፃናት በወቅቱ ትምህርት አያገኙም
**************
(ኢ ፕ ድ)
በመዲናዋ እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሱ ሕፃናት መካከል 35 በመቶ በወቅቱ ትምህርት ቤት እንደማይገቡ የአዲስ አበባ ሴቶች ፣ ሕፃናት፣ ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ፡፡
ቢሮው “የሕፃናት ትምህርት ፣ተሳትፎና ጥራት ለማሳደግ ጊዜው አሁን ነው” በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ ዘጠኝ ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአፍሪካ የሕፃናት ቀን አስመልክቶ ከማስታወቂያና ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።
በቢሮው የሕፃናት መብት ደህንነት ማስጠበቅ ቡድን መሪ አናኒያ ያቆብ እንደገለጹት፤ ቢሮው በቅርቡ ባደረገው ጥናት ሰባት ዓመት ሆኗቸው እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሱ ሕፃናት መካከል ወደ ትምህርት ቤት የሚገቡ ሕፃናት ቁጥር.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129751
**************
(ኢ ፕ ድ)
በመዲናዋ እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሱ ሕፃናት መካከል 35 በመቶ በወቅቱ ትምህርት ቤት እንደማይገቡ የአዲስ አበባ ሴቶች ፣ ሕፃናት፣ ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታወቀ፡፡
ቢሮው “የሕፃናት ትምህርት ፣ተሳትፎና ጥራት ለማሳደግ ጊዜው አሁን ነው” በሚል መሪ ሃሳብ ሰኔ ዘጠኝ ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአፍሪካ የሕፃናት ቀን አስመልክቶ ከማስታወቂያና ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።
በቢሮው የሕፃናት መብት ደህንነት ማስጠበቅ ቡድን መሪ አናኒያ ያቆብ እንደገለጹት፤ ቢሮው በቅርቡ ባደረገው ጥናት ሰባት ዓመት ሆኗቸው እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሱ ሕፃናት መካከል ወደ ትምህርት ቤት የሚገቡ ሕፃናት ቁጥር.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129751
በሚቀጥሉት ቀናት የሚጠበቀው ዕርጥበት የመኸር ሰብሎችን ለመዝራትና ማሳን ለማዘጋጀት አዎንታዊ ሚና ይኖረዋል
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በሚቀጥሉት ቀናት የሚጠበቀው እርጥበት አስቀድመው የሚዘሩ የመኸር ሰብሎችን ለመዝራትና ማሳን ለማዘጋጀት አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ ፡፡
ኢንስቲትዩት ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላከው መግለጫ፤ በሚቀጥሉት ዘጠኝ ቀናት የሚጠበቀው እርጥበት አስቀድመው የሚዘሩ የመኸር ሰብሎችን በወቅቱ ለመዝራትና ማሳን ለማዘጋጀት አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አስታውቋል።
በበልግ አብቃይ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ዘግይተው ለተዘሩና ፍሬ በመሙላት ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች፣ ለቋሚ አትክልቶች እና ፍራፍሬዎች የውሃ ፍላጎትን ከማሟላት አንጻር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በመግለጫው ተመላክቷል።
በምዕራብ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚጠበቀው የእርጥበት ሁኔታ የረጅም ጊዜ ሰብሎችን ለመዝራት፣ ለቋሚ ተክሎች፣ በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ለተተከሉና ለሚተከሉ ችግኞች እድገት ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል በሚቀጥሉት ቀናት በዓባይ፣ በላይኛውና በመካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ አዋሽ፣ ተከዜና በጥቂት የአፋር ደናክል ተፋሰሶች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የእርጥበት ያገኛሉ። በተፋሰሶች ላይ የሚኖረውን የገፀ ምድርም ሆነ የከርሰ ምድር የውሃ ሀብትን ያሻሽላል፤ ለመስኖም ሆነ ለሀይል ማመንጫነት የሚያገለግሉ የግድቦችን የውሃ መጠን ያሻሽላል ተብሏል፡፡
በአጠቃላይ በሚቀጥሉት ዘጠኝ ቀናት ለክረምት መፈጠር አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ከቀን ወደ ቀን እየተስፋፉና እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ ተመላክቷል።
በሄለን ወንድምነው
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በሚቀጥሉት ቀናት የሚጠበቀው እርጥበት አስቀድመው የሚዘሩ የመኸር ሰብሎችን ለመዝራትና ማሳን ለማዘጋጀት አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ ፡፡
ኢንስቲትዩት ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላከው መግለጫ፤ በሚቀጥሉት ዘጠኝ ቀናት የሚጠበቀው እርጥበት አስቀድመው የሚዘሩ የመኸር ሰብሎችን በወቅቱ ለመዝራትና ማሳን ለማዘጋጀት አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አስታውቋል።
በበልግ አብቃይ በሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ዘግይተው ለተዘሩና ፍሬ በመሙላት ላይ ለሚገኙ የበልግ ሰብሎች፣ ለቋሚ አትክልቶች እና ፍራፍሬዎች የውሃ ፍላጎትን ከማሟላት አንጻር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው በመግለጫው ተመላክቷል።
በምዕራብ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚጠበቀው የእርጥበት ሁኔታ የረጅም ጊዜ ሰብሎችን ለመዝራት፣ ለቋሚ ተክሎች፣ በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ለተተከሉና ለሚተከሉ ችግኞች እድገት ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
በሌላ በኩል በሚቀጥሉት ቀናት በዓባይ፣ በላይኛውና በመካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ ኦሞ ጊቤ፣ ስምጥ ሸለቆ፣ አዋሽ፣ ተከዜና በጥቂት የአፋር ደናክል ተፋሰሶች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የእርጥበት ያገኛሉ። በተፋሰሶች ላይ የሚኖረውን የገፀ ምድርም ሆነ የከርሰ ምድር የውሃ ሀብትን ያሻሽላል፤ ለመስኖም ሆነ ለሀይል ማመንጫነት የሚያገለግሉ የግድቦችን የውሃ መጠን ያሻሽላል ተብሏል፡፡
በአጠቃላይ በሚቀጥሉት ዘጠኝ ቀናት ለክረምት መፈጠር አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ከቀን ወደ ቀን እየተስፋፉና እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ ተመላክቷል።
በሄለን ወንድምነው
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
ኢትዮጵያ በማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንት ድንገተኛ ሕልፈት የተሰማትን ሐዘን ገለጸች
*************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ የማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንት ሳውሎስ ቺሊማን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት በቀጠፈው አሰቃቂ የአውሮፕላን አደጋ የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ገለጸች፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው የሐዘን መግለጫ በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ ለማላዊ መንግሥትና ሕዝብ የተሰማውን ሐዘን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
የማላዊ መከላከያ ኃይል አውሮፕላን የሀገሪቱን ምክትል ፕሬዚዳንት ሳውሎስ ቺሊማን ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎችን አሳፍሮ ባጋጠመው የመከስከስ አደጋ ሁሉም ተሳፋሪዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ማሳወቃቸው ይታወሳል፡፡
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
*************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ የማላዊ ምክትል ፕሬዚዳንት ሳውሎስ ቺሊማን ጨምሮ የዘጠኝ ሰዎችን ሕይወት በቀጠፈው አሰቃቂ የአውሮፕላን አደጋ የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ገለጸች፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው የሐዘን መግለጫ በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ ለማላዊ መንግሥትና ሕዝብ የተሰማውን ሐዘን በመግለጽ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
የማላዊ መከላከያ ኃይል አውሮፕላን የሀገሪቱን ምክትል ፕሬዚዳንት ሳውሎስ ቺሊማን ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎችን አሳፍሮ ባጋጠመው የመከስከስ አደጋ ሁሉም ተሳፋሪዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ማሳወቃቸው ይታወሳል፡፡
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) 100 ቀናት እና የሁለተኛው ሀገር በቀል ኢኮኖሚ አፈጻጸም እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ባቀረቡት ሪፖርት‼️
👉 ባለፉት አሥር ወራት የ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል፣
👉 ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ14 ነጥብ 3 በመቶ ብልጫ አሳይቷል፣
👉 መንግሥት 425 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰብስቧል፣ 271 ቢሊዮን ብሩ ከሀገር ውስጥ ገቢ የተሰበሰበ ነው፣
👉 ከሸቀጦች የወጪ ንግድ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር፤ ከሬሚታንስ 4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል፣
👉 የመንግሥት የበጀት ጉድለትም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ14 በመቶ ቀንሷል፣
👉 ለ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች በሀገር ውስጥ፤ ለ300 ሺህ ለሚሆኑት በውጭ ሀገራት የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፣
👉 በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካቾች ኢትዮጵያ የ7 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ታሰመዘግባለች፣
ዝርዝር መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129734
👉 ባለፉት አሥር ወራት የ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል፣
👉 ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ14 ነጥብ 3 በመቶ ብልጫ አሳይቷል፣
👉 መንግሥት 425 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰብስቧል፣ 271 ቢሊዮን ብሩ ከሀገር ውስጥ ገቢ የተሰበሰበ ነው፣
👉 ከሸቀጦች የወጪ ንግድ 2 ነጥብ 9 ቢሊዮን ዶላር፤ ከሬሚታንስ 4 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል፣
👉 የመንግሥት የበጀት ጉድለትም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ14 በመቶ ቀንሷል፣
👉 ለ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች በሀገር ውስጥ፤ ለ300 ሺህ ለሚሆኑት በውጭ ሀገራት የሥራ ዕድል ተፈጥሯል፣
👉 በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካቾች ኢትዮጵያ የ7 ነጥብ 9 በመቶ እድገት ታሰመዘግባለች፣
ዝርዝር መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129734
በኢኮኖሚና በሌሎች ዘርፎች የተገኙ ውጤቶች መንግሥት በተግባር እየፈጸመ መሆኑን ያመላክታሉ - አቶ አደም ፋራህ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢኮኖሚና በሌሎች ዘርፎች የተገኙ ውጤቶች መንግሥት ቃልን በተግባር እየፈጸመ መሆኑን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለፁ።
የበጀት ዓመቱ የመጨረሻው የ100 ቀናት የአፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፤ ግምገማውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸው፤ ገዥው ፓርቲ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማሳካት ለሕዝብ ቃል የገባቸው ግቦች እንደነበሩት አስታውሰዋል።
በፓርቲው ማኒፌስቶ የተቀመጡ ግቦችን በተግባር ዕውን ለማድረግ የዘንድሮውን ጨምሮ በየጊዜው የአፈጻጸም ግምገማዎች እንደሚደረጉ ጠቁመው፤ በግምገማው ቃልን በተግባር ማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።
ለአብነትም መንግሥት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከአፍሪካ ግዙፍ አምስት ኢኮኖሚዎች አንዱ የማድረግ ግብን ለሕዝብ በይፋ ማሳወቁን አስታውሰው፤ ይህንንም ቃል በተግባር ማረጋገጥ መቻሉን ነው የገለጹት።
የጥቅል አገራዊ ምርትን በአጭር ጊዜ 205 ቢሊየን ዶላር በማድረስ በእጥፍ ማሳደግ መቻሉን እንዲሁም በነፍስ ወከፍ ገቢም ዕድገት መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በግብርናው ዘርፍ ከ3 ሚሊየን ሄክታር መሬት በላይ በማልማትና 100 ሚሊየን ኩንታል ምርት በመጨመር ምርታማነትን ማሳደግ ስለመቻሉ ገልፀዋል።
በኢንዱስትሪው ዘርፍ ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ጨምሮ በዘርፉ በተሰሩ ሥራዎች ነባር ኢንዱስትሪዎች ወደ ሙሉ አቅማቸው እንዲሸጋገሩና አዳዲስ አልሚዎችም ወደማምረቻው ዘርፍ እንዲገቡ ማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል።
በቱሪዝም ዘርፍና በማዕድን ዘርፎች ያሉ ዕምቅ ጸጋዎችን የመለየትና የማልማት ሥራዎችም ትልልቅ ኩባንያዎች በዘርፉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ በማስቻል ለአገር ብልጽግና የሚበጁ ተግባራት መከናወናቸውንም አንስተዋል።
በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍም የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ግብ ለማሳካት የሚያስችሉ ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን በአጠቃላይ ግምገማዎቹ ቃልን በተግባር ለማረጋገጥ ጥረቱ መቀጠሉን አመላካች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በአጠቃላይ በኢኮኖሚውና በሌሎች ዘርፎች እንደ አገር የተገኘው እመርታ መንግሥት ቃልን በተግባር እየፈጸመ መቀጠሉን በግምገማው የተገኙ ስኬቶች ማሳያ መሆናቸውን ነው አቶ አደም የተናገሩት።
ሌላው መንግሥት በየጊዜው በሚደረጉ ሕዝባዊ ስብሰባዎች የሚነሱ የሕዝብ አንገብጋቢ ጥያቄዎችን በመለየት የመፍታት ቃል አንዱ ቁልፍ ጉዳይ እንደነበር ገልጸው፤ በዚህም ተጨባጭ ለውጦች መገኘታቸውን ተናግረዋል።
ለአብነትም ዓለም አቀፍ ችግር የሆነውን የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል በግብይት ሥርዓቱ ላይ በተከናወኑ ተግባራት የዋጋ ንረትን ወደ 23 በመቶ መቀነስ መቻሉን ጠቅሰዋል።
በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድም በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ለ 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች አዳዲስ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር መቻሉን አንስተዋል።
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢኮኖሚና በሌሎች ዘርፎች የተገኙ ውጤቶች መንግሥት ቃልን በተግባር እየፈጸመ መሆኑን የሚያረጋግጡ መሆናቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ገለፁ።
የበጀት ዓመቱ የመጨረሻው የ100 ቀናት የአፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ፤ ግምገማውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸው፤ ገዥው ፓርቲ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማሳካት ለሕዝብ ቃል የገባቸው ግቦች እንደነበሩት አስታውሰዋል።
በፓርቲው ማኒፌስቶ የተቀመጡ ግቦችን በተግባር ዕውን ለማድረግ የዘንድሮውን ጨምሮ በየጊዜው የአፈጻጸም ግምገማዎች እንደሚደረጉ ጠቁመው፤ በግምገማው ቃልን በተግባር ማረጋገጥ የሚያስችሉ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።
ለአብነትም መንግሥት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከአፍሪካ ግዙፍ አምስት ኢኮኖሚዎች አንዱ የማድረግ ግብን ለሕዝብ በይፋ ማሳወቁን አስታውሰው፤ ይህንንም ቃል በተግባር ማረጋገጥ መቻሉን ነው የገለጹት።
የጥቅል አገራዊ ምርትን በአጭር ጊዜ 205 ቢሊየን ዶላር በማድረስ በእጥፍ ማሳደግ መቻሉን እንዲሁም በነፍስ ወከፍ ገቢም ዕድገት መምጣቱን ጠቅሰዋል።
በግብርናው ዘርፍ ከ3 ሚሊየን ሄክታር መሬት በላይ በማልማትና 100 ሚሊየን ኩንታል ምርት በመጨመር ምርታማነትን ማሳደግ ስለመቻሉ ገልፀዋል።
በኢንዱስትሪው ዘርፍ ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ጨምሮ በዘርፉ በተሰሩ ሥራዎች ነባር ኢንዱስትሪዎች ወደ ሙሉ አቅማቸው እንዲሸጋገሩና አዳዲስ አልሚዎችም ወደማምረቻው ዘርፍ እንዲገቡ ማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል።
በቱሪዝም ዘርፍና በማዕድን ዘርፎች ያሉ ዕምቅ ጸጋዎችን የመለየትና የማልማት ሥራዎችም ትልልቅ ኩባንያዎች በዘርፉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ በማስቻል ለአገር ብልጽግና የሚበጁ ተግባራት መከናወናቸውንም አንስተዋል።
በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍም የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ ግብ ለማሳካት የሚያስችሉ ሰፊ ሥራዎች መከናወናቸውን በአጠቃላይ ግምገማዎቹ ቃልን በተግባር ለማረጋገጥ ጥረቱ መቀጠሉን አመላካች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በአጠቃላይ በኢኮኖሚውና በሌሎች ዘርፎች እንደ አገር የተገኘው እመርታ መንግሥት ቃልን በተግባር እየፈጸመ መቀጠሉን በግምገማው የተገኙ ስኬቶች ማሳያ መሆናቸውን ነው አቶ አደም የተናገሩት።
ሌላው መንግሥት በየጊዜው በሚደረጉ ሕዝባዊ ስብሰባዎች የሚነሱ የሕዝብ አንገብጋቢ ጥያቄዎችን በመለየት የመፍታት ቃል አንዱ ቁልፍ ጉዳይ እንደነበር ገልጸው፤ በዚህም ተጨባጭ ለውጦች መገኘታቸውን ተናግረዋል።
ለአብነትም ዓለም አቀፍ ችግር የሆነውን የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል በግብይት ሥርዓቱ ላይ በተከናወኑ ተግባራት የዋጋ ንረትን ወደ 23 በመቶ መቀነስ መቻሉን ጠቅሰዋል።
በሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድም በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ ለ 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዜጎች አዳዲስ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር መቻሉን አንስተዋል።
አርቲስት ይገረም ደጀኔ የአይን ብሌኑን ለኢትዮጵያ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ ለመለገስ ቃል ገባ
የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የደም ለጋሾች ቀን ቋሚ ደም ለጋሾችን በማመስገን ይከበራል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
20ኛው የደም ለጋሾች ቀን ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በማመስገን ከሰኔ 7 ጀምሮ እስከ 22 ቀን 2016 ዓም በተለያዩ መርሃግብሮች እንደሚከበር የኢትዮጵያ ደምና ህብረህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አሸናፊ ታዘበው(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ ጥራቱ የተጠበቀ የደም አቅርቦት የበርካታ እናቶች ህፃናትና የወጣቶችን ህይወት ያድናል።
ጠንነቱ ስለተጠበቀ የደም አቅርቦትና አስፈላጊነት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ይሰጣል ያሉት አሸናፊ ታዘበው(ዶ/ር) ቋሚ የደም ለጋሾች የማበረታታትና ጤንነቱ የተጠበቀ የደም አቅርቦት እንዲኖር እየሰራ ይገኛል።
የአገልግሎቱ አምባሳደር የሆነው አርቲስት ይገረም ደጀኔ በበኩሉ፤ ደም መለገስ ብዙ ግዜ የማይፈጅና የጤና ጉዳት የማያደርስ በጎ ተግባር ነው ሲሉ ገልፀዋል።
አንድ ሰው ደም ለግሶ በተወሰነ ደቂቃዎች ወደ ስራው መመለስ ይችላል። በተቃራኒው ደግሞ በርካታ ሰዎች በደም እጦት ህይወታቸው ያልፋል። በመሆኑም ማህበረሰቡ በቋሚነት ደም የመለገስ ልምድ ሊያዳብር ይገባል ብለዋል።
አርቲስት ይገረም ደጀኔ የአይን ብሌኑን ለኢትዮጵያ ደምና ህብረህዋስ ባንክ አገልግሎት ለመለገስ ቃል ገብቷል።
በአመለወርቅ ከበደ
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
የዘንድሮ ዓለም አቀፍ የደም ለጋሾች ቀን ቋሚ ደም ለጋሾችን በማመስገን ይከበራል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
20ኛው የደም ለጋሾች ቀን ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በማመስገን ከሰኔ 7 ጀምሮ እስከ 22 ቀን 2016 ዓም በተለያዩ መርሃግብሮች እንደሚከበር የኢትዮጵያ ደምና ህብረህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አሸናፊ ታዘበው(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፣ ጥራቱ የተጠበቀ የደም አቅርቦት የበርካታ እናቶች ህፃናትና የወጣቶችን ህይወት ያድናል።
ጠንነቱ ስለተጠበቀ የደም አቅርቦትና አስፈላጊነት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ይሰጣል ያሉት አሸናፊ ታዘበው(ዶ/ር) ቋሚ የደም ለጋሾች የማበረታታትና ጤንነቱ የተጠበቀ የደም አቅርቦት እንዲኖር እየሰራ ይገኛል።
የአገልግሎቱ አምባሳደር የሆነው አርቲስት ይገረም ደጀኔ በበኩሉ፤ ደም መለገስ ብዙ ግዜ የማይፈጅና የጤና ጉዳት የማያደርስ በጎ ተግባር ነው ሲሉ ገልፀዋል።
አንድ ሰው ደም ለግሶ በተወሰነ ደቂቃዎች ወደ ስራው መመለስ ይችላል። በተቃራኒው ደግሞ በርካታ ሰዎች በደም እጦት ህይወታቸው ያልፋል። በመሆኑም ማህበረሰቡ በቋሚነት ደም የመለገስ ልምድ ሊያዳብር ይገባል ብለዋል።
አርቲስት ይገረም ደጀኔ የአይን ብሌኑን ለኢትዮጵያ ደምና ህብረህዋስ ባንክ አገልግሎት ለመለገስ ቃል ገብቷል።
በአመለወርቅ ከበደ
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ማስተግበሪያ ፍኖተ ካርታ የሥነ ስርዓትና ፍሬ ነገር ህጎች እየተዘጋጁ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
የሽግግር ፍትህ ፖሊሲን ለመተግበር በአዋጁ የተጠቀሱ ተቋማትን ማቋቋም የሚያስችሉ የሥነ ስርዓትና ፍሬ ነገር ህጎች እየተዘጋጁ መሆኑን የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የበጀት ዓመቱ የመጨረሻው የ100 ቀናት አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። በዚህም መሰረት የፍትህ ሚኒስቴር የበጀት ዓመቱ የመጨረሻዎቹ 100 ቀናት የህግና ፍትህ ሥርዓቱ ያለበት አፈፃፀም ተገምግሟል፡፡
የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ(ዶ/ር) በግምገማው የሽግግር ፍትህ መጽደቅና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። የሽግግር ፍትህ ፖሊሲውን ለማዘጋጀት ጥናቶች፣ ምክክሮችና የባለድርሻ አካላትን የነቃ ተሳትፎ አካቶ የጸደቀ መሆኑን ተናግረዋል።
ፖሊሲውን መተግበር የሚያስችል ፍኖተ ካርታ መውጣቱን ገልጸው በፖሊሲው የተመላከቱ ተቋማትን ማቋቋም የሚያስችሉ የሥነ ስርዓትና ፍሬ ነገር ህጎች እየተዘጋጁ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የፍትህ ዘርፉን ለማሻሻል በፌደራልና በክልል ደረጃ ገቢራዊ የሚደረጉ ሀገር አቀፍ ህጎችና አሰራሮች መውጣታቸውን ጠቅሰው፣ የአስተዳደር ሥነ ስርዓት አዋጅን ማስተግበር፣ የወንጀል ሥነ ስርዓት አጽድቆ ገቢራዊ ማድረግም በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የማህበረሰብ ተኮር የፍትህ አገልግሎት ወይም ባህላዊ ፍርድ ቤትን የተመለከተ ሞዴል ህግ ተዘጋጅቶ ለክልሎች ተልኳል ሲሉም ጠቁመዋል።
የዲጂታላይዜሽን አሰራር፣ የፍትህ ዘርፉን አመራርና ባለሙያዎች ለማጥራት የተከናወኑ ተግባራት በጥንካሬ የሚወሰዱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በቀጣይም የፍትህ ስርዓቱን በማሻሻል የዜጎችን ተጠቃሚነት ማጎልበት የሚችሉ ማህበረሰብ ተኮር የፍትህ አገልግሎት ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል፡፡
የአስተዳደር ሥነ ሥርዓት አዋጅን በሁሉም ክልሎች ገቢራዊ ማድረግ የወንጀል ፍትህ ስርዓቱን ማሻሻል የቀጣይ የትኩረት መስክ መሆኑንም ገልጸዋል ሲለ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
****************
(ኢ ፕ ድ)
የሽግግር ፍትህ ፖሊሲን ለመተግበር በአዋጁ የተጠቀሱ ተቋማትን ማቋቋም የሚያስችሉ የሥነ ስርዓትና ፍሬ ነገር ህጎች እየተዘጋጁ መሆኑን የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የበጀት ዓመቱ የመጨረሻው የ100 ቀናት አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል። በዚህም መሰረት የፍትህ ሚኒስቴር የበጀት ዓመቱ የመጨረሻዎቹ 100 ቀናት የህግና ፍትህ ሥርዓቱ ያለበት አፈፃፀም ተገምግሟል፡፡
የፍትህ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ(ዶ/ር) በግምገማው የሽግግር ፍትህ መጽደቅና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። የሽግግር ፍትህ ፖሊሲውን ለማዘጋጀት ጥናቶች፣ ምክክሮችና የባለድርሻ አካላትን የነቃ ተሳትፎ አካቶ የጸደቀ መሆኑን ተናግረዋል።
ፖሊሲውን መተግበር የሚያስችል ፍኖተ ካርታ መውጣቱን ገልጸው በፖሊሲው የተመላከቱ ተቋማትን ማቋቋም የሚያስችሉ የሥነ ስርዓትና ፍሬ ነገር ህጎች እየተዘጋጁ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የፍትህ ዘርፉን ለማሻሻል በፌደራልና በክልል ደረጃ ገቢራዊ የሚደረጉ ሀገር አቀፍ ህጎችና አሰራሮች መውጣታቸውን ጠቅሰው፣ የአስተዳደር ሥነ ስርዓት አዋጅን ማስተግበር፣ የወንጀል ሥነ ስርዓት አጽድቆ ገቢራዊ ማድረግም በትኩረት እየተከናወነ ነው ብለዋል።
የማህበረሰብ ተኮር የፍትህ አገልግሎት ወይም ባህላዊ ፍርድ ቤትን የተመለከተ ሞዴል ህግ ተዘጋጅቶ ለክልሎች ተልኳል ሲሉም ጠቁመዋል።
የዲጂታላይዜሽን አሰራር፣ የፍትህ ዘርፉን አመራርና ባለሙያዎች ለማጥራት የተከናወኑ ተግባራት በጥንካሬ የሚወሰዱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በቀጣይም የፍትህ ስርዓቱን በማሻሻል የዜጎችን ተጠቃሚነት ማጎልበት የሚችሉ ማህበረሰብ ተኮር የፍትህ አገልግሎት ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል፡፡
የአስተዳደር ሥነ ሥርዓት አዋጅን በሁሉም ክልሎች ገቢራዊ ማድረግ የወንጀል ፍትህ ስርዓቱን ማሻሻል የቀጣይ የትኩረት መስክ መሆኑንም ገልጸዋል ሲለ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓም
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሐመድ በክልሉ የተከናወኑ የግብርና ስራዎችን አሰመልክተው ለኢፕድ በሰጡት ማብራሪያ ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች‼️
👉 ከ10 ሚሊየን ሄክታር የማያንስ ሊታረስ የሚችል መሬት አለ፤
👉 ከዚህ ውስጥ ከለውጡ በፊት ሲታረስ የነበረው ወደ 400ሺ ሄክታር ወደ 900 ሺ ሄክታር ማልማት ተችሏል፣
👉 ተጨማሪ 50ሺ ሄክታር በማልማት በአጠቃላይ ወደ 1 ሚሊዮን ሄክታር ለማሳደግ ይሰራል፣
👉 በክልሉ የተለያዩ ሰብል አይነቶችን ጨምሮ ይመረት የነበረው በዓመት ከ10 ሚሊዮን ኩንታል የማይበልጥ ነበር፣
👉 በአሁኑ ጊዜ ወደ 26 ሚሊዮን ኩንታል የተለያዩ ምርቶችን ማምረት ተችሏል፣
👉 በዘንድሮ ዓመት በጎዴና ሲቲ ዞኖች በ3 ሺ ሄክታር ላይ የሩዝ ምርት ለማምረት በሙከራ ደረጃ እየተሠራ ነው፣
👉 በፌደራል መስኖ እና ቆላማ ሚኒስቴር ድጋፍ ከስምንት ቢሊየን ብር በላይ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጀምረዋል፣
👉 ከግብርናው ጋር ተያይዞ በእንስሳት ሃብትም በጣም ጥሩ እምርታ እየታየ ይገኛል፣
👉 የእንስሳት ኳራንቲን ማዕከላትን ሠርቶ እንስሳት ለውጭ ገበያ እንዲቀርቡ ከማድረግ አንጻር ተግዳሮቶች አሉ፣
ርዕሰ መስተዳድሩ ከኢፕድ ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129495
👉 ከ10 ሚሊየን ሄክታር የማያንስ ሊታረስ የሚችል መሬት አለ፤
👉 ከዚህ ውስጥ ከለውጡ በፊት ሲታረስ የነበረው ወደ 400ሺ ሄክታር ወደ 900 ሺ ሄክታር ማልማት ተችሏል፣
👉 ተጨማሪ 50ሺ ሄክታር በማልማት በአጠቃላይ ወደ 1 ሚሊዮን ሄክታር ለማሳደግ ይሰራል፣
👉 በክልሉ የተለያዩ ሰብል አይነቶችን ጨምሮ ይመረት የነበረው በዓመት ከ10 ሚሊዮን ኩንታል የማይበልጥ ነበር፣
👉 በአሁኑ ጊዜ ወደ 26 ሚሊዮን ኩንታል የተለያዩ ምርቶችን ማምረት ተችሏል፣
👉 በዘንድሮ ዓመት በጎዴና ሲቲ ዞኖች በ3 ሺ ሄክታር ላይ የሩዝ ምርት ለማምረት በሙከራ ደረጃ እየተሠራ ነው፣
👉 በፌደራል መስኖ እና ቆላማ ሚኒስቴር ድጋፍ ከስምንት ቢሊየን ብር በላይ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጀምረዋል፣
👉 ከግብርናው ጋር ተያይዞ በእንስሳት ሃብትም በጣም ጥሩ እምርታ እየታየ ይገኛል፣
👉 የእንስሳት ኳራንቲን ማዕከላትን ሠርቶ እንስሳት ለውጭ ገበያ እንዲቀርቡ ከማድረግ አንጻር ተግዳሮቶች አሉ፣
ርዕሰ መስተዳድሩ ከኢፕድ ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129495