Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በኦጋዴን ከ21 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የተፈጥሮ ጋዝ መኖሩ ተረጋገጠ
***
(ኢ ፕ ድ)

በሶማሌ ክልል ኦጋዴን በተደረገ ዳሰሳ 21 ቢሊዮን 336 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ እንዳለ መረጋገጡን የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማትዮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ በሶማሌ ክልል ኦጋዴን በተደረገ ዳሰሳ 21 ቢሊዮን 336 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ እንዳለ ተረጋግጧል፡፡

በአካባቢው 19 ጉድጓዶችን በመቆፈር በተደረገ ዳሰሳ 21 ቢሊዮን 336 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ ተገኝቷል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በክልሉ ኦጋዴን አካባቢ ያለውን ሀብት በተገቢው መልኩ ለመጠቀም በስፋት ሥራዎች መሠራታቸውን አብራርተዋል፡፡

በአካባቢው ትልቅ ሀብት እንዳለ መረጋገጡን ያነሱት አቶ ሚሊዮን ፤ በተጨማሪም በኢትዮጵያ በስድስት ቦታዎች ላይ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ሀብት መኖሩን......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129874
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል 46 ሺህ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ አቅርቧል
*****
(ኢ ፕ ድ)
በበጀት ዓመቱ ባለፉት 11 ወራት 46 ሺህ ቶን የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ መቻሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል አስታወቀ፡፡ በመጪው ክረምት 71 ሚሊዮን የተለያየ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች ለመትከል ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ክልሉ ጨምሮ ገልጿል፡፡

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስራት መኩሪያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ በክልሉ 46 ሺህ ቶን የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ ተችሏል፡፡

እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ 67 ሺህ 348 ቶን የቡና ምርት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለመላክ ታቅዶ ባለፉት 11 ወራት 46 ሺህ ቶን ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ ተልኳል ያሉት አቶ አስራት፤ የተመረተው የቡና ምርትም ለሀገር ውስጥ ፍጆታ እንዲሁም ለውጭ ገበያ.....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129878
👍1
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
በክልሉ ከ612 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ነው
***************
(ኢ ፕ ድ)

በጋምቤላ ክልል በፌዴራል መንግሥት የተጀመሩ ከ612 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ዘጠኝ የመንገድ ፕሮጀክቶች በሥራ ላይ መሆናቸውን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡመድ ኡጁሉ ገለጹ፡፡

የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡመድ ኡጁሉ እንደገለፁት፤ የመሠረተ- ልማት ዘርፍ ጥራቱን የጠበቀ ፍትሃዊ የመሠረተ ልማት ሥርጭት ለማረጋገጥ በለውጡ ዓመታት የክልሉ መንግሥት ከፌዴራል መንግሥት ጋር በቅንጅት እየሠራ ይገኛል፡፡ በርካታ የመንገድ፣ የመብራትና የቴሌኮም ማስፋፊያ ተግባራትም ተከናውነዋል፡፡

በመንገድ መሠረት ልማት፣ ጤና ተቋማት፣ የትምህርት ተቋማትና ሌሎች የኤሰቲ መሠረተ ልማቶችም በሰፊው እንደተሠሩ የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በመንገድ ልማት ዘርፍ አያሌ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን አስገንዝበዋል፡፡

ከለውጡ በፊት የጎሬ-ጋምቤላ የአስፋልት መንገድ ብቻ የነበረ መሆኑን አንስተው፤ በአሁኑ ሰዓት በፌዴራል መንግሥት የተጀመሩ 612 ነጥብ 24 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው ዘጠኝ የመንገድ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129879
በጸጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ የነበረው የቡርቂቱ የውሃ ፕሮጀክት ዳግም ወደ ግንባታ ተመለሰ
****************
(ኢ ፕ ድ)
በጸጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ የነበረው የቡርቂቱ የውሃ ግድብ ፕሮጀክት ዳግም ወደ ግንባታ መመለሱን የምስራቅ ቦረና ዞን አስታወቀ።

የኦሮሚያ ክልል የግብርና ቢሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በምስራቅ ቦረና ዞን በጎሮ ዶላ ወረዳ የቡርቂቱ የውሃ ፕሮጀክት ጎብኝተዋል።

የምስራቅ ቦረና አስተዳደር አቶ አብዱራዛቅ ሁሴን በወቅቱ እንደገለጹት፤ በጸጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው ተቋርጦ የነበረው የቡርቂቱ የውሃ ግድብ ፕሮጀክት ዳግም ወደ ግንባታ ተመልሷል።

በክልሉ የፊና ፕሮጀክቶች ውስጥ የሚለሙ በዞኑ አራት የውሃ ግድብ ፕሮጀክቶች አሉ ያሉት አቶ አብዱራዛቅ፤ የቡርቂቱ የውሃ ግድብ የአርሶ አደሩን ከፍተኛ የውሃ ችግር ከመቅረፍ ጎን ለጎን በመስኖ የምግብ ፍጆታውን እንዲሸፍን ውጥን ያለው መሆኑን ጠቁመዋል።

እንደ አቶ አብዱራዛቅ ገለጻ፤፡ፕሮጀክቱ በ30 ሄክታር ላይ የተቀመጠ ሲሆን ፕሮጀክቱ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የኦሮሚያ መስኖና አርብቶ አደር ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ በበኩላቸው በክልሉ በፊና ፕሮጀክት ስር 73 የውሃ ግድብ እየተገነቡ መሆኑን ጠቅሰው 12 የሚሆኑት መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

የቡርቂቱ የውሃ ግድብ ፕሮጀክት የሚያስፈልገውን ማሽነሪ ተሟልቶ ዳግም ወደ ስራ ገብቷል።

አፈጻጸሙ 20 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል።

በልጅዓለም ፍቅሬ(ቦረና)
ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓም
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️
በከተማችን ከሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል ከሆኑ የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ተወያይተናል።
የዛሬው መድረካችን እየተሻሻለ የመጣውን የገዢ እና የተፎካካሪ ፓርቲዎች በጋራ የመስራት አዲስ የፖለቲካ ባህል መዳበር የበለጠ የሚያጠናክር ሲሆን፣ በዚህ ዓመት ብቻ ስለከተማችን ሰላም፣ ልማት እና የፖለቲካ ባህል መዳበር ስንመክር ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው። ምንም እንኳን የፖለቲካ ልዩነት ቢኖረንም፣ የጀመርነውን ይህን የትብብር ባህል በማጠናከር የጋራ አጀንዳዎቻችን ላይ ለጋራ ሃገር በጋራ መስራታችንን አሁንም እንቀጥላለን!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
በቀጣይ ሶስት አመታት ለማጠናቀቅ እየተሰራ የሚገኘው የአሶሳ ስታዲየም የግንባታ ሂደት አሁናዊ ገጽታ በፕሬስ ዐይን‼️

ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓም