የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ‼️
ያለ ህዝብ ብቁ ተሳትፎ የሚከናወን ስራ ሙሉ ሊሆን አይችልም!
ሰላማችንን ዘላቂ እና ህዝባዊ መሰረት ያለው ለማድረግ ዛሬ አሰልጥነን ያስመረቅናቸው 11 ሺሕ አዲስ ምልምል የሠላም ሠራዊት አባላትን ጨምሮ 341 ሺሕ የሠላም ሠራዊት አባላትን የከተማችን የሰላም ዘብ አድርገን አሰማርተናል።
ከ2013 ጀምሮ ሕዝባችንን በተደራጀ መልኩ ከጸጥታ ኃይሉ ጋር ማቀናጀት እና የሰላሙ ዋነኛ ባለቤት ማድረግ መቻላችን እስካሁን ጋስገኙን ውጤታማ እና ስኬታማ ስራዎች በተጨማሪ ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ሰላማዊ ማድረግ ችለናል።
ዛሬ የተመረቃችሁ የሰላም ሰራዊት አባላት ሕዝባችን የሰላሙ እና የተሰሩ መሰረተ ልማቶች ባለቤትና ቀዳሚ ተጠቃሚ መሆኑን በመረዳት በየአካባቢያችሁ የሰላምና የመሰረተ ልማቱ ዘብ በመሆን ህዝባችሁን በፍፁም ትህትና እና ፍቅር እንድታገለግሉ አደራ ማለት እወዳለሁ::
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ያለ ህዝብ ብቁ ተሳትፎ የሚከናወን ስራ ሙሉ ሊሆን አይችልም!
ሰላማችንን ዘላቂ እና ህዝባዊ መሰረት ያለው ለማድረግ ዛሬ አሰልጥነን ያስመረቅናቸው 11 ሺሕ አዲስ ምልምል የሠላም ሠራዊት አባላትን ጨምሮ 341 ሺሕ የሠላም ሠራዊት አባላትን የከተማችን የሰላም ዘብ አድርገን አሰማርተናል።
ከ2013 ጀምሮ ሕዝባችንን በተደራጀ መልኩ ከጸጥታ ኃይሉ ጋር ማቀናጀት እና የሰላሙ ዋነኛ ባለቤት ማድረግ መቻላችን እስካሁን ጋስገኙን ውጤታማ እና ስኬታማ ስራዎች በተጨማሪ ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ሰላማዊ ማድረግ ችለናል።
ዛሬ የተመረቃችሁ የሰላም ሰራዊት አባላት ሕዝባችን የሰላሙ እና የተሰሩ መሰረተ ልማቶች ባለቤትና ቀዳሚ ተጠቃሚ መሆኑን በመረዳት በየአካባቢያችሁ የሰላምና የመሰረተ ልማቱ ዘብ በመሆን ህዝባችሁን በፍፁም ትህትና እና ፍቅር እንድታገለግሉ አደራ ማለት እወዳለሁ::
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
የናይል ውኃን በፍትሀዊነት ለመጠቀም በተፋሰሱ ሀገራት መካከል ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል
- አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የናይል ውሃን በፍትሀዊነት ለመጠቀም በተፋሰሱ ሀገራት መካከል ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለፁ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት በመተባበር የአፍሪካ ድንበር ተሸጋሪ የውሃ ሀብትን በፍታዊነት መጠቀም ላይ ትኩረት ያደረገው 3ኛው አፍሪ ራን የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በጉባኤ ላይ እንደገለጹት፣ የናይል ተፋሰስ ሀገራት በመተባበር በጋራ መልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቆጣጠር ያስፈልጋል። በተፋሰሱ ሀገራት መካከል የልምድ ልውውጥና በጋራ መመካከር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የምትገነባው የዓባይ ግድብ ቀጣናዊ ውህደትንና በጋራ መልማትን እንደሚያጠናግር ገልጸዋል።
የናይል ተፋሰስ ኮሚሽን ለማቋቋም አባል ሀገራት የናይል የትብብር ማእቀፍን ማጽደቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በቅርቡ ቡሩንዲ ማጽደቁን በመግለጽ በቀጣይ አንድ አባል ሀገር ካጸደቀ ኮሚሽኑ እንደሚቋቋም ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በበኩላቸው፣ ጉባኤው በናይል ተፋሰስ ሀገራትና ማህበረሰብ መካከል ፍትሃዊ የውሃ ተጠቃሚነት እንዲኖር ያደርጋል።
ኢትዮጵያ የናይል ትብብር ማእቀፍን በመፈረም አህጉራዊ ውህደትና የጋራ ተጠቃሚነት እንዲኖር ቁርጠኝነቷን አሳይታለች ብለዋል።
በጉባኤው ላይ የተፋሰሰ ሀገራት ተወካዮች፣ ዲፕሎማቶችና ምሁራን ተገኝተዋል። በውሃ አስተዳደር ዙሪያ፣ የአየር ንረት ለውጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት ለዘላቂ ልማት በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት መጠቀም በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ የፓናል ውይይቶች ይደረጋሉ።
በሞገስ ጸጋዬ
ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓም
- አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የናይል ውሃን በፍትሀዊነት ለመጠቀም በተፋሰሱ ሀገራት መካከል ትብብርን ማጠናከር ያስፈልጋል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ገለፁ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት በመተባበር የአፍሪካ ድንበር ተሸጋሪ የውሃ ሀብትን በፍታዊነት መጠቀም ላይ ትኩረት ያደረገው 3ኛው አፍሪ ራን የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በጉባኤ ላይ እንደገለጹት፣ የናይል ተፋሰስ ሀገራት በመተባበር በጋራ መልማት፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቆጣጠር ያስፈልጋል። በተፋሰሱ ሀገራት መካከል የልምድ ልውውጥና በጋራ መመካከር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የምትገነባው የዓባይ ግድብ ቀጣናዊ ውህደትንና በጋራ መልማትን እንደሚያጠናግር ገልጸዋል።
የናይል ተፋሰስ ኮሚሽን ለማቋቋም አባል ሀገራት የናይል የትብብር ማእቀፍን ማጽደቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በቅርቡ ቡሩንዲ ማጽደቁን በመግለጽ በቀጣይ አንድ አባል ሀገር ካጸደቀ ኮሚሽኑ እንደሚቋቋም ገልጸዋል።
የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር አቶ ጃፋር በበኩላቸው፣ ጉባኤው በናይል ተፋሰስ ሀገራትና ማህበረሰብ መካከል ፍትሃዊ የውሃ ተጠቃሚነት እንዲኖር ያደርጋል።
ኢትዮጵያ የናይል ትብብር ማእቀፍን በመፈረም አህጉራዊ ውህደትና የጋራ ተጠቃሚነት እንዲኖር ቁርጠኝነቷን አሳይታለች ብለዋል።
በጉባኤው ላይ የተፋሰሰ ሀገራት ተወካዮች፣ ዲፕሎማቶችና ምሁራን ተገኝተዋል። በውሃ አስተዳደር ዙሪያ፣ የአየር ንረት ለውጥ፣ ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት ለዘላቂ ልማት በፍትሃዊነትና በምክንያታዊነት መጠቀም በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ የፓናል ውይይቶች ይደረጋሉ።
በሞገስ ጸጋዬ
ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓም
በኦሮሚያ ከ1 ሺህ 180 በላይ ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢንቨስትመንት ተሸጋግረዋል
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በክልሉ ባለፉት 10 ወራት ከአንድ ሺህ 180 በላይ ኢንተርፕራይዞች ወደተሻለ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የኦሮሚያ ሥራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ኃላፊ ኤባ ገርባ (ኢ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ቢሮው ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢንቨስትመንት እንዲሸጋገሩና ምርቶቻቸውን በስፋት እንዲያቀርቡ እየሠራ ነው፤ ባለፉት 10 ወራት አንድ ሺህ 182 ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡
ኢንተርፕራይዞች አቅማቸውን በማሳደግ የተለያዩ ምርቶችን ወደማዘጋጀት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፤ በኢንዱስትሪ፣ በግብርና ማቀነባበሪያዎች፣ በአገልግሎትና በተለያዩ ዘርፎች እራሳቸውን በማሳደግ ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በክልሉ በሚገኙ ወጣቶችና ኢንተርፕራይዞች አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ በርካታ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በሀገር ውስጥ ማዘጋጀት ተችሏል ብለዋል።
ቢሮው በየጊዜው ለሚሠሩ ቴክኖሎጂዎች የሙከራ መድረክ በማዘጋጀት ውጤታማነታቸው የሚለካ ሲሆን፤ በቀን እስከ ሰባት ኩንታል የሻይ ቅጠል ቆርጦ አድርቆ የሚያዘጋጅ ማሽን፣ የሩዝ ምርትን ሰብስቦ የሚያዘጋጅ ማሽን......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129948
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በክልሉ ባለፉት 10 ወራት ከአንድ ሺህ 180 በላይ ኢንተርፕራይዞች ወደተሻለ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የኦሮሚያ ሥራ እድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ኃላፊ ኤባ ገርባ (ኢ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ቢሮው ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢንቨስትመንት እንዲሸጋገሩና ምርቶቻቸውን በስፋት እንዲያቀርቡ እየሠራ ነው፤ ባለፉት 10 ወራት አንድ ሺህ 182 ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢንቨስትመንት ዘርፉ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡
ኢንተርፕራይዞች አቅማቸውን በማሳደግ የተለያዩ ምርቶችን ወደማዘጋጀት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፤ በኢንዱስትሪ፣ በግብርና ማቀነባበሪያዎች፣ በአገልግሎትና በተለያዩ ዘርፎች እራሳቸውን በማሳደግ ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በክልሉ በሚገኙ ወጣቶችና ኢንተርፕራይዞች አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ በርካታ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በሀገር ውስጥ ማዘጋጀት ተችሏል ብለዋል።
ቢሮው በየጊዜው ለሚሠሩ ቴክኖሎጂዎች የሙከራ መድረክ በማዘጋጀት ውጤታማነታቸው የሚለካ ሲሆን፤ በቀን እስከ ሰባት ኩንታል የሻይ ቅጠል ቆርጦ አድርቆ የሚያዘጋጅ ማሽን፣ የሩዝ ምርትን ሰብስቦ የሚያዘጋጅ ማሽን......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=129948
የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች‼️
የ1445ኛው የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ አሽከርካሪዎች የተለመደውን ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል፡፡
በዓሉን አስመልክቱ በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሶላት ስነ-ስርዓት ይካሄዳል፡፡
በዚህም፤
👉 ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ
👉 ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው አጎና ሲኒማ ላይ
👉 ከሜክሲኮ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ
👉 ከብሔራዊ ቤ/መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት ላይ፡፡
👉 ከኦሎሚፒያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ
👉 ከመገናኛ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ 22 መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ
👉 ከ ጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ለገሀር የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል አጠገብ
👉 ከሲግናል እና ከአቧሬ ወደ ካዛንቺስ የሚመጣው መንገድ አቧሬ ሴቶች አደባባይ ላይ
👉 ከመስቀል ፍላወር ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጣው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
👉 ከቄራ በአዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መገንጠያ ላይ
👉 ከጌጃ ሰፈር በሰንጋተራ ወደ ለገሐር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ
👉 ከአብነት በጌጃ ሰፈር ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ አጠገብ
👉 ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ሜትሮሎጂ መ/ቤት ላይ
👉 ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚሄዱ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ አካባቢ
👉 ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ወደ ለገሐር ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎላ ሚካኤል መስቀለኛው ላይ
ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ/ም ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጠቁሟል።
ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
የ1445ኛው የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ አሽከርካሪዎች የተለመደውን ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል፡፡
በዓሉን አስመልክቱ በአዲስ አበባ ስታዲዮምና በዙሪያው በሚገኙ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሶላት ስነ-ስርዓት ይካሄዳል፡፡
በዚህም፤
👉 ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ
👉 ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው አጎና ሲኒማ ላይ
👉 ከሜክሲኮ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ
👉 ከብሔራዊ ቤ/መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት ላይ፡፡
👉 ከኦሎሚፒያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ
👉 ከመገናኛ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ 22 መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ
👉 ከ ጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ለገሀር የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል አጠገብ
👉 ከሲግናል እና ከአቧሬ ወደ ካዛንቺስ የሚመጣው መንገድ አቧሬ ሴቶች አደባባይ ላይ
👉 ከመስቀል ፍላወር ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጣው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
👉 ከቄራ በአዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መገንጠያ ላይ
👉 ከጌጃ ሰፈር በሰንጋተራ ወደ ለገሐር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ
👉 ከአብነት በጌጃ ሰፈር ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ አጠገብ
👉 ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ሜትሮሎጂ መ/ቤት ላይ
👉 ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር ወደ ብሔራዊ ቴአትር ለሚሄዱ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ አካባቢ
👉 ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ወደ ለገሐር ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎላ ሚካኤል መስቀለኛው ላይ
ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ/ም ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጠቁሟል።
ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለ2016 የዒድ አል አድሃ በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች ‼️
👉 ነቢዩ ኢብራሂም በአላህ ትእዛዝ ልጃቸውን ለመሥዋዕትነት ያዘጋጁበት፤ ጽናታቸው ተፈትኖ ያሸነፉበት በዓል ነው፣
👉 ማንኛውም ፈተና በጽናት ካለፉት ዋጋው ከፈተናው በላይ መሆኑን እንማርበታለን፣
👉 ኢትዮጵያን ታላቅና የበለጸገች ሀገር ለማድረግ ስንነሣ ፈተናው ከባድ እንደሚሆን እናምን ነበር፣
👉 ነቢዩ ኢብራሂም ልጃቸው ኢስማኤልን ሳይሆን በምትኩ ከአላህ የተሰጣቸውን በግ ሠዉተዋል፣
👉 የሕዝባችንን ዘላቂ ጥቅሞች ለማስከበርና ከዛሬው የተሻለ ነገን ለመፍጠር ስንል፣ ብዙ ነገሮችን ሠዉተናል፤ ከምንወደው አካባቢ ወደ ሌላ ሄደናል፣
👉 ያለ መሥዋዕትነት የሚያድግ ሕዝብ፣ ያለ መሥዋዕትነት የሚበለጽግ ሀገር የለም፣
👉 የኮሪደር ልማቱን በዚህ መልኩ በመሥዋዕትነት ነው የሠራነው፡፡ ፍሬው ግን እጅግ ጣፋጭ መሆኑን አይተናል፣
👉 ሰላማችንን ለማስፈን ነፍጥን መጣል፤ ከጫካ መውጣትና የራስን ዋሻ ትቶ ወደ መስኩ መውጣትን ይፈልጋል፣
👉 ሁላችንም ለመሥዋዕትነት ከተዘጋጀን የማይሳካ የሰላም መንገድ የለም፣
👉 እንደ ልጅ ያሳደግናቸው ብዙ ልማዶች፣ ጠባዮች፣ አመለካከቶች፣ ርእዮተ ዓለሞችና አካሄዶች አሉን፡፡ እነርሱን ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም ስንል ለመሠዋት ዝግጁ ከሆንን፣ ውጤቱ ከሰላም በላይ ነው፣
👉 ምክክር የሚሳካው የተሻለ ሐሳብና የላቀ ዕውቀት በማዋጣት ብቻ አይደለም፤ ሌላ ወሳኝ ነገር ይፈልጋል፡፡ እርሱም መሥዋዕትነት ነው፣
👉 ከእኔ የተሻለ ሐሳብና ልምድ፣ ዕውቀትና ጥበብ ሊኖር ይችላል ብለን ማመንና መቀበል አለብን፣
👉 ልክ ልኩን ከመንገር፤ ነጥብ ከማስቆጠር፤ ጀግና ጀግና ከመጨዋት የወጣ ትኁት ሰብእና መያዝ አለብን፣
👉 እንደ ነቢዩ ኢብራሂም ያሳደግናቸውን ብቻ ሳይሆን አብረውን ያደጉትን ብዙ ጠባዮች ለመሠዋት መዘጋጀትን ይጠይቃል፣
👉 መሥዋዕትነት የሚከፍሉ ዜጎች በበዙ ቁጥር፣ ምክክር የላቀ ውጤት ያስገኛል፡፡
👉 የኮሪደር ልማታችን በየከተሞቻችን እንዲስፋፋ፤ ሰላማችን የጸና እና የማይደፈርስ እንዲሆን፤ ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ተካሂዶ እንዲሳካ - ያሳደግናቸውንና ያደጉብንን አንዳንድ ነገሮች መሥዋዕት ለማድረግ እንዘጋጅ፣
👉 ከጠመንጃ ወደ ማጨጃ እንዛወር፡፡ ከዲሞትፈር ወደ ምክክር እንምጣ፡፡ ከብሔር ግጭት ወደ ሐሳብ ፍጭት እንሻገር፡፡ የምንወደውን፣ የምንፈልገውንና ያሳደግነውን እንኳን ቢሆን ለሀገር ስንል ለመሠዋት እንዘጋጅ፡፡
መልካም በዓል ይሁን፡፡
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ስኔ 8 ቀን 2016 ዓ.ም
👉 ነቢዩ ኢብራሂም በአላህ ትእዛዝ ልጃቸውን ለመሥዋዕትነት ያዘጋጁበት፤ ጽናታቸው ተፈትኖ ያሸነፉበት በዓል ነው፣
👉 ማንኛውም ፈተና በጽናት ካለፉት ዋጋው ከፈተናው በላይ መሆኑን እንማርበታለን፣
👉 ኢትዮጵያን ታላቅና የበለጸገች ሀገር ለማድረግ ስንነሣ ፈተናው ከባድ እንደሚሆን እናምን ነበር፣
👉 ነቢዩ ኢብራሂም ልጃቸው ኢስማኤልን ሳይሆን በምትኩ ከአላህ የተሰጣቸውን በግ ሠዉተዋል፣
👉 የሕዝባችንን ዘላቂ ጥቅሞች ለማስከበርና ከዛሬው የተሻለ ነገን ለመፍጠር ስንል፣ ብዙ ነገሮችን ሠዉተናል፤ ከምንወደው አካባቢ ወደ ሌላ ሄደናል፣
👉 ያለ መሥዋዕትነት የሚያድግ ሕዝብ፣ ያለ መሥዋዕትነት የሚበለጽግ ሀገር የለም፣
👉 የኮሪደር ልማቱን በዚህ መልኩ በመሥዋዕትነት ነው የሠራነው፡፡ ፍሬው ግን እጅግ ጣፋጭ መሆኑን አይተናል፣
👉 ሰላማችንን ለማስፈን ነፍጥን መጣል፤ ከጫካ መውጣትና የራስን ዋሻ ትቶ ወደ መስኩ መውጣትን ይፈልጋል፣
👉 ሁላችንም ለመሥዋዕትነት ከተዘጋጀን የማይሳካ የሰላም መንገድ የለም፣
👉 እንደ ልጅ ያሳደግናቸው ብዙ ልማዶች፣ ጠባዮች፣ አመለካከቶች፣ ርእዮተ ዓለሞችና አካሄዶች አሉን፡፡ እነርሱን ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም ስንል ለመሠዋት ዝግጁ ከሆንን፣ ውጤቱ ከሰላም በላይ ነው፣
👉 ምክክር የሚሳካው የተሻለ ሐሳብና የላቀ ዕውቀት በማዋጣት ብቻ አይደለም፤ ሌላ ወሳኝ ነገር ይፈልጋል፡፡ እርሱም መሥዋዕትነት ነው፣
👉 ከእኔ የተሻለ ሐሳብና ልምድ፣ ዕውቀትና ጥበብ ሊኖር ይችላል ብለን ማመንና መቀበል አለብን፣
👉 ልክ ልኩን ከመንገር፤ ነጥብ ከማስቆጠር፤ ጀግና ጀግና ከመጨዋት የወጣ ትኁት ሰብእና መያዝ አለብን፣
👉 እንደ ነቢዩ ኢብራሂም ያሳደግናቸውን ብቻ ሳይሆን አብረውን ያደጉትን ብዙ ጠባዮች ለመሠዋት መዘጋጀትን ይጠይቃል፣
👉 መሥዋዕትነት የሚከፍሉ ዜጎች በበዙ ቁጥር፣ ምክክር የላቀ ውጤት ያስገኛል፡፡
👉 የኮሪደር ልማታችን በየከተሞቻችን እንዲስፋፋ፤ ሰላማችን የጸና እና የማይደፈርስ እንዲሆን፤ ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ተካሂዶ እንዲሳካ - ያሳደግናቸውንና ያደጉብንን አንዳንድ ነገሮች መሥዋዕት ለማድረግ እንዘጋጅ፣
👉 ከጠመንጃ ወደ ማጨጃ እንዛወር፡፡ ከዲሞትፈር ወደ ምክክር እንምጣ፡፡ ከብሔር ግጭት ወደ ሐሳብ ፍጭት እንሻገር፡፡ የምንወደውን፣ የምንፈልገውንና ያሳደግነውን እንኳን ቢሆን ለሀገር ስንል ለመሠዋት እንዘጋጅ፡፡
መልካም በዓል ይሁን፡፡
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ስኔ 8 ቀን 2016 ዓ.ም
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በ850 ሚሊዮን ብር የተገዙ ዘመናዊ የርጭት አውሮፕላኖችን ስራ አስጀመሩ
*******
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በ850 ሚሊዮን ብር የተገዙ አምስት ዘመናዊ የርጭት አውሮፕላኖች (ኤር ትራክተርስ) በይፋ ስራ አስጀምረዋል።
ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የበረሃ አንበጣ ወረርሽኝና ሌሎች አደጋዎችን ለመቆጣጠር የራሷ የኬሚካል ርጭት አውሮፕላኖች ስላልነበራት ለኪራይ እስከ 13 ቢሊየን ብር ወጪ ስታደርግ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የአደጋ መቆጣጠሪያ የኬሚካል ርጭት አውሮፕላኖች እንዲኖራት ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል።
ይህን ተከትሎም መንግሥት አምስት ዘመናዊ የኬሚካል ርጭትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ዘመናዊ ኤር ትራክተሮችን ግዥ ፈጽሞ በዛሬው ዕለት በይፋ ስራ አስጀምሯል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚህ ወቅት፥ ከዚህ ቀደም የአንበጣ ወረርሽኝ፣ የደን ቃጠሎና የግሪሳ ወፍን መቆጣጠር የሚያስችል ሀገራዊ አቅም ባለመኖሩ በሰው ኃይል በባህላዊ መንገድ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል ብለዋል።
በሰሜን ተራሮችና በባሌ ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ቃጠሎ ባጋጠመ ጊዜ ኢትዮጵያ በልመና እና በኪራይ ከሌሎች አገራት የርጭት አውሮፕላኖችን በማምጣት ስትጠቀም መቆየቷን አውስተዋል።
አሁን ላይ መንግስት አደጋን በራስ የመቋቋምና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አካል ያደረገውን የአምስት ኤር ትራክተሮች ( የርጭት አውሮፕላኖችን) ገዝቶ ወደ ስራ ማስገባቱንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የኤር ትራክተር ባለቤት መሆኗ የጸረ አረምና ጸረ ተባይ የኬሚካል ርጭትን፣ የበረሃ አንበጣ መከላከልን፣ የስንዴና መሰል ሰብሎች የዋግ በሽታን ለመከላከል ትልቅ ሀገራዊ አቅም መሆኑን ገልጸዋል።
አውሮፕላኖቹ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙና ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የመስጠት አቅም ያላቸው በመሆናቸው እንደ እሳት ያሉ እና ሎሎች የተፈጥሮ አደጋዎች በፍጥነት ምላሽ መስጠት እንደሚያስችሉም አንስተዋል።
አውሮፕላኖቹ ከኢትዮጵያ ባለፈም ለጎረቤት ሀገርና ለሌሎችም ጥቅም መስጠት የሚችሉ ናቸው ብለዋል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እውቀትና ቴክኖሎጂ የግብርና መር ስራን ለመተግበር በሂደት ላይ መሆኗን አንስተዋል።
ከ2011 ሰኔ ወር ጀምሮ የተከሰተው የበረሃ አንበጣ በስምንት ክልሎች 235 ወረዳዎችን ማዳረሱንና ሰፊ ጉዳት ማስከተሉን ጠቅሰው፥ የራሳችን የኬሚካል ርጭት አውሮፕላን ባለመኖሩ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራውም ሶስት ዓመት መውሰዱን ተናግረዋል።
በኪራይ ለመጡ አውሮፕላኖችና ለኬሚካል ርጭት 13 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን አውስተው፥ አሁን ላይ በ850 ሚሊዮን ብር 5 ኤር ትራክተሮችን በመግዛት ሀገራዊ አቅም መፈጠሩን ገልጸዋል።
ይህም ተጋላጭነትን ለመቀነስ፣ አደጋ ሲፈጠርም ፈጣን ምላሽ ለመስጠትና ለሌሎች ተቋማትና ሀገራት እንድንደርስ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ሀገር በቀሉ ናሽናል ኤርዌይስ ኤር ትራክተሮቹን የማስተዳደር ስራውን በጨረታ መረከቡን ጠቅሰዋል።
ከመደበኛ ስራቸው በተጓዳኝ ለሰፋፊ የንግድ እርሻ ልማት የኬሚካል ርጭት፣ ለእሳት አደጋና ሌሎችም ስራዎች በኪራይ ጥቅም ላይ ውለው ከፍተኛ ገቢ እንዲያስገኙ የሚያደርግ ስራ መጀመሩንም ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ለአብነትም ከኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽንና ከኦሮሚያ ምርጥ ዘር ድርጅት ጋር አውሮፕላኖቹን ለርጭት መጠቀም የሚያስችል ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል።
ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በ850 ሚሊዮን ብር የተገዙ አምስት ዘመናዊ የርጭት አውሮፕላኖች (ኤር ትራክተርስ) በይፋ ስራ አስጀምረዋል።
ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም የበረሃ አንበጣ ወረርሽኝና ሌሎች አደጋዎችን ለመቆጣጠር የራሷ የኬሚካል ርጭት አውሮፕላኖች ስላልነበራት ለኪራይ እስከ 13 ቢሊየን ብር ወጪ ስታደርግ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በራሷ አቅም የአደጋ መቆጣጠሪያ የኬሚካል ርጭት አውሮፕላኖች እንዲኖራት ይደረጋል ማለታቸው ይታወሳል።
ይህን ተከትሎም መንግሥት አምስት ዘመናዊ የኬሚካል ርጭትን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ዘመናዊ ኤር ትራክተሮችን ግዥ ፈጽሞ በዛሬው ዕለት በይፋ ስራ አስጀምሯል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በዚህ ወቅት፥ ከዚህ ቀደም የአንበጣ ወረርሽኝ፣ የደን ቃጠሎና የግሪሳ ወፍን መቆጣጠር የሚያስችል ሀገራዊ አቅም ባለመኖሩ በሰው ኃይል በባህላዊ መንገድ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል ብለዋል።
በሰሜን ተራሮችና በባሌ ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ቃጠሎ ባጋጠመ ጊዜ ኢትዮጵያ በልመና እና በኪራይ ከሌሎች አገራት የርጭት አውሮፕላኖችን በማምጣት ስትጠቀም መቆየቷን አውስተዋል።
አሁን ላይ መንግስት አደጋን በራስ የመቋቋምና ፈጣን ምላሽ የመስጠት አካል ያደረገውን የአምስት ኤር ትራክተሮች ( የርጭት አውሮፕላኖችን) ገዝቶ ወደ ስራ ማስገባቱንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ የኤር ትራክተር ባለቤት መሆኗ የጸረ አረምና ጸረ ተባይ የኬሚካል ርጭትን፣ የበረሃ አንበጣ መከላከልን፣ የስንዴና መሰል ሰብሎች የዋግ በሽታን ለመከላከል ትልቅ ሀገራዊ አቅም መሆኑን ገልጸዋል።
አውሮፕላኖቹ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙና ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የመስጠት አቅም ያላቸው በመሆናቸው እንደ እሳት ያሉ እና ሎሎች የተፈጥሮ አደጋዎች በፍጥነት ምላሽ መስጠት እንደሚያስችሉም አንስተዋል።
አውሮፕላኖቹ ከኢትዮጵያ ባለፈም ለጎረቤት ሀገርና ለሌሎችም ጥቅም መስጠት የሚችሉ ናቸው ብለዋል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እውቀትና ቴክኖሎጂ የግብርና መር ስራን ለመተግበር በሂደት ላይ መሆኗን አንስተዋል።
ከ2011 ሰኔ ወር ጀምሮ የተከሰተው የበረሃ አንበጣ በስምንት ክልሎች 235 ወረዳዎችን ማዳረሱንና ሰፊ ጉዳት ማስከተሉን ጠቅሰው፥ የራሳችን የኬሚካል ርጭት አውሮፕላን ባለመኖሩ የመከላከልና የመቆጣጠር ስራውም ሶስት ዓመት መውሰዱን ተናግረዋል።
በኪራይ ለመጡ አውሮፕላኖችና ለኬሚካል ርጭት 13 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን አውስተው፥ አሁን ላይ በ850 ሚሊዮን ብር 5 ኤር ትራክተሮችን በመግዛት ሀገራዊ አቅም መፈጠሩን ገልጸዋል።
ይህም ተጋላጭነትን ለመቀነስ፣ አደጋ ሲፈጠርም ፈጣን ምላሽ ለመስጠትና ለሌሎች ተቋማትና ሀገራት እንድንደርስ የሚያስችል ነው ብለዋል።
ሀገር በቀሉ ናሽናል ኤርዌይስ ኤር ትራክተሮቹን የማስተዳደር ስራውን በጨረታ መረከቡን ጠቅሰዋል።
ከመደበኛ ስራቸው በተጓዳኝ ለሰፋፊ የንግድ እርሻ ልማት የኬሚካል ርጭት፣ ለእሳት አደጋና ሌሎችም ስራዎች በኪራይ ጥቅም ላይ ውለው ከፍተኛ ገቢ እንዲያስገኙ የሚያደርግ ስራ መጀመሩንም ገልጸዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
ለአብነትም ከኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽንና ከኦሮሚያ ምርጥ ዘር ድርጅት ጋር አውሮፕላኖቹን ለርጭት መጠቀም የሚያስችል ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል።
ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓም
የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት‼️
እንኳን ለዒድ አል አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
ኢድ አል አድሃ (አረፋ)በሙስሊም ማኅበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ክብር ያለው በዓል ነው። ዐቅሙና ሁኔታው የፈቀደላቸው ምዕመናን የሐጅ ሥነ ሥርዓትን በመፈጸም ያከብሩታል። ሌሎች ደግሞ በየሀገራቸው በጋራ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ በጸሎት፣ በመደጋገፍና በአብሮነት ያከብሩታል። በሀገራችንም ሙስሊሞች በዓሉን በጸሎት፣ ማዕድን በማጋራት እንዲሁም በደስታ በፍቅር ተጋግዘው ሲያሳልፉ እየያን አድገናል። አብረንም አክብረናል።
የዘንድሮ በዓል ሲከበር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በመጠየቅና በመደገፍ እንዲሁም ዐቅመ ደካሞችን በመንከባከብ እንደሚሆን አምናለሁ።
በዚሁ አጋጣሚ የሀገራችን ሙስሊም ማኅበረሰብ የመደጋገፍ ባህል ከተረጂነት ለመላቀቅ ለምናደርገው ትግል ወሳኝ ዕሴት ነው። እርስ በእርሳችን በመደጋገፍ በተረጂነት ከመታወቅ መውጣት አለብን። ለዚህ ደግሞ በበዓል ጊዜ የምናደርገውን መደጋገፍ የዘወትር ተግባር ማድረግ ነው።
እንደ ሀገር ላለፍንባቸው ችግሮቻችን መፍትሔ የሆነው የሽግግር ፍትሕ እና መፃዒ አብሮነታችንን ለማጎልበት ወሳኝ ለሆነው የሀገራዊ የምክክር ውጤታማነት ሙስሊሙ ማኅበረሰብ የበኩሉን ሀገራዊ ኃላፊነት እንዲወጣ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ። በድጋሚ እንኳን ለኢድ አል አድሃ (አረፋ)በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ፣ በዓሉ የሰላም የፍቅር የደስታ የአንድነት በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓም
እንኳን ለዒድ አል አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
ኢድ አል አድሃ (አረፋ)በሙስሊም ማኅበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ክብር ያለው በዓል ነው። ዐቅሙና ሁኔታው የፈቀደላቸው ምዕመናን የሐጅ ሥነ ሥርዓትን በመፈጸም ያከብሩታል። ሌሎች ደግሞ በየሀገራቸው በጋራ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ በጸሎት፣ በመደጋገፍና በአብሮነት ያከብሩታል። በሀገራችንም ሙስሊሞች በዓሉን በጸሎት፣ ማዕድን በማጋራት እንዲሁም በደስታ በፍቅር ተጋግዘው ሲያሳልፉ እየያን አድገናል። አብረንም አክብረናል።
የዘንድሮ በዓል ሲከበር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በመጠየቅና በመደገፍ እንዲሁም ዐቅመ ደካሞችን በመንከባከብ እንደሚሆን አምናለሁ።
በዚሁ አጋጣሚ የሀገራችን ሙስሊም ማኅበረሰብ የመደጋገፍ ባህል ከተረጂነት ለመላቀቅ ለምናደርገው ትግል ወሳኝ ዕሴት ነው። እርስ በእርሳችን በመደጋገፍ በተረጂነት ከመታወቅ መውጣት አለብን። ለዚህ ደግሞ በበዓል ጊዜ የምናደርገውን መደጋገፍ የዘወትር ተግባር ማድረግ ነው።
እንደ ሀገር ላለፍንባቸው ችግሮቻችን መፍትሔ የሆነው የሽግግር ፍትሕ እና መፃዒ አብሮነታችንን ለማጎልበት ወሳኝ ለሆነው የሀገራዊ የምክክር ውጤታማነት ሙስሊሙ ማኅበረሰብ የበኩሉን ሀገራዊ ኃላፊነት እንዲወጣ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ። በድጋሚ እንኳን ለኢድ አል አድሃ (አረፋ)በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ፣ በዓሉ የሰላም የፍቅር የደስታ የአንድነት በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ሰኔ 8 ቀን 2016 ዓም
በአቶ አደም ፋራህ የተመራ የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ሩሲያ ቭላዲቮስቶክ ገባ
******************
(ኢ ፕ ድ)
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ የልዑክ ቡድን ሩሲያ ቭላዲቮስቶክ ከተማ ገብቷል።
የልኡክ ቡድኑ በብሪክስ ሃገራት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዓለም አቀፍ ፎረም ላይ ይሳተፋል።
ከሰኔ 9 እስከ 12/2016 በሚካሔደውና ዎርልድ ማጆሪቲ ፎር መልቲፖላር ኦርደር በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ፎረም ላይ አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ፣ በብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ ዶክተር ሰማ ጥሩነህ ይሳተፋሉ።
የልኡክ ቡድኑ ከፎረሙ ጎን ለጎን የብሪክስ አባል ሃገራት ከሆኑ አቻ የፓርቲ አመራሮች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚካሔድም የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።
ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም
******************
(ኢ ፕ ድ)
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ የልዑክ ቡድን ሩሲያ ቭላዲቮስቶክ ከተማ ገብቷል።
የልኡክ ቡድኑ በብሪክስ ሃገራት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዓለም አቀፍ ፎረም ላይ ይሳተፋል።
ከሰኔ 9 እስከ 12/2016 በሚካሔደውና ዎርልድ ማጆሪቲ ፎር መልቲፖላር ኦርደር በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ፎረም ላይ አቶ አደም ፋራህን ጨምሮ በብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ፣ በብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ ዶክተር ሰማ ጥሩነህ ይሳተፋሉ።
የልኡክ ቡድኑ ከፎረሙ ጎን ለጎን የብሪክስ አባል ሃገራት ከሆኑ አቻ የፓርቲ አመራሮች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚካሔድም የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።
ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም