የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ
********************
(ኢ ፕ ድ)
የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሰታወቁት የአውሮፕላን ማረፊያው ተገንብቶ አገልግሎት መጀመር በአካባቢው የሚገኘውን የተፈጥሮ ጸጋ በተሻለ ለማልማት እና የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማስፋት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡
አካባቢው ያለውን የቱሪዝም ሀብት ጥቅም ላይ ለማዋል፣ የሕዝቦችን ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ለማቀላጠፍ ብሎም በአጠቃላይ የሕዝቡን ሕይወት ለመቀየር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡
በበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አወሉ አብዲ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ የተገነባ የሚገኘው የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የረጅም ዓመታት ጥያቄያቸውን የመለሰ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች መናገራቸውን ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓም
********************
(ኢ ፕ ድ)
የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሰታወቁት የአውሮፕላን ማረፊያው ተገንብቶ አገልግሎት መጀመር በአካባቢው የሚገኘውን የተፈጥሮ ጸጋ በተሻለ ለማልማት እና የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማስፋት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡
አካባቢው ያለውን የቱሪዝም ሀብት ጥቅም ላይ ለማዋል፣ የሕዝቦችን ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ለማቀላጠፍ ብሎም በአጠቃላይ የሕዝቡን ሕይወት ለመቀየር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡
በበረራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አወሉ አብዲ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ የተገነባ የሚገኘው የነቀምቴ ጉዲና ቱምሳ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የረጅም ዓመታት ጥያቄያቸውን የመለሰ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች መናገራቸውን ከኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የማኀበራዊ የትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓም
ኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍን ለኃይል አማራጭነት ለመጠቀም እየሠራች ነው
********
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የሚገኙ ዋና ዋና ማዕድናትን ለኃይል አማራጭነት በማዋል የካርበን ልቀትን ለመቀነስ እየሰራች ነው ሲል የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።
የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማትዮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍን ለኃይል አማራጭነት በመጠቀም የካርበን ልቀትን ለመቀነስ እየሰራች ትገኛለች።
ኮፐር፣ ኒኬል፣ ኮባልት፣ ሊቲየም እንዲሁም ሌሎች ውድና ለኃይል አማራጭ የሚሆኑ የማዕድን ዓይነቶች በኢትዮጵያ የሚገኙ ስለመሆኑ በተለያዩ መንገዶች መረጋገጡን ያመላከቱት አቶ ሚሊዮን፤ ይህም ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የደረሰውን የካርበን ልቀት ለመቀነስ......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130092
********
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የሚገኙ ዋና ዋና ማዕድናትን ለኃይል አማራጭነት በማዋል የካርበን ልቀትን ለመቀነስ እየሰራች ነው ሲል የማዕድን ሚኒስቴር አስታወቀ።
የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማትዮስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍን ለኃይል አማራጭነት በመጠቀም የካርበን ልቀትን ለመቀነስ እየሰራች ትገኛለች።
ኮፐር፣ ኒኬል፣ ኮባልት፣ ሊቲየም እንዲሁም ሌሎች ውድና ለኃይል አማራጭ የሚሆኑ የማዕድን ዓይነቶች በኢትዮጵያ የሚገኙ ስለመሆኑ በተለያዩ መንገዶች መረጋገጡን ያመላከቱት አቶ ሚሊዮን፤ ይህም ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የደረሰውን የካርበን ልቀት ለመቀነስ......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130092
ስምንት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን አርሶ አደሮች ኩታ ገጠም ግብርናን እየተገበሩ ነው
***
(ኢ ፕ ድ)
ስምንት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን የሚሆኑ አርሶ አደሮች ማሳቸውን በኩታ ገጠም እያለሙ መሆኑን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ገለጸ።
የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሤ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ ኩታ ገጠም እርሻን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው።
በዚህም አርሶ አደሮች በ11 ሰብሎች በኩታ ገጠም እየሠሩ ነው ያሉት ዶክተር ማደፍሮ፤ ከነዚህ ውስጥ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ጤፍ፣ ሰሊጥ፣ አኩሪ አተርና የቢራ ገብስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከፍራፍሬም አቮካዶ፣ ማንጎ እና ሙዝ እንዲሁም ከአትክልት ቲማቲም እና ሽንኩርት በኩታ ገጠም እየለሙ መሆኑን ተናግረዋል።
የኩታ ገጠም እርሻን የማልማት ሂደት አርሶ አደሮች በተመሳሳይ ጊዜ የማረስ፣ ዘር የመዝራት፣ የግብርና ምርትን የሚያሳድጉ ግብዓቶችን በጋራ የመጠቀም እድል የሚፈጥር......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130089
***
(ኢ ፕ ድ)
ስምንት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን የሚሆኑ አርሶ አደሮች ማሳቸውን በኩታ ገጠም እያለሙ መሆኑን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ገለጸ።
የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሤ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ ኢንስቲትዩቱ ኩታ ገጠም እርሻን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው።
በዚህም አርሶ አደሮች በ11 ሰብሎች በኩታ ገጠም እየሠሩ ነው ያሉት ዶክተር ማደፍሮ፤ ከነዚህ ውስጥ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ጤፍ፣ ሰሊጥ፣ አኩሪ አተርና የቢራ ገብስ ተጠቃሽ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከፍራፍሬም አቮካዶ፣ ማንጎ እና ሙዝ እንዲሁም ከአትክልት ቲማቲም እና ሽንኩርት በኩታ ገጠም እየለሙ መሆኑን ተናግረዋል።
የኩታ ገጠም እርሻን የማልማት ሂደት አርሶ አደሮች በተመሳሳይ ጊዜ የማረስ፣ ዘር የመዝራት፣ የግብርና ምርትን የሚያሳድጉ ግብዓቶችን በጋራ የመጠቀም እድል የሚፈጥር......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130089
በግንቦት ወር ከቡና የወጪ ንግድ ከ209 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል
*******
(ኢ ፕ ድ)
በግንቦት ወር 43 ሺህ 481 ቶን በላይ ቡና በመላክ 209 ነጥብ 54 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የቡናና ሻይ ባለስልጣን ገለጸ።
የቡናና ሻይ ባለስልጣን የሕዝብ ግንኙነትና የኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሳህለማርያም ገብረመድህን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት በግንቦት ወር ብቻ 43 ሺህ 481 ቶን ቡና በመላክ 209 ነጥብ 54 ሚሊዮን ዶላር ተገኝቷል።
በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ውስጥም በአጠቃላይ 252 ሺህ 466 ነጥብ 98 ቶን የቡና ምርት በመላክ አንድ ቢሊዮን 208 ሚሊዮን 73 ሺህ ዶላር ተገኝቷል።
ይህ ውጤት ካለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ወደ ውጭ ከተላከው ምርት እጅግ ከፍተኛ ውጤት የታየበት ነውም ብለዋል።ለውጤቱ መገኘት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የጎላ ድርሻ ያለው መሆኑን ጠቅሰው፤ ቡናን ከሚያለማው አርሶ አደር ጀምሮ ቡና አቅራቢና ላኪዎች.......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130099
*******
(ኢ ፕ ድ)
በግንቦት ወር 43 ሺህ 481 ቶን በላይ ቡና በመላክ 209 ነጥብ 54 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የቡናና ሻይ ባለስልጣን ገለጸ።
የቡናና ሻይ ባለስልጣን የሕዝብ ግንኙነትና የኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሳህለማርያም ገብረመድህን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት በግንቦት ወር ብቻ 43 ሺህ 481 ቶን ቡና በመላክ 209 ነጥብ 54 ሚሊዮን ዶላር ተገኝቷል።
በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ውስጥም በአጠቃላይ 252 ሺህ 466 ነጥብ 98 ቶን የቡና ምርት በመላክ አንድ ቢሊዮን 208 ሚሊዮን 73 ሺህ ዶላር ተገኝቷል።
ይህ ውጤት ካለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት ተመሳሳይ ወቅት ወደ ውጭ ከተላከው ምርት እጅግ ከፍተኛ ውጤት የታየበት ነውም ብለዋል።ለውጤቱ መገኘት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ከፍተኛ ትኩረት የጎላ ድርሻ ያለው መሆኑን ጠቅሰው፤ ቡናን ከሚያለማው አርሶ አደር ጀምሮ ቡና አቅራቢና ላኪዎች.......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130099
"የቦረና ዳልጋ የከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል በሙሉ አቅሙ እየሰራ ነው" - የቦረና ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት
**
(ኢ ፕ ድ)
በዞኑ ተከስቶ በነበረው ድርቅ ምክንያት ተጎድቶ የነበረው የቦረና ዳልጋ ከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል በሙሉ አቅሙ እየሰራ መሆኑን የቦረና ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የኦሮሚያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ጨምሮ ሌሎች የቢሮው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን የሚገኘው የዳልጋ ከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል ጎብኝተዋል።
የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጃለላ ዱለቻ እንደገለጹት፤ የቦረና ዳልጋ ከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል የሚያስፈልገው ግብዓት አሟልቶ በሙሉ አቅሙ እየሰራ ነው።
ማዕከሉ በቀጣይ ዝርያዎቹን ለአርብቶ አደሩ ለማከፋፈል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የቦረና ዳልጋ የከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል ኃላፊ ተወካይ ዲዳ ኮንሶ በበኩላቸው ድርቁ በተከሰተበት ወቅት 200 የነበረው አሁን ከ450 በላይ ማሳደግ ተችሏል።
በልጅዓለም ፍቅሬ(ቦረና ዞን)
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም
**
(ኢ ፕ ድ)
በዞኑ ተከስቶ በነበረው ድርቅ ምክንያት ተጎድቶ የነበረው የቦረና ዳልጋ ከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል በሙሉ አቅሙ እየሰራ መሆኑን የቦረና ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የኦሮሚያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ጨምሮ ሌሎች የቢሮው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን የሚገኘው የዳልጋ ከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል ጎብኝተዋል።
የግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጃለላ ዱለቻ እንደገለጹት፤ የቦረና ዳልጋ ከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል የሚያስፈልገው ግብዓት አሟልቶ በሙሉ አቅሙ እየሰራ ነው።
ማዕከሉ በቀጣይ ዝርያዎቹን ለአርብቶ አደሩ ለማከፋፈል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የቦረና ዳልጋ የከብቶች ዝርያ ማሻሻያና ማራቢያ ማዕከል ኃላፊ ተወካይ ዲዳ ኮንሶ በበኩላቸው ድርቁ በተከሰተበት ወቅት 200 የነበረው አሁን ከ450 በላይ ማሳደግ ተችሏል።
በልጅዓለም ፍቅሬ(ቦረና ዞን)
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ከኢፕድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ካነሷቸው ሀሳቦች‼️
👉 ገና በጥናት ያልተደረሰባቸውን ሳይጨምር፣ ክልላችን ከሁሉም በበለጠ በማዕድን ሀብት የበለፀገ ክልል ነው፣
👉 በ2014 ዓም ሁለት ሺህ 300 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል፤
👉 ካማሽ ዞን ላይ የድንጋይ ከሰል ማምረት ተጀምሯል፣
👉 ሌላው የማእድን ሀብት እጣን ነው፣ ወጣቶች አንድ ኩንታል እጣን 40 ሺህ ብር በመሸጥና ተጠቃሚ ሆነዋል፣
👉 ከለውጡ በፊት ከ700 ሺህ ሄክታር በላይ አምርቶ አያውቅም ፣ ከለውጡ በኋላ ግን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሄክታር መሬት በአርሶ አደር ብቻ ለምቷል፣
👉በተለያዩ ዘርፎች ከ900 በላይ ባለሀብቶች ፍቃድ ወስደው ወደ ሥራ በመግባት ላይ ይገኛሉ፤
👉 በተለያዩ ዘርፎች ከ34 ሺህ በላይ የሥራ እድል ተፈጥሮ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፣
👉 11 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች አሉ፤ ሰባቱ አነስተኛ የመሰኖ ፕሮጀክቶች ናቸው፣
👉 አምስት የመጀመሪያ ደረጃ (ፕራይመሪ) ሆስፒታሎች ተገንብተዋል፣
👉 የሰላም ችግሮቻችንን ሙሉ ለሙሉ ካስወገድን በጥቂት ዓመታት የፈለግነው የብልፅግና ምእራፍ ላይ እንደርሳለን፣
👉 ባለፉት ስድስት ዓመታት ውስጥ በክልላችን የተመዘገበው ትርጉም ያለው ለውጥ ነው፡
👉 ከለውጡ በኋላ ግን ወደ ላይ ተስቦ የተወሰደው መሬትና የመሬት ጉዳይ ወደ ክልሉ እንዲመለስ ተደርጎ ለባለሀብቶች በመሰጠቱ ምክንያት በርካታ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል
👉 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሕዝብ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል አስተሳሰብና ማንነትን ያዳበረው ገና አሁን ነው፣
👉 እራሱን በራሱ በትክክል ማስተዳደር የጀመረው ከለውጥ በኋላ ነው፣
ዝርዝር መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130127
👉 ገና በጥናት ያልተደረሰባቸውን ሳይጨምር፣ ክልላችን ከሁሉም በበለጠ በማዕድን ሀብት የበለፀገ ክልል ነው፣
👉 በ2014 ዓም ሁለት ሺህ 300 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል፤
👉 ካማሽ ዞን ላይ የድንጋይ ከሰል ማምረት ተጀምሯል፣
👉 ሌላው የማእድን ሀብት እጣን ነው፣ ወጣቶች አንድ ኩንታል እጣን 40 ሺህ ብር በመሸጥና ተጠቃሚ ሆነዋል፣
👉 ከለውጡ በፊት ከ700 ሺህ ሄክታር በላይ አምርቶ አያውቅም ፣ ከለውጡ በኋላ ግን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሄክታር መሬት በአርሶ አደር ብቻ ለምቷል፣
👉በተለያዩ ዘርፎች ከ900 በላይ ባለሀብቶች ፍቃድ ወስደው ወደ ሥራ በመግባት ላይ ይገኛሉ፤
👉 በተለያዩ ዘርፎች ከ34 ሺህ በላይ የሥራ እድል ተፈጥሮ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፣
👉 11 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች አሉ፤ ሰባቱ አነስተኛ የመሰኖ ፕሮጀክቶች ናቸው፣
👉 አምስት የመጀመሪያ ደረጃ (ፕራይመሪ) ሆስፒታሎች ተገንብተዋል፣
👉 የሰላም ችግሮቻችንን ሙሉ ለሙሉ ካስወገድን በጥቂት ዓመታት የፈለግነው የብልፅግና ምእራፍ ላይ እንደርሳለን፣
👉 ባለፉት ስድስት ዓመታት ውስጥ በክልላችን የተመዘገበው ትርጉም ያለው ለውጥ ነው፡
👉 ከለውጡ በኋላ ግን ወደ ላይ ተስቦ የተወሰደው መሬትና የመሬት ጉዳይ ወደ ክልሉ እንዲመለስ ተደርጎ ለባለሀብቶች በመሰጠቱ ምክንያት በርካታ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል
👉 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሕዝብ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል አስተሳሰብና ማንነትን ያዳበረው ገና አሁን ነው፣
👉 እራሱን በራሱ በትክክል ማስተዳደር የጀመረው ከለውጥ በኋላ ነው፣
ዝርዝር መረጃውን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130127
በከተማዋ የሚገኙ 35 ትምህርት ቤቶች ለ2017 የትምህርት ዘመን ምዝገባ እንዳያካሂዱ ዕገዳ ተጣለ
*******
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ የሚገኙ 35 የቅድመ አንደኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለ2017 የትምህርት ዘመን ምዝገባ እንዳያካሂዱ ማገዱን የአዲስ አበባ ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሰታወቀ።
ለ2017 የትምህርት ዘመን የሚቀጥሉና የማይቀጥሉ የትምህርት ተቋማትንም ይፋ አድርጓል።
የአዲስ አበባ ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዳኛዉ ገብሩ እንደገለጹት፣ ለ2017 የትምህርት ዘመን ባደረገዉ ቁጥጥር የፖሊሲ ጥሰት የፈጸሙና የትምህርት መመሪያዎችን ያላሟሉ 35 የቅድመ አንደኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግል ይዞታ ያላቸዉ ትምህርት ቤቶች ላይ እገዳ ጥሏል።
ከእነዚህ ትምህርት ቤቶች መካከልም የካ፣ ልደታ ጉለሌና ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ የሚገኙ የጊብሰን ትምህርት ቤቶች፣የቅዱስ ሚካኤል አምስት ትምህርት ቤቶች፣ የካ አፖሎ ትምህርት ቤት ይገኙበታል።
የቅዱስ ሚካኤል ትምህርት ቤቶች የስያሜ ለዉጥ በማድረግ ለመቀጠል በመጠየቁም ጉዳዩ እየታየ መሆኑ ተገልጿል።
ዕገዳ በተጣለባቸዉ ትምህር ቤቶች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በመኖረያ አቅሪያቢያቸዉ በሚገኙ የግልና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ እንዲስተናግዱ ይደረጋል ብለዋል።
በተጨማሪም የተዘጉት ትምህርት ቤቶችም የተሟላ የተማሪዎችን ማስረጃ እንዲሰጡ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
መስከረም ሰይፉ
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ የሚገኙ 35 የቅድመ አንደኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለ2017 የትምህርት ዘመን ምዝገባ እንዳያካሂዱ ማገዱን የአዲስ አበባ ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሰታወቀ።
ለ2017 የትምህርት ዘመን የሚቀጥሉና የማይቀጥሉ የትምህርት ተቋማትንም ይፋ አድርጓል።
የአዲስ አበባ ትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ዳኛዉ ገብሩ እንደገለጹት፣ ለ2017 የትምህርት ዘመን ባደረገዉ ቁጥጥር የፖሊሲ ጥሰት የፈጸሙና የትምህርት መመሪያዎችን ያላሟሉ 35 የቅድመ አንደኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግል ይዞታ ያላቸዉ ትምህርት ቤቶች ላይ እገዳ ጥሏል።
ከእነዚህ ትምህርት ቤቶች መካከልም የካ፣ ልደታ ጉለሌና ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ የሚገኙ የጊብሰን ትምህርት ቤቶች፣የቅዱስ ሚካኤል አምስት ትምህርት ቤቶች፣ የካ አፖሎ ትምህርት ቤት ይገኙበታል።
የቅዱስ ሚካኤል ትምህርት ቤቶች የስያሜ ለዉጥ በማድረግ ለመቀጠል በመጠየቁም ጉዳዩ እየታየ መሆኑ ተገልጿል።
ዕገዳ በተጣለባቸዉ ትምህር ቤቶች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በመኖረያ አቅሪያቢያቸዉ በሚገኙ የግልና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ እንዲስተናግዱ ይደረጋል ብለዋል።
በተጨማሪም የተዘጉት ትምህርት ቤቶችም የተሟላ የተማሪዎችን ማስረጃ እንዲሰጡ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
መስከረም ሰይፉ
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም
አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከተባበሩት መንግስት ድርጅት ጠቅላይ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
****
(ኢ ፕ ድ)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስት ድርጅት ጠቅላይ ጉባኤ ፕሬዚዳንት አምባሳደር ዴኒስ ፍራንሲስን ጋር በአለም አቀፍና በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያና ተመድ አብረው በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች፣ በአለም አቀፍና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ በሰጡት ማብራሪያ ገልጸዋል።
በአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ የሀሳብ ልውውጥ ማድረጋቸውን የገለጹት አምባሳደር ነብዩ፣ ኢትዮጵያ ለቀጣናው መረጋጋት የምታደርገውን ጥረት በተመለከት አድናቆት ችረዋል ብለዋል።
አምባሳደር ዴኒስ ለታዳጊ የሀገራት አጀንዳዎች በተለይ የእዳ ቅነሳና ሽግሽግ፣ የዘላቂ ልማት አፈጻጸም ላይ ለሰጡት ትኩረት አምባሳደር ታዬ ምስጋና ማቅረባቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ትኩረት ሰጥታ እንደምትሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ለተባበሩት መንግስት ድርጅት ጠቅላይ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ማረጋገጫ መስጠታቸውን ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል።
በውይይቱ ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለችውን የፖለቲካና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን በተመለተከተ ገለጻ ተድርጎላቸዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የተባበሩት መንግስት ድርጅት ጠቅላይ ጉባኤ ፕሬዚዳንት አምባሳደር ዴኒስ ፍራንሲስን ጋር በአለም አቀፍና በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት ኢትዮጵያና ተመድ አብረው በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች፣ በአለም አቀፍና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ በሰጡት ማብራሪያ ገልጸዋል።
በአፍሪካ ቀንድ ጉዳይ የሀሳብ ልውውጥ ማድረጋቸውን የገለጹት አምባሳደር ነብዩ፣ ኢትዮጵያ ለቀጣናው መረጋጋት የምታደርገውን ጥረት በተመለከት አድናቆት ችረዋል ብለዋል።
አምባሳደር ዴኒስ ለታዳጊ የሀገራት አጀንዳዎች በተለይ የእዳ ቅነሳና ሽግሽግ፣ የዘላቂ ልማት አፈጻጸም ላይ ለሰጡት ትኩረት አምባሳደር ታዬ ምስጋና ማቅረባቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ ትኩረት ሰጥታ እንደምትሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ ለተባበሩት መንግስት ድርጅት ጠቅላይ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ማረጋገጫ መስጠታቸውን ቃል አቀባዩ ጠቅሰዋል።
በውይይቱ ኢትዮጵያ እያከናወነች ያለችውን የፖለቲካና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን በተመለተከተ ገለጻ ተድርጎላቸዋል።
በሞገስ ጸጋዬ
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም
የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት‼️
የታላቁ ህዳሴ ግድብ መገኛ፣ የንጉስ ሼህ ሆጀሌ ሀገር፣ የወርቋ ምድር ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ገብተናል። በቆይታችንም በክልሉ የሚገኙ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን የምንጎበኝ ይሆናል፡፡ በአሶሳ አውሮፕላን ማረፊያ የሞቀ አቀባበል ላደረጉልን የክልሉ ፕሬዝደንት እና ካቢኒያቸው እንዲሁም የአሶሳ ከተማ ህዝብ ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም
የታላቁ ህዳሴ ግድብ መገኛ፣ የንጉስ ሼህ ሆጀሌ ሀገር፣ የወርቋ ምድር ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ገብተናል። በቆይታችንም በክልሉ የሚገኙ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን የምንጎበኝ ይሆናል፡፡ በአሶሳ አውሮፕላን ማረፊያ የሞቀ አቀባበል ላደረጉልን የክልሉ ፕሬዝደንት እና ካቢኒያቸው እንዲሁም የአሶሳ ከተማ ህዝብ ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።
ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓም