Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.8K subscribers
40K photos
304 videos
7 files
5.76K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተዋል
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ለ2016/17 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የአረንጓዴ አሻራ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች መዘጋጀታቸውን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በአንድ ጀንበር 150 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዕቅድ መያዙም ተመላክቷል፡፡

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢያሱ ኤልያስ (ፕ/ር) ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ለ2016/17 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ ስድስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞችን በማዘጋጀት ከእቅድ በላይ ማከናወን ተችሏል፡፡

አጠቃላይ ከተዘጋጁት ሰባት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኞች መካከል 56 በመቶ የሚሆኑት ብዝሀ ጥቅም ያላቸው የፍራፍሬና የማገዶ ችግኞች ሲሆኑ፤ 44 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ የአካባቢ ጥበቃና የደን ሽፋንን የሚጨምሩ ችግኞች መሆናቸውን.......

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130384
ቴክኒክና ሙያ – የኢኮኖሚ ዕድገት ሞተር
******************
(ኢ ፕ ድ)
ቴክኒክና ሙያ የአዕምሮና እጅ ጥበብ ውጤቶች የሚፈልቁበት ዘርፍ ነው፡፡

ይህን ዘርፍ የሀገርን ኢኮኖሚ በተገቢው ልክ እንዲደግፍ ለማስቻል የተለያዩ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡

ዜጎችን በተለያየ መስክ የሙያ ባለቤት እና የፈጠራ ምንጭ ያደረገ የስልጠና ዘርፍ እንደመሆኑ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ የዕድገት ሞተር ለማድረግ የተሠሩ ሥራዎችን መዳሰስ ተገቢ ይሆናል፡፡

የቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) የስልጠና ዘርፉ ለአንድ ሀገር ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወት፤ ለኢንዱስትሪው መስክ ደግሞ ቀኝ እጅ ነው ይላሉ፡፡

ዘርፉ የሚያፈራው የሰው ኃይል ከኢንዱስትሪው ጋር ቀጥታ ግንኙነት እያለው እንኳን ይህን ሚናውን ያገናዘበ ትኩረት ሲሰጠው አልነበረም ባይ ናቸው፡፡

የመንግሥት ትኩረት በተለያዩ ጊዜያት እየተሻሻለ መምጣቱን የሚገልጹት ዳይሬክተሩ፤ በተለይ ከጣሊያን ወረራ ወዲህ ተግባረ ዕድ የቴክኒክ ትምህርት ቤት 1942 ላይ እንዲከፈት መደረጉን ይናገራሉ። ከትምህርት ቤቱ መቋቋም በኋላ ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130385
1
ወደ ውጭ በሚላኩ የግብርና ምርቶች ላይ ዘመናዊ የቁጥጥርና ደህንነት ሥርዓት እየተገነባ ነው
***************
(ኢ ፕ ድ)
ወደ ውጭ በሚላኩ የግብርና ምርቶች ላይ ዘመናዊ የቁጥጥርና ደህንነት ሥርዓት እየተገነባ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

በኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር አምራችና ላኪዎች ማህበር እና በኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የተዘጋጀው የግብርና ውጤቶች ቁጥጥርና ደህንነት ላይ ያተኮረ ጉባኤ ትናንት ተካሂዷል፡፡

የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ድሪባ ኩማ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር፤ ባለስልጣኑ ወደ ውጪ የሚላኩና ከውጭ ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ የግብርና ምርቶችን የደህንነትና ቁጥጥር አገልግሎት እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡

እስካሁን የነበረው የአገልግሎት አሰጣጥ በአብዛኛው ወረቀት ላይ የተመሰረተ እንደሆነና አሁን ላይ አገልግሎቱን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር ከአውሮፓ ኅብረትና ከትሬድ ማርክ አፍሪካ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=130447
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሳምንት በነገው ዕለት በኤግዚቢሽን ማዕከል ይከፈታል
*****
(ኢ ፕ ድ)
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሳምንት ነገ በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል እንደሚከፈት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ሥልጠናና የተቋማት ልማት ዘርፍ ሀላፊ ዶክተር አበራ ብሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት:- የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሳምንት የቴክኒክና ሙያ ለዘላቂ ልማት በሚል መሪ ሀሳብ ከሰኔ 15 እስከ 20 ይካሄዳል።

የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሳምንት በነገው ዕለት በኤግዚቢሽን ማዕከል ይከፈታል ያሉት ዶክተር አበራ በከተማው የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች;ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች:የሥራ ፈጠራ ባለቤቶች ወጣቶች ምርትና አገር በቀል ሥራዎች ለእይታ ይቀርባሉ ብለዋል።

ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሳምንቱ ዓላማ በዘርፉ እየተሰሩ ያሉት ተግባራት ለህብረተሰቡ ለማስተዋወቅ የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው በተለይም በማህበረሰቡ ዘንድ በቴክኒክና ሙያ ያለውን ግንዛቤ ከፍ ለማድረግ በየዓመቱ የሚዘጋጅ መርሃግብር መሆኑን ገልጸዋል።

በመርሃግብሩ በርካታ ኮሌጆች ተሳታፊ እንደሚሆኑ በመግለጽ በተለይም ሁሉም የመግስት ኮሌጆች ያመረቷቸውን ምርቶችና ቴክኖሎጂዎች ይዘው የሚቀርቡበት አውደርዕይ መሆኑን ተናግረዋል።

የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሳምንት ለ14 ጊዜ የሚከበር መሆኑን በመግለጽ በኮሌጆች መካከል የተለያዩ የችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ ውድድርና እውቅና እንደሚካሄድ ተናግረዋል።

በተጨማሪም በጋርመንት ሥራዎች ላይ የፋሽን የስፖርት የቴክኖሎጂ ውድድር የተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው ዘርፉ ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲያድግ ድጋፍ ያደረጉ ተቋማት እውቅና እንደሚሰጥ አስረድተዋል።

ሰኔ 20 የማጠቃለያ መርሃግብር እንደሚካሄድ ገልጸው አውደርዕዩን ከ50 ሺህ በላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚጎበኙት ይጠበቃል ብለዋል።

በማርቆስ በላይ
ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓም
በ10 ወራት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች‼️

👉በተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም 7 ነጥብ 88 ሚሊዮን ተማሪዎችን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፣

👉22 ነጥብ 7 ሚሊዮን የሁለተኛ ደረጃ መጽሐፍት ታትመዋል፣

👉ትምህርት ለትውልድ መርሐግብር 5 ሺህ 873 አዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታና 14 ሺህ 791 ትምህርት ቤቶች ጥገና ስራ ተከናዉኗል፣

👉የመውጫ ፈተና አተገባበር ሂደት ፈተናውን ከወሰዱ 97 ሺህ 673 ተማሪዎች ውስጥ 27 ሺህ 035 አልፈዋል፣

👉በ2016ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተናን በወረቀትና በኦንላይን መስጠት የሚቻልበት አቅም ተፈጥሯል፣

👉ከ136 የፌደራል ተቋማት ለ18 ሺህ 326 ሰራተኞች የትምህርት ማስረጃ ትክክለኛነት ተረጋግጧል፣

👉በትርክት ግንባታ የግብረ-ገብ ትምህርት በስርዓተ ትምህርቱ ውስጥ ተካቶ መሰጠት ጀምሯል፣

👉ለጎረቤት ሀገሮች የሚሰጡ የነጻ ትምህርት እድሎችን በማሳደግ በ2016 ዓም 865 ተማሪዎችን እየተማሩ ነው፣

ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓም
አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከተ.መ.ድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሀፊ ጋር ተወያዩ
****************
(ኢ ፕ ድ)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሀፊ ክላቨር ጋቴትን ዛሬ በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ በመጪው ሀምሌ ወር የምታስተናግደው 4ኛዉ ፋይናንስ ለልማት ጉባዔ የቅድመ ዝግጅት ስብሰባ የተሳካ እንዲሆን ለማድረግ በጋራ መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል፡፡

በቀጣይ መስከረም ወር በኒውዮርክ በሚካሄደው የመጭው ዘመን ስብሰባ (Summit of the Future) ላይ ሊኖሩ በሚገባቸው ተሳትፎዎች ዙሪያም የሀሳብ ልውውጥ አድርገዋል።

አፍሪካ አዳራሽ የተሰኘውን የኮሚሽኑ አዳራሽ የእድሳት ስራ በአዲስ አበባ እየተከናወነ ከሚገኘው የኮሪደር ልማትና ከተገነቡት የቱሪስት መዳረሻ ቦታዎች ጋር በማስተሳሰር አዳራሹን አንድ የቱሪስት መስህብ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ተደርጓል።

ኮሚሽኑና ኢትዮጵያ በልማትና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተባብረው መስራት በሚችሉበት አግባብ ላይ መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓም
ኢትዮጵያ ላለፉት አምስት አመታት በ2011 ዓመተ ምህረት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተጠነሰሰው የአረንጓዴ ዓሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት በየአመቱ የችግኝ ተከላ ስራ ስታካሂድ ቆይታለች። ዛሬ የባለፉት አመታት ጥረታችንን በማጤን የ2016ቱን ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ቅድመ ጅማሮ መርሃ ግብር አካሂደናል።

በተካሄደውም የአረንጓዴ ዓሻራ ቅድመ መክፈቻ መርሃ ግብር ሁነት የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ሪፖርት ይፋ ሆኗል። በመቀጠልም የሀገራዊውን የአረንጓዴ አሻራ ይዘት እና የስራ ውጤት በሰዋዊ ተረክ የሚያቀርብ አለምአቀፍ ዘጋቢ ፊልም የምረቃ እይታ ተካሂዷል።

ይፋ የተደረገው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ሪፖርት እንዳመለከተው የደን ሽፋናችን በ2011 ዓመተ ምህረት ከነበረበት 17.2 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ ብሏል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመርሃ ግብሩ ባደረጉት ንግግር ይህን የዕድገት ውጤት ማስቀጠል እንደሚገባ ማሳሰባቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።

ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓም