#ኦሮሚያ
በኦሮሚያ ክልል በ2016 የበጀት ዓመት ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ከ79 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 20 ሺህ 664 ፕሮጀክቶች ለምረቃ ተዘጋጅተዋል።
መንግስት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋትና ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን በተገባደደዉ የበጀት አመት ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል።
ሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓም
በኦሮሚያ ክልል በ2016 የበጀት ዓመት ዘርፈ ብዙ አገልግሎት የሚሰጡ ከ79 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 20 ሺህ 664 ፕሮጀክቶች ለምረቃ ተዘጋጅተዋል።
መንግስት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋትና ተደራሽ የማድረግ ስራዎችን በተገባደደዉ የበጀት አመት ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል።
ሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት‼️
ኩታ ገጠም እርሻ እየተስፋፋ ነው። የዚህ ክረምት የእርሻ ዕቅዳችንን ሊያሳካ የሚችል ሰፊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። እንቅስቃሴውም መጠናከር አለበት። በዚህ ዓመት ከ24 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ለማረስ ዕቅድ አለን። ይሄንን ዕቅድ ለማሳካት ከዝናቡ ጋር መሽቀዳደም አለብን። ኩታ ገጠም ማድረግ አለብን፤ ዘመናዊ መንገድ መከተልም አለብን። ይሄ ጥረት ነው በምግብ ራስን ለመቻል የምናደርገውን ጥረት የሚያሳካው።
ሐምሌ 1ቀን 2016 ዐም
ኩታ ገጠም እርሻ እየተስፋፋ ነው። የዚህ ክረምት የእርሻ ዕቅዳችንን ሊያሳካ የሚችል ሰፊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። እንቅስቃሴውም መጠናከር አለበት። በዚህ ዓመት ከ24 ሚሊዮን ሄክታር በላይ ለማረስ ዕቅድ አለን። ይሄንን ዕቅድ ለማሳካት ከዝናቡ ጋር መሽቀዳደም አለብን። ኩታ ገጠም ማድረግ አለብን፤ ዘመናዊ መንገድ መከተልም አለብን። ይሄ ጥረት ነው በምግብ ራስን ለመቻል የምናደርገውን ጥረት የሚያሳካው።
ሐምሌ 1ቀን 2016 ዐም
የሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል በሀገራቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እየሠራ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ የሚገኘው የሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል በሩሲያና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን የእርስ በእርስ ግንኙነት ለማጠናከር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አሌክሳንደር እቪሲትገንቪ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል በዋናነት የተቋቋመው በሁለቱ ሀገራት መካከል በባህል፣ በቋንቋ፣ በትምህርትና በሌሎችም ዘርፎች ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረን ለማድረግ ነው።
በዚህም ማዕከሉ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በየወቅቱ የሀገራቱን ግንኙነት ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ሊያደርጉ የሚችሉ ኮንሰርቶች፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ሳይንሳዊ ኮንፈረንሶች፣ የሩስያ ቋንቋ ኮርሶችንና የተለያዩ ባህላዊና ትምህርታዊ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ቆይቷል ብለዋል፡፡
ማዕከሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሩሲያ የስኮላርሺፕ ፕሮግራም በማግኘት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ምክንያት እየሆነ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ከዚህ ቀደም በሩሲያ ትምህርታቸውን ይከታተሉ የነበሩ ኢትዮጵያውያን......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131654
****************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ የሚገኘው የሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል በሩሲያና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን የእርስ በእርስ ግንኙነት ለማጠናከር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አሌክሳንደር እቪሲትገንቪ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል በዋናነት የተቋቋመው በሁለቱ ሀገራት መካከል በባህል፣ በቋንቋ፣ በትምህርትና በሌሎችም ዘርፎች ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖረን ለማድረግ ነው።
በዚህም ማዕከሉ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በየወቅቱ የሀገራቱን ግንኙነት ወደተሻለ ደረጃ ከፍ ሊያደርጉ የሚችሉ ኮንሰርቶች፣ ኤግዚቢሽኖች፣ ሳይንሳዊ ኮንፈረንሶች፣ የሩስያ ቋንቋ ኮርሶችንና የተለያዩ ባህላዊና ትምህርታዊ ዝግጅቶችን ሲያከናውን ቆይቷል ብለዋል፡፡
ማዕከሉ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሩሲያ የስኮላርሺፕ ፕሮግራም በማግኘት ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ምክንያት እየሆነ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ከዚህ ቀደም በሩሲያ ትምህርታቸውን ይከታተሉ የነበሩ ኢትዮጵያውያን......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131654
ሰው ሠራሽ አስተውሎት – የነገዋ ኢትዮጵያ አንዱ ተስፋ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ(የሰው ሠራሽ አስተውሎት) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሕይወታችን ውስጥ ያለው ወሳኝ ሚና እየጨመረ ይገኛል፡፡
የሶፍትዌር መሐንዲሶች እንደሚገልጹት የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኮምፒዩተሮችና ማሽኖች እንደ ሰው ልጅ እንዲያመዛዝኑ፤ ነገሮችን እንዲገነዘቡ፤ ማንኛውንም ነገር እንዲማሩ፤ እንዲያቅዱና ፈጠራዎችን እንዲከውኑ በማድረግ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ እንዲያሳኩ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ነው።
ቴክኖሎጂ የራሱ የሆነ አወንታዊና አሉታዊ ተጽዕኖዎች ቢኖሩትም አውንታዊ ጎኑን መረዳትና በአግባቡ መጠቀም ይገባል፡፡
ወጣት ቶማስ ወርቅነህ ይባላል፤ በምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአይ ሲቲ ትምህርት ክፍል የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ ነው፡፡
ወጣቱን ያገኘነው በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው 14ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ የምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን........
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131653
**********************
(ኢ ፕ ድ)
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ(የሰው ሠራሽ አስተውሎት) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሕይወታችን ውስጥ ያለው ወሳኝ ሚና እየጨመረ ይገኛል፡፡
የሶፍትዌር መሐንዲሶች እንደሚገልጹት የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኮምፒዩተሮችና ማሽኖች እንደ ሰው ልጅ እንዲያመዛዝኑ፤ ነገሮችን እንዲገነዘቡ፤ ማንኛውንም ነገር እንዲማሩ፤ እንዲያቅዱና ፈጠራዎችን እንዲከውኑ በማድረግ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ እንዲያሳኩ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ነው።
ቴክኖሎጂ የራሱ የሆነ አወንታዊና አሉታዊ ተጽዕኖዎች ቢኖሩትም አውንታዊ ጎኑን መረዳትና በአግባቡ መጠቀም ይገባል፡፡
ወጣት ቶማስ ወርቅነህ ይባላል፤ በምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአይ ሲቲ ትምህርት ክፍል የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ ነው፡፡
ወጣቱን ያገኘነው በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው 14ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ የምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን........
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131653
ሕዝብና መንግሥትን ያስታረቀው – የዱግና ድልድይ
******************
(ኢ ፕ ድ)
በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን መዋቅር ሥር ከሚገኙ ወረዳዎች፣ ሎካ አባያ ወረዳ አንዱ ነው።
ይህ ወረዳ 23 ቀበሌዎች ያሉት ሲሆን፤ በወረዳው ከሚገኙ ትልልቅ ወንዞች አንዱ የሆነው ግዳቦ ወንዝ ወረዳውን ለሁለት ከፍሎ ያልፋል።
ወንዙ ላይ ተሽከርካሪ የሚያልፍበት፣ ሰው የሚሻገርበት ዘመናዊ ድልድይ ለዘመናት ስላልነበረ፤ ምጥ የተያዘች ወላድ እንዲሁም በጽኑ የታመመ በሽተኛ በቃሬዛ ሆነው በሰው ሸክም ነበር ወደ ጤና ተቋም የሚያመሩት።
ወንዙ ሲሞላ ሁሌም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አይሄዱም ነበር።
በተለይ በክረምት ወራት የአንድ ወረዳ ማህበረሰብ እንዲሁም የቤተሰብ አባላት ጭምር ከወንዝ ወዲህና ወዲያ ሆነው በዓይን እየተያዩ በኀዘንና በደስታ መገናኘት አይችሉም ነበር ይላሉ የወረዳው ነዋሪ አቶ ካሳሁን ከበደ።
ሁሌም ክረምት በመጣ ቁጥር ወንዙን እንሻገራለን እያሉ የብዙ ሰዎች ሕይወት ያልፋል የሚሉት አቶ ካሳሁን፤ “የአህያ ባል ከጅብ አያድን” እንዲሉ የአካባቢው ማህበረሰብ ወንዙ ላይ በእንጨት ርብራብ ይሠራው የነበረው ባሕላዊ ድልድይ ክረምት ሲመጣ በጎርፍ ስለሚወሰድ፤ ወንዙን አያሻግርም።
ሆኖም ሁሌም ክረምቱ ሲያልፍ የአካባቢው ማህበረሰብ “ለሰውና ለእንስሳት መተላለፊያ” በሚል በእንጨት ርብራብ ባሕላዊ ድልድይ እየሠራ......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131643
******************
(ኢ ፕ ድ)
በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን መዋቅር ሥር ከሚገኙ ወረዳዎች፣ ሎካ አባያ ወረዳ አንዱ ነው።
ይህ ወረዳ 23 ቀበሌዎች ያሉት ሲሆን፤ በወረዳው ከሚገኙ ትልልቅ ወንዞች አንዱ የሆነው ግዳቦ ወንዝ ወረዳውን ለሁለት ከፍሎ ያልፋል።
ወንዙ ላይ ተሽከርካሪ የሚያልፍበት፣ ሰው የሚሻገርበት ዘመናዊ ድልድይ ለዘመናት ስላልነበረ፤ ምጥ የተያዘች ወላድ እንዲሁም በጽኑ የታመመ በሽተኛ በቃሬዛ ሆነው በሰው ሸክም ነበር ወደ ጤና ተቋም የሚያመሩት።
ወንዙ ሲሞላ ሁሌም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አይሄዱም ነበር።
በተለይ በክረምት ወራት የአንድ ወረዳ ማህበረሰብ እንዲሁም የቤተሰብ አባላት ጭምር ከወንዝ ወዲህና ወዲያ ሆነው በዓይን እየተያዩ በኀዘንና በደስታ መገናኘት አይችሉም ነበር ይላሉ የወረዳው ነዋሪ አቶ ካሳሁን ከበደ።
ሁሌም ክረምት በመጣ ቁጥር ወንዙን እንሻገራለን እያሉ የብዙ ሰዎች ሕይወት ያልፋል የሚሉት አቶ ካሳሁን፤ “የአህያ ባል ከጅብ አያድን” እንዲሉ የአካባቢው ማህበረሰብ ወንዙ ላይ በእንጨት ርብራብ ይሠራው የነበረው ባሕላዊ ድልድይ ክረምት ሲመጣ በጎርፍ ስለሚወሰድ፤ ወንዙን አያሻግርም።
ሆኖም ሁሌም ክረምቱ ሲያልፍ የአካባቢው ማህበረሰብ “ለሰውና ለእንስሳት መተላለፊያ” በሚል በእንጨት ርብራብ ባሕላዊ ድልድይ እየሠራ......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=131643
"በ2016/17 የመኸር ምርት 9 ሺህ ሄክታር መሬት በበርበሬ ለመሸፈን እየተሰራ ነው"- የሀላባ ዞን ግብርና መምሪያ
****************
(ኢ ፕ ድ)
በበርበሬን በስፋት በማምረት ከሚታወቁ አካባቢዎች መካከል የሀላባ ዞን አንዱ ነው፡፡
የሀላባ በርበሬን የምርታማነት ችግር በመቅረፍ አምራች አርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡
የበርበሬን በጥራትና በብዛት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እንዲሁም ለኤክስፖርት በሚሆን ደረጃ ለማምረት እንዲቻል ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።
በ2016/17 የመኸር ምርት ዘመን 9 ሺህ ሄ/ር መሬት በበርበሬ በመሸፈን 108 ሺህ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑን የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀጂ ኑሪዬ ተናግረዋል።
በዞኑ በርበሬ በዋናነት የመኸር ሰብል መሆኑን ያነሱት ኃላፊው ከ3 ዓመት ወዲህ በበልግ ማልመት በመጀመሩ የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት እንዳሻሻለ አብራርተዋል።
በዞኑ በተመረጡ 10 ቀበሌዎች በበልግ ወቅት የበርበሬ ልማትን ለማስፋፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓም
****************
(ኢ ፕ ድ)
በበርበሬን በስፋት በማምረት ከሚታወቁ አካባቢዎች መካከል የሀላባ ዞን አንዱ ነው፡፡
የሀላባ በርበሬን የምርታማነት ችግር በመቅረፍ አምራች አርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡
የበርበሬን በጥራትና በብዛት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እንዲሁም ለኤክስፖርት በሚሆን ደረጃ ለማምረት እንዲቻል ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።
በ2016/17 የመኸር ምርት ዘመን 9 ሺህ ሄ/ር መሬት በበርበሬ በመሸፈን 108 ሺህ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑን የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀጂ ኑሪዬ ተናግረዋል።
በዞኑ በርበሬ በዋናነት የመኸር ሰብል መሆኑን ያነሱት ኃላፊው ከ3 ዓመት ወዲህ በበልግ ማልመት በመጀመሩ የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት እንዳሻሻለ አብራርተዋል።
በዞኑ በተመረጡ 10 ቀበሌዎች በበልግ ወቅት የበርበሬ ልማትን ለማስፋፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓም