Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ – Telegram
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.9K subscribers
39.9K photos
298 videos
7 files
5.74K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በጎፋ ዞን በተከሰተው የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖችና ቤተሰቦች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል
*************
- የሟቾች ቁጥር ከ150 ማለፉ ተገልጿል
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ትላንት ረፋድ አካባቢ በተከሰተው የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖችና ህይወታቸው ላጡ ቤተሰቦች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ መንግስት ኮምንኬሽን ቢሮ አስታውቋል፡፡

በአከባቢው በጣለዉ ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተዉ የመሬት ናዳ በአንድ የቤተሰብ አባላት ላይ ጉዳት መድረሱን ተከትሎ እነሱን ለማትረፍ በወጡት ተጨማሪ ሰዎች ላይ የመሬት ናዳ በመከሰቱ የሟቾች ቁጥር ከፍ ማለቱን የክልሉ መንግስት ኮምንኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን ገልፀዋል፡፡

የክልሉ መንግስት በአደጋው የተጎዱ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋምና ለመደገፍ ኮሚቴ አቋቁሞ እየሰራም እደሚገኝ ተናግረዋል ።

የተጎዱ ዜጎችን መደገፍና የነፍስ አድን ስራ ቅድሚያ ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ያሉት ወ/ሮ ሰናይት በአከባቢዉ ተጨማሪ ጉዳት እንዳይከሰት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የመንግስት አካላት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር በአሁኑ ሰአት የተጎዱ ሰዎችን ነብስ ለማዳን እና ለተጎጂዎች አስፈላጊውን የህክምና የመጠለያ እና ምግብ በማቅረብ በርብርብ ላይ ይገኛል።

በአደጋው እስካሁን ድረስ ከ150 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ማጣቸውም ተገልጿል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር፣ እና ከአጎራባች ክልሎች እና ዞኖች የተወጣጡ ባለሞያዎች በሥፍራው በመገኘት ለተጎጂዎች ድጋፍ እያደረጉ እንደሚገኝ ከክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም
በጎፋ ዞን በመሬት ናዳ አደጋ ለተጎዱ ዜጎች አፋጣኝ ምላሽ እየተሰጠ ነው
****
(ኢ.ፕ.ድ)

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት ናዳ አደጋ ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ወገኖች አፋጣኝ ምላሽ እየተሰጠ መሆኑን የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን አስታወቀ።

የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ እንዳሉት በዞኑ በተከሰተው የመሬት ናዳ አደጋ በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል።

ሀምሌ 14 ቀን 2016 ዓ.ም በነበረው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት የመሬት ናዳው ማጋጠሙን ጠቁመዋል።

በመጀመሪያው ናዳ 4 ሰዎች መሞታቸውን እና እነዚህን ለማውጣት የሄዱ ወገኖች የሁለተኛው ናዳ ሰለባ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ጉዳቱ ከተከሰተ ጀምሮ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

በጉዳቱ 400 የሚሆኑ ዜጎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው፤ የሚያስፈልጋቸውን ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን አንስተዋል።

አሁንም ተጨማሪ ጉዳት እንዳይፈጠር ከበርካታ ተቋማት የተውጣጡ የባለሙያዎች ቡድን ወደስፍራው መላኩን ገልጸዋል፡፡

ተፈናቃዮችን ወደ ምቹ አካባቢ የማስፈርና አስፈላጊውን ድጋፍ የማቅረብ ስራዎች ጎን ለጎን እየተሰሩ መሆኑን መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም
በ2017 በጀት ዓመት 386 አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዷል

4 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል

******************
(ኢ ፕ ድ)
በ2017 በጀት ዓመት 386 አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት እና ከውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ፍሰት አራት ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዶ እየሠራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ወይዘሮ ሃና አርአያስላሴ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፣ ኮሚሽኑ በ2017 በጀት ዓመት ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ በአምስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ አተኩሮ በመሥራት፣ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃዶችን በመስጠት ከውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት የሚገኘውን ገቢም ለማሳደግ አቅዶ እየሠራ ነው፡፡

እንደ ወይዘሮ ሃና ገለጻ፣ የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ማሻሻል፣ በ2016 በጀት ዓመት የወጡ አዳዲስ ሕጎችን ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ ማስገባት፣ የሎጂስቲክስና የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ሥርዓት ማሻሻያዎችን ማድረግ እና የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን ሥራን ……….

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩነ ይጫኑ
https://press.et/?p=132794
ምዘና አልባው የመንጃ ፈቃድ እድሳት
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
... መንጃ ፈቃድ ካወጣ ስድስት ዓመታትን ያስቆጠረት ወጣት ሱራፌል አራጌ፣ እስካሁን ድረስ መንጃ ፈቃዴን ከማሳደስ ውጪ መኪና አሽከርክሬ አላውቅም ይላል::

መንጃ ፈቃድ ያለው ሁሉ መኪና ያሽከረክራል ማለት አይደለም የሚለው ወጣቱ፤ በእድሳቱ ወቅት የመንጃ ፈቃዱ ባለቤት መጠነኛ የሙያ ፈተና የሚፈተንበት አሠራር ቢኖር መልካም እንደሆነ ያስረዳል።

መንጃ ፈቃድ ማሳደሻው ጊዜ ካለፈ ግን ግዴታ ለሰዓታት የተግባር ፈተና መውሰድ ይጠይቃል ያለው ወጣቱ፤ የመኪና ማሽከርከር ቴክኒካል እውቀት እንደመሆኑ ከሥራው ጋር መቆየትን የሚጠይቅ በመሆኑ አሠራሩ የማሳደሻ ጊዜ ላለፈበት ብቻ ሳይሆን፣ ሁሉንም የሚያካትት ሊሆን ይገባል ይላል።

ይህን አሠራር በአጭር ጊዜ መተግባር ከባድ ቢሆን እንኳ፣ መንጃ ፈቃድ ይዞ ሲያሽከረክር የቆየውን ሳያሽከረክር ከቆየው የሚለይበት...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132796
በሃዋሳ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የቱሪዝም እንቅስቃሴውን ለማሳደግ ያስችላል
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በሐዋሳ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ የቱሪዝም እንቅስቃሴውን ለማሳደግ እንደሚያስችል የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በቅርቡ በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ በተሻለ ሁኔታ ለመቀየር ያስችላል።

የኮሪደር ልማቱ የመንገድ ማስዋብ ሥራዎችን ያካተተ፣ የብስክሌት እና የእግረኛ መንገዶችን የለየ እንዲሁም የአካል ጉዳተኞችን ከግምት ባስገባ መልኩ እየተከናወነ....

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132847
በሞጆ ከተማ በ2017 በጀት ዓመት ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ይገነባሉ
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በ2017 በጀት ዓመት ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች እንደሚገነቡና ለ20 ሺህ ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደሚፈጠሩ የሞጆ ከተማ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

የሞጆ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ እሸቱ ሹሚ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ሕዝብ የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።

በዚህም በ2017 በጀት ዓመት የከተማውን ሕዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ይገነባሉ።

ፕሮጀክቶቹን ወደ ሥራ ለማስገባት የዝግጅት ሥራዎች እየተሠሩ ነው ያሉት አቶ እሸቱ፤ በቀጣይም የህብረተሰቡን መሠረታዊ ችግር ሊቀርፉ የሚችሉ ሥራዎች እውን....

https://press.et/?p=132845
የሰነድ መዋዕለ ንዋይ መመሪያ ለካፒታል ገበያ መጠናከር አይነተኛ ሚና ይኖረዋል
*************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ያዘጋጀውና ለሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ፈቃድ መስጠት የሚያስችለው መመሪያ ለካፒታል ገበያ መጠናከር ለዘርፉ ዕድገት አይነተኛ ሚና እንደሚኖረው በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ መመህርና የኢኮኖሚ ተመራማሪ የሆኑት ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ተናገሩ።

ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ የመዋዕለ ንዋይ መመሪያ አስተዳደር መኖር የካፒታል ኢንቨስትመንት ወደሀገር ሲመጣ እንዴት በአግባቡ ማስተዳደር ይቻላል የሚለውን የሚወስን ሕግ ነው። መመሪያው መዘጋጀቱ የካፒታል ገበያ እድገትን ለማፋጠንና ለማጠናከር ይረዳል።

በተጨማሪ ከፈቃድ አሰጣጡ ጋር ተያይዞ አዳዲስ እውቀትና ቴክኖሎጂዎች እንደሚመጡ ጠቁመው፤ ዘርፉን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር መመሪያው አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።

ኢንቨስትመንቱም እንዲስፋፋና በተወሰኑ ነገሮች ለይ ብቻ ትኩረት
ሙሉውን ለማነበብ ሊንኩን ይጫኑ …………..

https://press.et/?p=132797
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አውሮፕላኖች አምራቹ ATR በጋራ ለመስራት ተስማሙ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና ክፍል የአውሮፕላኖች አምራች ከሆነው "ATR" አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ፈጸሙ።

በስምምነቱ መሰረት በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና ክፍል በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የATR ስሪት አውሮፕላኖችን የመጠገን አቅሙን የሚያዳብር መሆኑን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም
አዋሽ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት አመት 37 ነጥብ 6 ቢሊዮን አዳዲስ ብድሮች መስጠቱን አስታወቀ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
- የባንኩ ጠቅላላ ሐብት 300 ቢሊየን ብር ደርሷል
አዋሽ ባንክ ባለፈው የሂሳብ አመት 37 ነጥብ 6 ቢሊዮን አዳዲስ ብድሮችን መስጠቱን አስታወቀ
ባንኩ በዛሬው እለት ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው ከሌሎች አመታት በተለየ ሁኔታ ጥቃቅንና አነስተኛ ተበዳሪዎችን ታሳቢ ያደረገ የብድር አገልግሎት ሰጥቷል

ባንኩ በበጀት አመቱ 11 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱንም አስታውቋል።
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሺፈራው እንዳሉት ባንኩ ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋት ባለፈው የበጀት አመት 74 አዳዲስ ቅርንጫፎችን ከፍቷል።

ሥራ አስፈፃሚው፣ የባንኩ ጠቅላላ ሐብት 300 ቢሊዮን መድረሱን አስታውቀው፤ በቀጣይ በተለይ በቴክኖሎጂ የታገዙ የባንክ አገልግሎቶችን በማስፋት ረገድ ሰፋፊ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
ዮርዳኖስ ፍቅሩ
ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
ኮሚሽኑ ከልማት አጋር ተቋማት ጋር ተወያየ
***********
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት (ዩኤን.ዲ.ፒ) በኩል ድጋፍ ከሚያደርጉ የውጪ የልማት አጋር አካላት ጋር አምስተኛ ዙር ውይይት አድርጓል፡፡
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር) ኮሚሽኑ ከአራተኛው ዙር ውይይት በኋላ ያከናወናቸውን አበይት ተግባራትን በተመለከተ ለተሳታፊዎች ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ገለፃውን የተከታተሉት የልማት አጋሮች የቀረበውን ማብራሪያ መነሻ አድርገው ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል፡፡
በኮሚሽኑና በምክክሩ ዙሪያ ከተሳታፊ አጋር ድርጅቶች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች አባል ኮሚሽነሮች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሀምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በገዜ ጎፋ ወረዳ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናኑ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፌ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች አደጋው በደረሰበት ቦታ በመገኘት አጽናንተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ ከትናንት በስቲያ በጣለው ከባድ ዝናብ ሳቢያ የተከሰተው የመሬት መንሸራተት በሰውና በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማስከተሉ ይታወሳል።
አፈ ጉባኤውን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በቦታው በመገኘት አጽናንተዋል።
የክልሉ መንግስትና የአካባቢው ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት የነፍስ አድንና ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን በርብርብ እያከናወኑ ይገኛሉ።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የሚደረጉ የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችም በቅንጅት በመከናወን ላይ ናቸው።
ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
በደብረ ብርሃን 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የደብረ ብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።

22 ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት መሸጋገራቸው ተመላክቷል።

የደብረብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት፤ ደብረብርሃን ከተማን የኢንቨስትመንት ተመራጭ ከተማ በማድረግ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።

በ2016 በጀት ዓመት 26 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 200 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች...

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132871