በሞጆ ከተማ በ2017 በጀት ዓመት ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ይገነባሉ
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በ2017 በጀት ዓመት ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች እንደሚገነቡና ለ20 ሺህ ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደሚፈጠሩ የሞጆ ከተማ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
የሞጆ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ እሸቱ ሹሚ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ሕዝብ የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
በዚህም በ2017 በጀት ዓመት የከተማውን ሕዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ይገነባሉ።
ፕሮጀክቶቹን ወደ ሥራ ለማስገባት የዝግጅት ሥራዎች እየተሠሩ ነው ያሉት አቶ እሸቱ፤ በቀጣይም የህብረተሰቡን መሠረታዊ ችግር ሊቀርፉ የሚችሉ ሥራዎች እውን....
https://press.et/?p=132845
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በ2017 በጀት ዓመት ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች እንደሚገነቡና ለ20 ሺህ ወጣቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደሚፈጠሩ የሞጆ ከተማ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
የሞጆ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ እሸቱ ሹሚ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ ከተማ አስተዳደሩ የከተማውን ሕዝብ የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል።
በዚህም በ2017 በጀት ዓመት የከተማውን ሕዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ከ75 በላይ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ይገነባሉ።
ፕሮጀክቶቹን ወደ ሥራ ለማስገባት የዝግጅት ሥራዎች እየተሠሩ ነው ያሉት አቶ እሸቱ፤ በቀጣይም የህብረተሰቡን መሠረታዊ ችግር ሊቀርፉ የሚችሉ ሥራዎች እውን....
https://press.et/?p=132845
የሰነድ መዋዕለ ንዋይ መመሪያ ለካፒታል ገበያ መጠናከር አይነተኛ ሚና ይኖረዋል
*************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ያዘጋጀውና ለሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ፈቃድ መስጠት የሚያስችለው መመሪያ ለካፒታል ገበያ መጠናከር ለዘርፉ ዕድገት አይነተኛ ሚና እንደሚኖረው በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ መመህርና የኢኮኖሚ ተመራማሪ የሆኑት ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ የመዋዕለ ንዋይ መመሪያ አስተዳደር መኖር የካፒታል ኢንቨስትመንት ወደሀገር ሲመጣ እንዴት በአግባቡ ማስተዳደር ይቻላል የሚለውን የሚወስን ሕግ ነው። መመሪያው መዘጋጀቱ የካፒታል ገበያ እድገትን ለማፋጠንና ለማጠናከር ይረዳል።
በተጨማሪ ከፈቃድ አሰጣጡ ጋር ተያይዞ አዳዲስ እውቀትና ቴክኖሎጂዎች እንደሚመጡ ጠቁመው፤ ዘርፉን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር መመሪያው አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
ኢንቨስትመንቱም እንዲስፋፋና በተወሰኑ ነገሮች ለይ ብቻ ትኩረት
ሙሉውን ለማነበብ ሊንኩን ይጫኑ …………..
https://press.et/?p=132797
*************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ያዘጋጀውና ለሰነድ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ፈቃድ መስጠት የሚያስችለው መመሪያ ለካፒታል ገበያ መጠናከር ለዘርፉ ዕድገት አይነተኛ ሚና እንደሚኖረው በሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ መመህርና የኢኮኖሚ ተመራማሪ የሆኑት ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ተናገሩ።
ሞላ አለማየሁ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ የመዋዕለ ንዋይ መመሪያ አስተዳደር መኖር የካፒታል ኢንቨስትመንት ወደሀገር ሲመጣ እንዴት በአግባቡ ማስተዳደር ይቻላል የሚለውን የሚወስን ሕግ ነው። መመሪያው መዘጋጀቱ የካፒታል ገበያ እድገትን ለማፋጠንና ለማጠናከር ይረዳል።
በተጨማሪ ከፈቃድ አሰጣጡ ጋር ተያይዞ አዳዲስ እውቀትና ቴክኖሎጂዎች እንደሚመጡ ጠቁመው፤ ዘርፉን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር መመሪያው አስፈላጊ መሆኑን አንስተዋል።
ኢንቨስትመንቱም እንዲስፋፋና በተወሰኑ ነገሮች ለይ ብቻ ትኩረት
ሙሉውን ለማነበብ ሊንኩን ይጫኑ …………..
https://press.et/?p=132797
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አውሮፕላኖች አምራቹ ATR በጋራ ለመስራት ተስማሙ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና ክፍል የአውሮፕላኖች አምራች ከሆነው "ATR" አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ፈጸሙ።
በስምምነቱ መሰረት በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና ክፍል በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የATR ስሪት አውሮፕላኖችን የመጠገን አቅሙን የሚያዳብር መሆኑን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና ክፍል የአውሮፕላኖች አምራች ከሆነው "ATR" አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ፈጸሙ።
በስምምነቱ መሰረት በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጥገና ክፍል በአፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የATR ስሪት አውሮፕላኖችን የመጠገን አቅሙን የሚያዳብር መሆኑን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም
አዋሽ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት አመት 37 ነጥብ 6 ቢሊዮን አዳዲስ ብድሮች መስጠቱን አስታወቀ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
- የባንኩ ጠቅላላ ሐብት 300 ቢሊየን ብር ደርሷል
አዋሽ ባንክ ባለፈው የሂሳብ አመት 37 ነጥብ 6 ቢሊዮን አዳዲስ ብድሮችን መስጠቱን አስታወቀ
ባንኩ በዛሬው እለት ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው ከሌሎች አመታት በተለየ ሁኔታ ጥቃቅንና አነስተኛ ተበዳሪዎችን ታሳቢ ያደረገ የብድር አገልግሎት ሰጥቷል
ባንኩ በበጀት አመቱ 11 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱንም አስታውቋል።
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሺፈራው እንዳሉት ባንኩ ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋት ባለፈው የበጀት አመት 74 አዳዲስ ቅርንጫፎችን ከፍቷል።
ሥራ አስፈፃሚው፣ የባንኩ ጠቅላላ ሐብት 300 ቢሊዮን መድረሱን አስታውቀው፤ በቀጣይ በተለይ በቴክኖሎጂ የታገዙ የባንክ አገልግሎቶችን በማስፋት ረገድ ሰፋፊ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
ዮርዳኖስ ፍቅሩ
ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
- የባንኩ ጠቅላላ ሐብት 300 ቢሊየን ብር ደርሷል
አዋሽ ባንክ ባለፈው የሂሳብ አመት 37 ነጥብ 6 ቢሊዮን አዳዲስ ብድሮችን መስጠቱን አስታወቀ
ባንኩ በዛሬው እለት ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው ከሌሎች አመታት በተለየ ሁኔታ ጥቃቅንና አነስተኛ ተበዳሪዎችን ታሳቢ ያደረገ የብድር አገልግሎት ሰጥቷል
ባንኩ በበጀት አመቱ 11 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱንም አስታውቋል።
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ፀሐይ ሺፈራው እንዳሉት ባንኩ ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋት ባለፈው የበጀት አመት 74 አዳዲስ ቅርንጫፎችን ከፍቷል።
ሥራ አስፈፃሚው፣ የባንኩ ጠቅላላ ሐብት 300 ቢሊዮን መድረሱን አስታውቀው፤ በቀጣይ በተለይ በቴክኖሎጂ የታገዙ የባንክ አገልግሎቶችን በማስፋት ረገድ ሰፋፊ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
ዮርዳኖስ ፍቅሩ
ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
ኮሚሽኑ ከልማት አጋር ተቋማት ጋር ተወያየ
***********
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት (ዩኤን.ዲ.ፒ) በኩል ድጋፍ ከሚያደርጉ የውጪ የልማት አጋር አካላት ጋር አምስተኛ ዙር ውይይት አድርጓል፡፡
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር) ኮሚሽኑ ከአራተኛው ዙር ውይይት በኋላ ያከናወናቸውን አበይት ተግባራትን በተመለከተ ለተሳታፊዎች ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ገለፃውን የተከታተሉት የልማት አጋሮች የቀረበውን ማብራሪያ መነሻ አድርገው ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል፡፡
በኮሚሽኑና በምክክሩ ዙሪያ ከተሳታፊ አጋር ድርጅቶች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች አባል ኮሚሽነሮች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሀምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
***********
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት (ዩኤን.ዲ.ፒ) በኩል ድጋፍ ከሚያደርጉ የውጪ የልማት አጋር አካላት ጋር አምስተኛ ዙር ውይይት አድርጓል፡፡
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር) ኮሚሽኑ ከአራተኛው ዙር ውይይት በኋላ ያከናወናቸውን አበይት ተግባራትን በተመለከተ ለተሳታፊዎች ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ገለፃውን የተከታተሉት የልማት አጋሮች የቀረበውን ማብራሪያ መነሻ አድርገው ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል፡፡
በኮሚሽኑና በምክክሩ ዙሪያ ከተሳታፊ አጋር ድርጅቶች ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች አባል ኮሚሽነሮች ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ሀምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በገዜ ጎፋ ወረዳ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናኑ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፌ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች አደጋው በደረሰበት ቦታ በመገኘት አጽናንተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ ከትናንት በስቲያ በጣለው ከባድ ዝናብ ሳቢያ የተከሰተው የመሬት መንሸራተት በሰውና በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማስከተሉ ይታወሳል።
አፈ ጉባኤውን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በቦታው በመገኘት አጽናንተዋል።
የክልሉ መንግስትና የአካባቢው ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት የነፍስ አድንና ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን በርብርብ እያከናወኑ ይገኛሉ።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የሚደረጉ የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችም በቅንጅት በመከናወን ላይ ናቸው።
ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፌ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች አደጋው በደረሰበት ቦታ በመገኘት አጽናንተዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ ከትናንት በስቲያ በጣለው ከባድ ዝናብ ሳቢያ የተከሰተው የመሬት መንሸራተት በሰውና በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ማስከተሉ ይታወሳል።
አፈ ጉባኤውን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራል መንግስት የስራ ኃላፊዎች ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በቦታው በመገኘት አጽናንተዋል።
የክልሉ መንግስትና የአካባቢው ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት የነፍስ አድንና ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ማድረግ የሚያስችሉ ተግባራትን በርብርብ እያከናወኑ ይገኛሉ።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የሚደረጉ የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችም በቅንጅት በመከናወን ላይ ናቸው።
ሐምሌ 17 ቀን 2016 ዓ.ም
በደብረ ብርሃን 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የደብረ ብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
22 ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት መሸጋገራቸው ተመላክቷል።
የደብረብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት፤ ደብረብርሃን ከተማን የኢንቨስትመንት ተመራጭ ከተማ በማድረግ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
በ2016 በጀት ዓመት 26 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 200 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132871
*********
(ኢ.ፕ.ድ)
በተጠናቀቀው የ2016 በጀት ዓመት 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የደብረ ብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
22 ኢንዱስትሪዎች ወደ ምርት መሸጋገራቸው ተመላክቷል።
የደብረብርሃን ከተማ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ብርሃን ገብረህይወት እንደገለጹት፤ ደብረብርሃን ከተማን የኢንቨስትመንት ተመራጭ ከተማ በማድረግ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
በ2016 በጀት ዓመት 26 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 200 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 30 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 216 ባለሀብቶች...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132871
“ከኮሚሽኑ ምስረታ በኋላ ኢትዮጵያን በጸጥታው ምክር ቤት አጀንዳ ለማድረግ ምክንያት አይኖርም”
-ፕሮፌሰር መኮንን አያና
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከናይል ተፋሰስ የትብብር ኮሚሽን ምስረታ በኋላ ኢትዮጵያን በውሃ ምክንያት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት አጀንዳ አድርጎ ማቅረብ ምክንያት እንደማይኖር በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር መኮንን አያና አስታወቁ።
ፕሮፌሰር መኮንን አያና ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሐምሌ ወር በ2016 ዓ.ም መጀመሪያ ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን ስድስተኛ ሀገር በመሆን በፓርላማ አጽድቃለች።
በዚህም ከ11 የናይል ተፋሰስ ሀገራት ውስጥ ስድስት ሀገራት በፓርላማ በማጽደቃቸው ቋሚ የናይል ተፋሰስ ሀገራት ኮሚሽን ሙሉ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132866
-ፕሮፌሰር መኮንን አያና
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከናይል ተፋሰስ የትብብር ኮሚሽን ምስረታ በኋላ ኢትዮጵያን በውሃ ምክንያት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት አጀንዳ አድርጎ ማቅረብ ምክንያት እንደማይኖር በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ፕሮፌሰር መኮንን አያና አስታወቁ።
ፕሮፌሰር መኮንን አያና ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በሐምሌ ወር በ2016 ዓ.ም መጀመሪያ ደቡብ ሱዳን የናይል ስምምነት ማዕቀፍን ስድስተኛ ሀገር በመሆን በፓርላማ አጽድቃለች።
በዚህም ከ11 የናይል ተፋሰስ ሀገራት ውስጥ ስድስት ሀገራት በፓርላማ በማጽደቃቸው ቋሚ የናይል ተፋሰስ ሀገራት ኮሚሽን ሙሉ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132866
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሶስት ትሪሊዮን ብር የሚደርስ ሀብት አፍርተዋል
************
(ኢ.ፕ.ድ)
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አጠቃላይ ሀብት ሶስት ትሪሊዮን ብር የደረሰ መሆኑ ተገለጸ።
የልማት ድርጅቶቹ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ እያደገ መምጣቱን የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታውቋል።
የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ተቋሙ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም እና ተወዳዳሪነት እንዲሻሻል ማድረግ፣ ዘመናዊ የኮርፖሬት አስተዳደርና የኮርፖሬት ፋይናንስ ሥርዓትን መዘርጋት፣ የልማት ድርጅቶቹ ልምድ እና ዕውቀት ባላቸው ሰዎች የሚመሩበትን ሥርዓት መዘርጋት ከሚተገብራቸው ተግባራቶቹ ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው።
በዚህም የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ለሀገር ኢኮኖሚ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132867
************
(ኢ.ፕ.ድ)
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አጠቃላይ ሀብት ሶስት ትሪሊዮን ብር የደረሰ መሆኑ ተገለጸ።
የልማት ድርጅቶቹ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ እያደገ መምጣቱን የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታውቋል።
የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ኃይለሚካኤል ለኢፕድ እንደገለጹት፤ ተቋሙ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አፈጻጸም እና ተወዳዳሪነት እንዲሻሻል ማድረግ፣ ዘመናዊ የኮርፖሬት አስተዳደርና የኮርፖሬት ፋይናንስ ሥርዓትን መዘርጋት፣ የልማት ድርጅቶቹ ልምድ እና ዕውቀት ባላቸው ሰዎች የሚመሩበትን ሥርዓት መዘርጋት ከሚተገብራቸው ተግባራቶቹ ውስጥ ተጠቃሽ ናቸው።
በዚህም የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ለሀገር ኢኮኖሚ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132867
በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት አንሰጥም የሚሉ ተቋማት የወንጀል ኃላፊነት አለባቸው
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት አንሰጥም የሚሉ ተቋማት የወንጀል ኃላፊነት እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል ሲል የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ።
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሕግና ፖሊሲ ክፍል ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ 1284/2015 በግልጽ ባስቀመጠው ድንጋጌ ማንነትን በማረጋገጥ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ተቋማት የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም ሊሰጡ እንደሚገባቸው ተደንግጓል።
ይህ ድንጋጌ በሀገሪቱ ከፍተኛ ሕግ አውጪ አካል በሆነው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተደነገገ አዋጅ ነው ያሉት ጋብሬላ፤ ይህንን የማይተገብሩ ግለሰቦችና ተቋማት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132869
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት አንሰጥም የሚሉ ተቋማት የወንጀል ኃላፊነት እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል ሲል የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ።
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሕግና ፖሊሲ ክፍል ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ 1284/2015 በግልጽ ባስቀመጠው ድንጋጌ ማንነትን በማረጋገጥ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ተቋማት የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም ሊሰጡ እንደሚገባቸው ተደንግጓል።
ይህ ድንጋጌ በሀገሪቱ ከፍተኛ ሕግ አውጪ አካል በሆነው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተደነገገ አዋጅ ነው ያሉት ጋብሬላ፤ ይህንን የማይተገብሩ ግለሰቦችና ተቋማት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132869
በከተማዋ በክረምት በጎ ፍቃድ 250 የአረጋውያን ቤቶች እድሳትና ግንባታ ሥራ ተጀምሯል
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሀዋሳ ከተማ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት 250 የአረጋውያን እና የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች እድሳትና ግንባታ ሥራ መጀመሩን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ።
የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በከተማዋ በዘንድሮ በ2016 ዓ.ም ክረምት በበጎ ፍቃድ አገልግሎት 250ሺህ ዜጎች ተጠቃሚ ይሆናሉ።
ከሚከናወኑት የበጎ ፍቃድ ሥራዎች ውስጥ አንዱ በሰው ተኮር ተግባራት የአረጋውያን ቤቶች እድሳትና ግንባታ መሆኑን የጠቆሙት አቶ መኩሪያ፤ በያዝነው ክረምት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የ250 ቤቶች ግንባታና እድሳት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132870
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሀዋሳ ከተማ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት 250 የአረጋውያን እና የአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች እድሳትና ግንባታ ሥራ መጀመሩን የከተማ አስተዳደሩ ገለጸ።
የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በከተማዋ በዘንድሮ በ2016 ዓ.ም ክረምት በበጎ ፍቃድ አገልግሎት 250ሺህ ዜጎች ተጠቃሚ ይሆናሉ።
ከሚከናወኑት የበጎ ፍቃድ ሥራዎች ውስጥ አንዱ በሰው ተኮር ተግባራት የአረጋውያን ቤቶች እድሳትና ግንባታ መሆኑን የጠቆሙት አቶ መኩሪያ፤ በያዝነው ክረምት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የ250 ቤቶች ግንባታና እድሳት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://press.et/?p=132870