#የውጭ_ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻያ‼️
በገበያ ወደሚወሰን የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት መሸጋገር የሚያስገኛቸው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች፤
👉 የውጭ ምንዛሪ ገቢ በሚያስገኙ ዘርፎች የተሠማሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ይጠቅማል፣
👉 የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለነዋሪዎችና ለአምራች ዘርፎች ጥቅም መዋሉን ለማረጋገጥ ይረዳል፣
👉 በኢኮኖሚው ውስጥ ኢ-መደበኛነትንና ሕገ ወጥነትን ሲያበረታቱ የቆዩ በርካታ የንግድ አሠራሮችን ለማስቀረት ይረዳል፣
👉 ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎችን ያበረታታል፣
👉 የግሉን ዘርፍ ለማሳደግና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማዘመን ያግዛል፣
👉 ኢኮኖሚውን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ለማድረግ የተወሰዱ የማሻሻያ እርምጃዎችን የሚያጠናክር ይሆናል፤
👉 የውጭ ኢንቨስተሮችን በመሳብ፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ፣ የንግድ ሥርዓታችንን ከአጎራባችና ከአቻ ሀገራት ጋር የተጣጣመ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፣
ኢትዮጵያ በትናንትናው ዕለት መንግሥት አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራምን አስመልክቶ የሰጠውን መግለጫ ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻሉ ይታወሳል።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
በገበያ ወደሚወሰን የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት መሸጋገር የሚያስገኛቸው ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች፤
👉 የውጭ ምንዛሪ ገቢ በሚያስገኙ ዘርፎች የተሠማሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ይጠቅማል፣
👉 የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለነዋሪዎችና ለአምራች ዘርፎች ጥቅም መዋሉን ለማረጋገጥ ይረዳል፣
👉 በኢኮኖሚው ውስጥ ኢ-መደበኛነትንና ሕገ ወጥነትን ሲያበረታቱ የቆዩ በርካታ የንግድ አሠራሮችን ለማስቀረት ይረዳል፣
👉 ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎችን ያበረታታል፣
👉 የግሉን ዘርፍ ለማሳደግና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለማዘመን ያግዛል፣
👉 ኢኮኖሚውን ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ለማድረግ የተወሰዱ የማሻሻያ እርምጃዎችን የሚያጠናክር ይሆናል፤
👉 የውጭ ኢንቨስተሮችን በመሳብ፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በማሳደግ፣ የንግድ ሥርዓታችንን ከአጎራባችና ከአቻ ሀገራት ጋር የተጣጣመ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፣
ኢትዮጵያ በትናንትናው ዕለት መንግሥት አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራምን አስመልክቶ የሰጠውን መግለጫ ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻሉ ይታወሳል።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
ዲያስፖራው ከሃምሳ አራት ሚሊዮን ብር በላይ ለፅዱና ለአረንጓዴ ዐሻራ አስተዋፅዖ አድርጓል
*****
(ኢ ፕ ድ)
ዲያስፖራው ከሃምሳ አራት ሚሊዮን ብር በላይ በማዋጣት በፅዱ እና አረንጓዴ ዐሻራ ተሳትፎ ማድረጉን የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት አስታወቀ::
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር አቶ አባይነህ አቅናው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳሉት፤ ዲያስፖራው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ጥሪ መሠረት ከሠላሳ ሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ለፅዱ ጎዳና እና አረንጓዴ መርሐ ግብር መዋጮ አድርጓል:: ሃያ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚገመት ብር ወጪ በማድረግ አስራ አምስት መፀዳጃ ቤቶችን ለመሥራት ቃል ተገብቷል::
የዲያስፖራው በተደራጀ መንገድ ያለውን ክህሎት፣ ዕውቀት እና ቴክኖሎጂ ወደ ሀገሩ በመምጣት አስተዋፅዖ እንዲያደርግ የበኩሉን እንዲወጣ የማሳተፍ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል:: እስከ አሁን ተስፋ ቴክ ኤንድ ሰርቭ ፎር አርቲካል የሚባል የቴክኖሎጂ ካምፓኒ በየጊዜው እየመጣ ሰዎችን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ሥልጠና ይሰጣል፤ እንዲሁም ብራይት ኦፍ ቴክኖሎጂ የሚባል ካምፓኒ በቋሚነት በሚባል ደረጃ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ልምምዶች እየሰጠ.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133184
*****
(ኢ ፕ ድ)
ዲያስፖራው ከሃምሳ አራት ሚሊዮን ብር በላይ በማዋጣት በፅዱ እና አረንጓዴ ዐሻራ ተሳትፎ ማድረጉን የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት አስታወቀ::
የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር አቶ አባይነህ አቅናው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳሉት፤ ዲያስፖራው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ጥሪ መሠረት ከሠላሳ ሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ለፅዱ ጎዳና እና አረንጓዴ መርሐ ግብር መዋጮ አድርጓል:: ሃያ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚገመት ብር ወጪ በማድረግ አስራ አምስት መፀዳጃ ቤቶችን ለመሥራት ቃል ተገብቷል::
የዲያስፖራው በተደራጀ መንገድ ያለውን ክህሎት፣ ዕውቀት እና ቴክኖሎጂ ወደ ሀገሩ በመምጣት አስተዋፅዖ እንዲያደርግ የበኩሉን እንዲወጣ የማሳተፍ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አመልክተዋል:: እስከ አሁን ተስፋ ቴክ ኤንድ ሰርቭ ፎር አርቲካል የሚባል የቴክኖሎጂ ካምፓኒ በየጊዜው እየመጣ ሰዎችን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ሥልጠና ይሰጣል፤ እንዲሁም ብራይት ኦፍ ቴክኖሎጂ የሚባል ካምፓኒ በቋሚነት በሚባል ደረጃ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ልምምዶች እየሰጠ.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133184
👍1
በቀጣይ አራት ዓመታት ምን ይጠበቃል⁉️
👉 የኢትዮጵያ ኢከኖሚ በአማካይ በ8 በመቶ ያህል ያድጋል፤
👉 የዋጋ ንረት ወደ 10 በመቶ የተጠጋ ይሆናል፤
👉 የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ 11 በመቶ ይደርሳል፣
👉 የመንግሥት ዕዳ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ወደ 35 በመቶ ዝቅ ይላል፤
👉 የወጪና የገቢ ንግድ ዋጋ ወደ 20 ቢሊዮን ዶላር ያድጋል፤
👉 ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንት ወደ 8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ይላል፤
👉 ዓለም አቀፍ የመጠባበቂያ ክምችት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ ይሆናል፣
👉 የኢትዮጵያ ኢከኖሚ በአማካይ በ8 በመቶ ያህል ያድጋል፤
👉 የዋጋ ንረት ወደ 10 በመቶ የተጠጋ ይሆናል፤
👉 የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ 11 በመቶ ይደርሳል፣
👉 የመንግሥት ዕዳ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ያለው ድርሻ ወደ 35 በመቶ ዝቅ ይላል፤
👉 የወጪና የገቢ ንግድ ዋጋ ወደ 20 ቢሊዮን ዶላር ያድጋል፤
👉 ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንት ወደ 8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ይላል፤
👉 ዓለም አቀፍ የመጠባበቂያ ክምችት ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ ይሆናል፣
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት‼️
የሉሲ(ድንቅነሽ) ግኝት የሳይንሱን ማኅበረሰብ ብሎም መላውን አለም ስለምድራችን እና ስላሳለፈችው የሕይወት መልክ ለማወቅ ያስቻለ መሥራች ሁነት ነበር። ግኝቱ ብዙ ጥያቄዎችን የመለሰ ብዙ አዳዲስ ጥያቄዎችን ያነሳሳ ሲሆን በጥያቄዎቹም ለብዙ ምርምሮች መነሻ መሆኑ እስከዛሬ እንደቀጠለ ነው።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
የሉሲ(ድንቅነሽ) ግኝት የሳይንሱን ማኅበረሰብ ብሎም መላውን አለም ስለምድራችን እና ስላሳለፈችው የሕይወት መልክ ለማወቅ ያስቻለ መሥራች ሁነት ነበር። ግኝቱ ብዙ ጥያቄዎችን የመለሰ ብዙ አዳዲስ ጥያቄዎችን ያነሳሳ ሲሆን በጥያቄዎቹም ለብዙ ምርምሮች መነሻ መሆኑ እስከዛሬ እንደቀጠለ ነው።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
“ቀደምት የሠው ልጆች መገኛ የሆነችውን ድንቅ ሀገር እንድትጎበኙ ጥሪ አቀርባለሁ”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)
በመላው ዓለም የምትገኙ ሁሉ ቀደምት የሠው ልጆች መገኛ የሆነችውን ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያን ጎብኙ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።
“የድንቅ ግኝት ግማሽ ምዕት ዓመት” በሚል መሪ ሃሳብ የድንቅነሽ ቅሪተ አካል የተገኘበት 50ኛ ዓመት በዓል በቱሪዝም ሚኒስቴር አስተባባሪነት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ ተከብሯል።
በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድንቅ ሀገር በሆነችው ኢትዮጵያ በርካታ የዓለም ቅርሶች አሉ፤ ይህንን መጎብኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የተመዘገቡና በርካታ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መስህቦች አሏት፤ ባለፉት 5 ዓመታት በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።
ድንቅነሽ የተገኘችበት 50 ዓመት ሲከበርም ኢትዮጵያ እንደ ፕሮፌሰር ዮሐንስ ያሉ በዓለም ምርጥ የተባሉ የቅሪተ አካላት ግኝት ያላቸው ተመራማሪዎችን የያዘች ሀገር በመሆኗ በቀጣይ በዘርፉ ብዙ ምርምር ይደረጋል ብለዋል።
በመድረኩ የሉሲ ቅሪተ አካልን ያገኙት ፕሮፌሰር ዶናልድ ጆንሰንና ኢትዮጵያዊው የቅሪተ አካላትና የሰው ዘር አመጣጥ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ዮሐንስ ኃይለሥላሴ እንዲሁም የዘርፉ ተመራማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)
በመላው ዓለም የምትገኙ ሁሉ ቀደምት የሠው ልጆች መገኛ የሆነችውን ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያን ጎብኙ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።
“የድንቅ ግኝት ግማሽ ምዕት ዓመት” በሚል መሪ ሃሳብ የድንቅነሽ ቅሪተ አካል የተገኘበት 50ኛ ዓመት በዓል በቱሪዝም ሚኒስቴር አስተባባሪነት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ ተከብሯል።
በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድንቅ ሀገር በሆነችው ኢትዮጵያ በርካታ የዓለም ቅርሶች አሉ፤ ይህንን መጎብኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የተመዘገቡና በርካታ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መስህቦች አሏት፤ ባለፉት 5 ዓመታት በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።
ድንቅነሽ የተገኘችበት 50 ዓመት ሲከበርም ኢትዮጵያ እንደ ፕሮፌሰር ዮሐንስ ያሉ በዓለም ምርጥ የተባሉ የቅሪተ አካላት ግኝት ያላቸው ተመራማሪዎችን የያዘች ሀገር በመሆኗ በቀጣይ በዘርፉ ብዙ ምርምር ይደረጋል ብለዋል።
በመድረኩ የሉሲ ቅሪተ አካልን ያገኙት ፕሮፌሰር ዶናልድ ጆንሰንና ኢትዮጵያዊው የቅሪተ አካላትና የሰው ዘር አመጣጥ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ዮሐንስ ኃይለሥላሴ እንዲሁም የዘርፉ ተመራማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
👍1
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
******
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።
አየር መንገዱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን አጓጉዟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በሰጡት መግለጫ፣ አየር መንገዱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 14 በመቶ አድጓል።
በጀት ዓመቱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን በማጓጓዙን ገልጸው፤ 13 ነጥብ 4 ዓለም አቀፍ መንገደኞች ሲሆኑ ቀሪዎቹ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ናቸው ብለዋል።
በጭነት 754 ሺህ 681 ቶን ማጓጓዙን ገልጸው፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ስድስት በመቶ ማደጉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ አምስት ዓለም አቀፍ የመንገደኛ መዳረሻ በመጨመር የአለም አቀፍ በረራ መዳረሻዎችን 139 ማድረስ መቻሉን አስታውቀዋል።
በሄለን ወንድምነው
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።
አየር መንገዱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን አጓጉዟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በሰጡት መግለጫ፣ አየር መንገዱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 14 በመቶ አድጓል።
በጀት ዓመቱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን በማጓጓዙን ገልጸው፤ 13 ነጥብ 4 ዓለም አቀፍ መንገደኞች ሲሆኑ ቀሪዎቹ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ናቸው ብለዋል።
በጭነት 754 ሺህ 681 ቶን ማጓጓዙን ገልጸው፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ስድስት በመቶ ማደጉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ አምስት ዓለም አቀፍ የመንገደኛ መዳረሻ በመጨመር የአለም አቀፍ በረራ መዳረሻዎችን 139 ማድረስ መቻሉን አስታውቀዋል።
በሄለን ወንድምነው
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
ዛሬ ሃያ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎቻችን የትምህርት ጥራትን አስመልክቶ ባካሄዱት የኦን ላይን ስልጠና መክፈቻ ወቅት የትውልድ ቅብብል የተሳካ የሚሆነው እንደነርሱ ያሉ መምህራን በሚወጡት እጅግ ጠቃሚ ሚና መሆኑን ገልጫለሁ።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
ዛሬ ሃያ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎቻችን የትምህርት ጥራትን አስመልክቶ ባካሄዱት የኦን ላይን ስልጠና መክፈቻ ወቅት የትውልድ ቅብብል የተሳካ የሚሆነው እንደነርሱ ያሉ መምህራን በሚወጡት እጅግ ጠቃሚ ሚና መሆኑን ገልጫለሁ።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም