የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት‼️
የሉሲ(ድንቅነሽ) ግኝት የሳይንሱን ማኅበረሰብ ብሎም መላውን አለም ስለምድራችን እና ስላሳለፈችው የሕይወት መልክ ለማወቅ ያስቻለ መሥራች ሁነት ነበር። ግኝቱ ብዙ ጥያቄዎችን የመለሰ ብዙ አዳዲስ ጥያቄዎችን ያነሳሳ ሲሆን በጥያቄዎቹም ለብዙ ምርምሮች መነሻ መሆኑ እስከዛሬ እንደቀጠለ ነው።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
የሉሲ(ድንቅነሽ) ግኝት የሳይንሱን ማኅበረሰብ ብሎም መላውን አለም ስለምድራችን እና ስላሳለፈችው የሕይወት መልክ ለማወቅ ያስቻለ መሥራች ሁነት ነበር። ግኝቱ ብዙ ጥያቄዎችን የመለሰ ብዙ አዳዲስ ጥያቄዎችን ያነሳሳ ሲሆን በጥያቄዎቹም ለብዙ ምርምሮች መነሻ መሆኑ እስከዛሬ እንደቀጠለ ነው።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
“ቀደምት የሠው ልጆች መገኛ የሆነችውን ድንቅ ሀገር እንድትጎበኙ ጥሪ አቀርባለሁ”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)
በመላው ዓለም የምትገኙ ሁሉ ቀደምት የሠው ልጆች መገኛ የሆነችውን ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያን ጎብኙ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።
“የድንቅ ግኝት ግማሽ ምዕት ዓመት” በሚል መሪ ሃሳብ የድንቅነሽ ቅሪተ አካል የተገኘበት 50ኛ ዓመት በዓል በቱሪዝም ሚኒስቴር አስተባባሪነት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ ተከብሯል።
በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድንቅ ሀገር በሆነችው ኢትዮጵያ በርካታ የዓለም ቅርሶች አሉ፤ ይህንን መጎብኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የተመዘገቡና በርካታ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መስህቦች አሏት፤ ባለፉት 5 ዓመታት በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።
ድንቅነሽ የተገኘችበት 50 ዓመት ሲከበርም ኢትዮጵያ እንደ ፕሮፌሰር ዮሐንስ ያሉ በዓለም ምርጥ የተባሉ የቅሪተ አካላት ግኝት ያላቸው ተመራማሪዎችን የያዘች ሀገር በመሆኗ በቀጣይ በዘርፉ ብዙ ምርምር ይደረጋል ብለዋል።
በመድረኩ የሉሲ ቅሪተ አካልን ያገኙት ፕሮፌሰር ዶናልድ ጆንሰንና ኢትዮጵያዊው የቅሪተ አካላትና የሰው ዘር አመጣጥ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ዮሐንስ ኃይለሥላሴ እንዲሁም የዘርፉ ተመራማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)
በመላው ዓለም የምትገኙ ሁሉ ቀደምት የሠው ልጆች መገኛ የሆነችውን ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያን ጎብኙ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ።
“የድንቅ ግኝት ግማሽ ምዕት ዓመት” በሚል መሪ ሃሳብ የድንቅነሽ ቅሪተ አካል የተገኘበት 50ኛ ዓመት በዓል በቱሪዝም ሚኒስቴር አስተባባሪነት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ዛሬ ተከብሯል።
በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድንቅ ሀገር በሆነችው ኢትዮጵያ በርካታ የዓለም ቅርሶች አሉ፤ ይህንን መጎብኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የተመዘገቡና በርካታ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መስህቦች አሏት፤ ባለፉት 5 ዓመታት በቱሪዝም ዘርፍ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል።
ድንቅነሽ የተገኘችበት 50 ዓመት ሲከበርም ኢትዮጵያ እንደ ፕሮፌሰር ዮሐንስ ያሉ በዓለም ምርጥ የተባሉ የቅሪተ አካላት ግኝት ያላቸው ተመራማሪዎችን የያዘች ሀገር በመሆኗ በቀጣይ በዘርፉ ብዙ ምርምር ይደረጋል ብለዋል።
በመድረኩ የሉሲ ቅሪተ አካልን ያገኙት ፕሮፌሰር ዶናልድ ጆንሰንና ኢትዮጵያዊው የቅሪተ አካላትና የሰው ዘር አመጣጥ ተመራማሪው ፕሮፌሰር ዮሐንስ ኃይለሥላሴ እንዲሁም የዘርፉ ተመራማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በጌትነት ተስፋማርያም
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
👍1
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
******
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።
አየር መንገዱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን አጓጉዟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በሰጡት መግለጫ፣ አየር መንገዱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 14 በመቶ አድጓል።
በጀት ዓመቱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን በማጓጓዙን ገልጸው፤ 13 ነጥብ 4 ዓለም አቀፍ መንገደኞች ሲሆኑ ቀሪዎቹ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ናቸው ብለዋል።
በጭነት 754 ሺህ 681 ቶን ማጓጓዙን ገልጸው፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ስድስት በመቶ ማደጉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ አምስት ዓለም አቀፍ የመንገደኛ መዳረሻ በመጨመር የአለም አቀፍ በረራ መዳረሻዎችን 139 ማድረስ መቻሉን አስታውቀዋል።
በሄለን ወንድምነው
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።
አየር መንገዱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን አጓጉዟል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በሰጡት መግለጫ፣ አየር መንገዱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 7 ነጥብ 02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 14 በመቶ አድጓል።
በጀት ዓመቱ 17 ነጥብ አንድ ሚሊዮን መንገደኞችን በማጓጓዙን ገልጸው፤ 13 ነጥብ 4 ዓለም አቀፍ መንገደኞች ሲሆኑ ቀሪዎቹ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ናቸው ብለዋል።
በጭነት 754 ሺህ 681 ቶን ማጓጓዙን ገልጸው፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ስድስት በመቶ ማደጉን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ አምስት ዓለም አቀፍ የመንገደኛ መዳረሻ በመጨመር የአለም አቀፍ በረራ መዳረሻዎችን 139 ማድረስ መቻሉን አስታውቀዋል።
በሄለን ወንድምነው
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
ዛሬ ሃያ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎቻችን የትምህርት ጥራትን አስመልክቶ ባካሄዱት የኦን ላይን ስልጠና መክፈቻ ወቅት የትውልድ ቅብብል የተሳካ የሚሆነው እንደነርሱ ያሉ መምህራን በሚወጡት እጅግ ጠቃሚ ሚና መሆኑን ገልጫለሁ።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
ዛሬ ሃያ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎቻችን የትምህርት ጥራትን አስመልክቶ ባካሄዱት የኦን ላይን ስልጠና መክፈቻ ወቅት የትውልድ ቅብብል የተሳካ የሚሆነው እንደነርሱ ያሉ መምህራን በሚወጡት እጅግ ጠቃሚ ሚና መሆኑን ገልጫለሁ።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመጪው ረቡዕ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ
***
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመጪው ረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 58 (4) እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአሰራርና የአባላት ሥነምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 15 (1 እና 2) መሰረት ምክር ቤቱ በዕረፍት ላይ እያለ የምክር ቤቱን ውሳኔ የሚሹ አስቸኳይ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ አስቸኳይ ስብሰባ ሊጠራ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡
በዚሁ መሰረት የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ለረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርተዋል፡፡
ስለሆነም የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት በዕለቱ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ ሪፖርት በማድረግ በአስቸኳይ ስብሰባው እንዲገኙ ጥሪ መተላለፉን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
***
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመጪው ረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 58 (4) እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአሰራርና የአባላት ሥነምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 15 (1 እና 2) መሰረት ምክር ቤቱ በዕረፍት ላይ እያለ የምክር ቤቱን ውሳኔ የሚሹ አስቸኳይ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ አስቸኳይ ስብሰባ ሊጠራ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡
በዚሁ መሰረት የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ለረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርተዋል፡፡
ስለሆነም የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት በዕለቱ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ ሪፖርት በማድረግ በአስቸኳይ ስብሰባው እንዲገኙ ጥሪ መተላለፉን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በደረሰዉ የመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸዉ ላጡ ወገኖች የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት በጎፋ ዞን ሳዉላ ከተማ ተካሄደ።
ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓም
ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓም