የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
ዛሬ ሃያ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎቻችን የትምህርት ጥራትን አስመልክቶ ባካሄዱት የኦን ላይን ስልጠና መክፈቻ ወቅት የትውልድ ቅብብል የተሳካ የሚሆነው እንደነርሱ ያሉ መምህራን በሚወጡት እጅግ ጠቃሚ ሚና መሆኑን ገልጫለሁ።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
ዛሬ ሃያ ስምንት ዩኒቨርሲቲዎቻችን የትምህርት ጥራትን አስመልክቶ ባካሄዱት የኦን ላይን ስልጠና መክፈቻ ወቅት የትውልድ ቅብብል የተሳካ የሚሆነው እንደነርሱ ያሉ መምህራን በሚወጡት እጅግ ጠቃሚ ሚና መሆኑን ገልጫለሁ።
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመጪው ረቡዕ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ
***
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመጪው ረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 58 (4) እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአሰራርና የአባላት ሥነምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 15 (1 እና 2) መሰረት ምክር ቤቱ በዕረፍት ላይ እያለ የምክር ቤቱን ውሳኔ የሚሹ አስቸኳይ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ አስቸኳይ ስብሰባ ሊጠራ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡
በዚሁ መሰረት የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ለረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርተዋል፡፡
ስለሆነም የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት በዕለቱ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ ሪፖርት በማድረግ በአስቸኳይ ስብሰባው እንዲገኙ ጥሪ መተላለፉን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
***
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመጪው ረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 58 (4) እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአሰራርና የአባላት ሥነምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 15 (1 እና 2) መሰረት ምክር ቤቱ በዕረፍት ላይ እያለ የምክር ቤቱን ውሳኔ የሚሹ አስቸኳይ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ አስቸኳይ ስብሰባ ሊጠራ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡
በዚሁ መሰረት የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ ለረቡዕ ሐምሌ 24 ቀን 2016 ዓ.ም አስቸኳይ ስብሰባ ጠርተዋል፡፡
ስለሆነም የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት በዕለቱ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ ሪፖርት በማድረግ በአስቸኳይ ስብሰባው እንዲገኙ ጥሪ መተላለፉን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓም
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በደረሰዉ የመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸዉ ላጡ ወገኖች የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት በጎፋ ዞን ሳዉላ ከተማ ተካሄደ።
ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓም
ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓም
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ለኢትዮጵያ የ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር ብድር አጸደቀ
**-
(ኢ.ፕ.ድ)
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት አስፍጻሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ ለአራት ዓመት የ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር የተራዘመ ብድር አገልግሎት አቅርቦትን አጽድቋል፡፡
አይ ኤም ኤፍ ጉዳዩን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል...!!
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት አስፈጻሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ የሚሆንና መጠኑም 2.556 ቢሊየን SDR (የኮታው 850% ወይም ወደ 3.4 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ) የሆነ፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መፋለስን መፍታትን እና በግል ዘርፉ ለሚመራ እድገት መሠረት መጣልን አላማው ያደረገውን የመንግሥትን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አፈጻጸም የሚደግፍ የአራት ዓመት የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦት(ECF) አጽድቋል።
የአስፈጻሚ ቦርዱ ውሳኔም ኢትዮጵያ ከባላንስ ኦፍ ፓይመንት ጋር የተያያዙ ፍላጎቶቿን እንድታሟላ የሚረዳትን እንዲሁም በጀቷን የሚደግፈውን የ766.75 ሚሊየን SDR ወይም 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ የሚሆን ገንዘብ ክፍያ ወዲያውኑ እንዲለቀቅ የሚያስችል ይሆናል።
በአራት ዓመቱ የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦት የሚደገፈው የመንግሥት የኢኮኖሚ ፕሮግራም የግል ዘርፉን እንቅስቃሴ የሚያነቃቃ ሁለገብ የፖሊሲ ፓኬጅን እንዲሁም የላቀ እና በይበልጥ አካታች የሆነ እድገትን ማምጣትይቻል ዘንድ ኢኮኖሚውን ክፍት ማድረግን ኢላማው ያደረገ ነው።
ማሻሻያው ተጋላጭ በሆኑ ቤተሰቦች/አባዎራዎች ላይ የሚኖረውን ተጽእኖ ለማለዘብ ይቻል ዘንድ የማህበራዊ ሴፍቲ ኔቶችን ማጠናከርም የመንግሥት የማሻሻያ ፕሮግራም አንድ ወሳኝ ክፍለአካል ነው። ቁልፍ የሚባሉት ፖሊሲዎችም የሚከተሉትን ያካትታሉ፡
1) ውጫዊ ኢሚዛናዊንትን ለመፍታት እና የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለማስታገስ በገበያ ወደሚወሰን የምንዛሪ ዋጋ መሄድ፤
2) የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍን በማዘመን የዋጋ ግሽበትን መዋጋት፤
3) የሀገር ውስጥ የገንዘብ ምንጮችን በማሰባብሰብ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ሕዝባዊ ወጪዎች ማዋል፤
4) ከውጪአበዳሪዎች ጋር የሚደረጉ ወቅታዊ የእዳ ሪስትረክቸሪንግ ስምምነቶችን በመፈጸም ጭምር የእዳ አከፋፈል ዘላቂነትን መመለስ እንዲሁም
5) ወሳኝ የሆኑ የማክሮ ፋይናንሺያል ተጋላጭነቶችን ለመቀነስ የመንግሥት ኢንተርፕራይዞችን የገንዘብ አቋም ማጠናከር።
ፕሮግራሙ ከልማት አጋሮች የሚገኝ ተጨማሪ የገንዘብ አቅርቦትን በማፋጠን እንዲሁም በመካሄድ ላይ ያለው የእዳ ሪስትረክቸሪንግ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የሚያደርግ ማዕቀፍ በመስጠት ረገድ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
**-
(ኢ.ፕ.ድ)
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት አስፍጻሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ ለአራት ዓመት የ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር የተራዘመ ብድር አገልግሎት አቅርቦትን አጽድቋል፡፡
አይ ኤም ኤፍ ጉዳዩን አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል...!!
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት አስፈጻሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ የሚሆንና መጠኑም 2.556 ቢሊየን SDR (የኮታው 850% ወይም ወደ 3.4 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ) የሆነ፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መፋለስን መፍታትን እና በግል ዘርፉ ለሚመራ እድገት መሠረት መጣልን አላማው ያደረገውን የመንግሥትን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አፈጻጸም የሚደግፍ የአራት ዓመት የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦት(ECF) አጽድቋል።
የአስፈጻሚ ቦርዱ ውሳኔም ኢትዮጵያ ከባላንስ ኦፍ ፓይመንት ጋር የተያያዙ ፍላጎቶቿን እንድታሟላ የሚረዳትን እንዲሁም በጀቷን የሚደግፈውን የ766.75 ሚሊየን SDR ወይም 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ የሚሆን ገንዘብ ክፍያ ወዲያውኑ እንዲለቀቅ የሚያስችል ይሆናል።
በአራት ዓመቱ የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦት የሚደገፈው የመንግሥት የኢኮኖሚ ፕሮግራም የግል ዘርፉን እንቅስቃሴ የሚያነቃቃ ሁለገብ የፖሊሲ ፓኬጅን እንዲሁም የላቀ እና በይበልጥ አካታች የሆነ እድገትን ማምጣትይቻል ዘንድ ኢኮኖሚውን ክፍት ማድረግን ኢላማው ያደረገ ነው።
ማሻሻያው ተጋላጭ በሆኑ ቤተሰቦች/አባዎራዎች ላይ የሚኖረውን ተጽእኖ ለማለዘብ ይቻል ዘንድ የማህበራዊ ሴፍቲ ኔቶችን ማጠናከርም የመንግሥት የማሻሻያ ፕሮግራም አንድ ወሳኝ ክፍለአካል ነው። ቁልፍ የሚባሉት ፖሊሲዎችም የሚከተሉትን ያካትታሉ፡
1) ውጫዊ ኢሚዛናዊንትን ለመፍታት እና የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለማስታገስ በገበያ ወደሚወሰን የምንዛሪ ዋጋ መሄድ፤
2) የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍን በማዘመን የዋጋ ግሽበትን መዋጋት፤
3) የሀገር ውስጥ የገንዘብ ምንጮችን በማሰባብሰብ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ሕዝባዊ ወጪዎች ማዋል፤
4) ከውጪአበዳሪዎች ጋር የሚደረጉ ወቅታዊ የእዳ ሪስትረክቸሪንግ ስምምነቶችን በመፈጸም ጭምር የእዳ አከፋፈል ዘላቂነትን መመለስ እንዲሁም
5) ወሳኝ የሆኑ የማክሮ ፋይናንሺያል ተጋላጭነቶችን ለመቀነስ የመንግሥት ኢንተርፕራይዞችን የገንዘብ አቋም ማጠናከር።
ፕሮግራሙ ከልማት አጋሮች የሚገኝ ተጨማሪ የገንዘብ አቅርቦትን በማፋጠን እንዲሁም በመካሄድ ላይ ያለው የእዳ ሪስትረክቸሪንግ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የሚያደርግ ማዕቀፍ በመስጠት ረገድ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ከ7 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ብሄራዊ መታወቂያ ለመውሰድ ተመዝግበዋል
******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ለመውሰድ የተመዘገቡ ሰዎች ቁጥር ከ7 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ። በ364 የምዝገባ ጣቢያዎች አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወ/ሪት ቃልኪዳን አብርሃም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም በኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓትን በመዘርጋት ዜጎች እና ሕጋዊ ነዋሪዎች የመታወቅ መብታቸው እንዲረጋገጡ እና አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መንገድ ማግኘት እንዲችሉ የሚያደርግ ነው። በአሁኑ ጊዜም አገልግሎቱን ለሕዝቡ ተደራሽ ለማድረግ በ364 ጣቢያዎች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል።
ብሄራዊ መታወቂያ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መንገድ ማግኘት ከማስቻል ባለፈ በአገልግሎት ሰጪና ተቀባይ መካከል በሚኖር ግንኙነት ላይ እምነት እንዲዳብር፣ በግል እና በመንግሥት ተቋማት የማንነት ማረጋገጥ ሂደት በተቀላጠፈ መንገድ እንዲከናወን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133254
******
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ለመውሰድ የተመዘገቡ ሰዎች ቁጥር ከ7 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ። በ364 የምዝገባ ጣቢያዎች አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑም ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ወ/ሪት ቃልኪዳን አብርሃም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም በኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓትን በመዘርጋት ዜጎች እና ሕጋዊ ነዋሪዎች የመታወቅ መብታቸው እንዲረጋገጡ እና አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መንገድ ማግኘት እንዲችሉ የሚያደርግ ነው። በአሁኑ ጊዜም አገልግሎቱን ለሕዝቡ ተደራሽ ለማድረግ በ364 ጣቢያዎች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል።
ብሄራዊ መታወቂያ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መንገድ ማግኘት ከማስቻል ባለፈ በአገልግሎት ሰጪና ተቀባይ መካከል በሚኖር ግንኙነት ላይ እምነት እንዲዳብር፣ በግል እና በመንግሥት ተቋማት የማንነት ማረጋገጥ ሂደት በተቀላጠፈ መንገድ እንዲከናወን.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133254
በ2017 ጎንደር ከተማን
******
(ኢ ፕ ድ)
በ2017 ጎንደር ከተማን
የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሀይ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በከተማዋ በተፈጠረው አንጻራዊ ሰላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ማንሠራራት ጀምረዋል።
በከተማዋ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴውን ወደነበረበት ለመመለስ በርካታ ሥራዎች ተሠርተዋል ያሉት ከንቲባው በተያዘው በጀት አመትም ከተማዋን
እስካሁን በነበረው ሂደት መከላከያ ሠራዊት፣ የአካባቢው የጸጥታ ኃይልና ማህበረሰቡ በሰሩት የቅንጅት ሥራ በከተማዋ አንጻራዊ ሰላም ከመስፈኑም ባለፈ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ከነበሩበት ማንሠራራት እንደጀመሩ ተናግረዋል።
በአካባቢው በተፈጠሩ ችግሮች ከወልቃይትና በዙሪያው ካሉ አካባቢዎች የንግድ ትስስሩ ተስተጓጉሎ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን በተገኘው አንጻራዊ ሰላም ምርትና ሸቀጦች ወደ ከተማው እየገቡ በመሆኑ የከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ከነበረበት......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133256
ስማርት ሲቲ ለማድረግና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እየተሠራ ነው******
(ኢ ፕ ድ)
በ2017 ጎንደር ከተማን
ስማርት ሲቲ ለማድረግ እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እየተሠራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ተናገሩ። የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሀይ ለኢፕድ እንደገለጹት፤ በከተማዋ በተፈጠረው አንጻራዊ ሰላም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ማንሠራራት ጀምረዋል።
በከተማዋ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴውን ወደነበረበት ለመመለስ በርካታ ሥራዎች ተሠርተዋል ያሉት ከንቲባው በተያዘው በጀት አመትም ከተማዋን
ስማርት ሲቲ ለማድረግ እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን እየተሠራ ነው ብለዋል። እስካሁን በነበረው ሂደት መከላከያ ሠራዊት፣ የአካባቢው የጸጥታ ኃይልና ማህበረሰቡ በሰሩት የቅንጅት ሥራ በከተማዋ አንጻራዊ ሰላም ከመስፈኑም ባለፈ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ከነበሩበት ማንሠራራት እንደጀመሩ ተናግረዋል።
በአካባቢው በተፈጠሩ ችግሮች ከወልቃይትና በዙሪያው ካሉ አካባቢዎች የንግድ ትስስሩ ተስተጓጉሎ እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን በተገኘው አንጻራዊ ሰላም ምርትና ሸቀጦች ወደ ከተማው እየገቡ በመሆኑ የከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ ከነበረበት......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133256
የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለጎፋ ዞን አምሰት ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
****************
(ኢ ፕ ድ)
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጃዋር የተመራ ልዑክ በጎፋ ዞን በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 5 ሚሊዬን ብር ድጋፍ አደረገ።
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው የፍቅር ተምሳሌት የሆነው የድሬዳዋ ህዝብ በሀዘናችን ሰዓት ከጎናችን ስለሆናችሁ ምስጋና ይገባችዋል ብለዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
ድጋፉን ያስረከቡት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በአደጋው የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን በድሬዳዋ ህዝብ ስም ገልፀው ለተጎዱ ወገኖች መፅናናትን መመኘታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት ገልጿል።
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
****************
(ኢ ፕ ድ)
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጃዋር የተመራ ልዑክ በጎፋ ዞን በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 5 ሚሊዬን ብር ድጋፍ አደረገ።
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው የፍቅር ተምሳሌት የሆነው የድሬዳዋ ህዝብ በሀዘናችን ሰዓት ከጎናችን ስለሆናችሁ ምስጋና ይገባችዋል ብለዋል።
ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት በመደገፍ ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
ድጋፉን ያስረከቡት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በአደጋው የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን በድሬዳዋ ህዝብ ስም ገልፀው ለተጎዱ ወገኖች መፅናናትን መመኘታቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት ገልጿል።
ሐምሌ 23 ቀን 2016 ዓም
ማርሽ ቀያሪው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ
********************
(ኢ ፕ ድ)
መንግሥት አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራምን አስመልክቶ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻሉን አስታውቋል።
ከትናንት ጀምሮ ሥራ ላይ የዋለው ይህ ማሻሻያ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ልማትን ከማረጋገጥ እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ ምን ፋይዳ ይኖረዋል?
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ሰነድ እንደሚያትተው፤ እስካሁን የነበረው የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት የተረጋጋ የውጭ ምንዛሪ ተመንና ዝቅተኛ የዋጋ ንረት መኖሩን ለማረጋገጥ የታለመ ቢሆንም፣ በሂደት ግን ለጥቁር ገበያ መስፋፋት፣ ለከፍተኛ የዋጋ ንረት፣ በከበሩ ማዕድናት ለሚደረግ ሰፊ የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲሁም የውጭ ምንዛሪ ከባንክ ሥርዓት ውጭ እንዲሆንና ከሀገር እንዲሸሽ አንዱና ዋነኛ ምክንያት ሆኗል።
ይህ ሁሉ ከአምራች ዘርፎች ይልቅ ጥቂት ሕገወጦችና ደላሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑና ሥር የሰደደ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንዲከሰት አድርጓል።
በዚህ የተነሣ በርካታ የንግድ ድርጅቶችና ባለሀብቶች ተጎጂ ሆነዋል፤ የወጪ ንግድንና የፋብሪካ ምርቶችን ለማስፋፋት፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለማሳደግ የተቀመጡ.......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133251
********************
(ኢ ፕ ድ)
መንግሥት አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራምን አስመልክቶ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ማሻሻሉን አስታውቋል።
ከትናንት ጀምሮ ሥራ ላይ የዋለው ይህ ማሻሻያ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ልማትን ከማረጋገጥ እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ከማድረግ አኳያ ምን ፋይዳ ይኖረዋል?
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ሰነድ እንደሚያትተው፤ እስካሁን የነበረው የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት የተረጋጋ የውጭ ምንዛሪ ተመንና ዝቅተኛ የዋጋ ንረት መኖሩን ለማረጋገጥ የታለመ ቢሆንም፣ በሂደት ግን ለጥቁር ገበያ መስፋፋት፣ ለከፍተኛ የዋጋ ንረት፣ በከበሩ ማዕድናት ለሚደረግ ሰፊ የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲሁም የውጭ ምንዛሪ ከባንክ ሥርዓት ውጭ እንዲሆንና ከሀገር እንዲሸሽ አንዱና ዋነኛ ምክንያት ሆኗል።
ይህ ሁሉ ከአምራች ዘርፎች ይልቅ ጥቂት ሕገወጦችና ደላሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑና ሥር የሰደደ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እንዲከሰት አድርጓል።
በዚህ የተነሣ በርካታ የንግድ ድርጅቶችና ባለሀብቶች ተጎጂ ሆነዋል፤ የወጪ ንግድንና የፋብሪካ ምርቶችን ለማስፋፋት፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለማሳደግ የተቀመጡ.......
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://press.et/?p=133251
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
በጎንደር ከተማ የፋሲል ቤተመንግስት እድሳት ተጀምሯል። በጣም ጥሩ ሁኔታ ላይም ይገኛል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ፋሲልን ወደ ቀደመ ግርማ ሞገሱ እንመልሰዋለን።
በጎንደር ከተማ የፋሲል ቤተመንግስት እድሳት ተጀምሯል። በጣም ጥሩ ሁኔታ ላይም ይገኛል። በአጭር ጊዜ ውስጥ ፋሲልን ወደ ቀደመ ግርማ ሞገሱ እንመልሰዋለን።